cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

የኛ ግጥም ና ታሪክ

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
164
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Фото недоступнеДивитись в Telegram
“የምኒልክ ፈረስ በክንፎቹ ሔደ” ምኒልክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ ግብሩ እንቁላል ነበር ይኸን ጊዜ አበሻ፡፡ በሠራው ወጨፎ ባመጣው እርሳስ ተፈጠመ ጣልያን አበሻ እንዳይደርስ፡፡ ምኒልክ ተጉዞ የምትጠይቁኝ ፊትም አላለፈ ኋላም አይገኝ፡፡ መድፋን መትረየሱን ባድዋ መሬት ዘርቶ እንክርዳዱን ነቅሎ ስንዴውን ለይቶ የዘራውን እህል አጭዶና ወቅቶ ላንቶኔሊ አሳየው ፍሬውን አምርቶ፡፡ እንዳቀና ብሎ ለምኖ መሬት ንግድ ሊያሰፋበት ሊዘራ አትክልት እየመጣ ሊሰጥ ግብሩን ለመንግሥት ለጓዙ ማረፊያ አገር ቢሰጡት ተጠማኝ ሰንብቶ ሆኖ ባለርስት ወሰን እየገፋ ጥቂት በጥቂት እውነት እርስት ሆነው ተቀበረበት፡፡ ባሕር ዘሎ መምጣት ለማንም አትበጅ እንደ ተልባ ስፍር ትከዳለች እንጂ አትረጋምና ያለተወላጅ፡፡ የዳኛው አሽከሮች እየተባባሉ ብልት መቆራረጥ አንድነት ያውቃሉ #ዓድዋ ከከተማው ሥጋ ቆርጠው ጣሉ፡፡ የእስክንድር ፈረስ መቼ ተወለደ የምኒልክ ፈረስ በክንፎቹ ሔደ፡፡ ደንገላሳ ሲዘል እየተንጓደደ የሮማውን ኩራት በእግታ አሰገደ፡፡ አገርህን ምኒልክ እንዳሁን ፈትሻት እጁን ቀምሼ አላውቅም እያለ ሲያማህ ቀመሰና እጅህን መጥቶ ጠላትህ ሮም ላይ ተሰማ ለጋስ መሆንህ፡፡ አባተ በመድፋ አምሳውን ሲገድል ባልቻ በመትረየስ ነጥሎ ሲጥል የጐጃሙ ንጉሥ ግፋ በለው ሲል እቴጌ ጣይቱ እቴጌ ብርሃን ዳዊቷን ዘርግታ ስምዓኒ ስትል ተማራኪው ባዙቅ ውሃ ውሃ ሲል ዳኛው ስጠው አለ ሠላሳ በርሜል፡፡ እንደ በላዔ ሰብአ እንደመቤታችን ሲቻለው ይምራል የኛማ ጌታችን፡፡ 🔘ተክለ ጻድቅ መኩሪያ🔘
Показати все...
#አድዋ_ዛሬ_ናት_አድዋ_ትላንት ፡ ፡ #በአሌክስ_አብርሃም (አንቀፅ 17 ፡ እኛም መስኮታችንን አንከፍትም፣ እናንተም ሚስቶቻችንን አትዩ ፡) ጣሊያን ኢትዮጵያን ወርራ አምስት ዓመት ፍዳዋን በልታ፣ ፍዳችንን ስታሰበላን አያቴ እሳት የላሰ የውስጥና የውጭ አርበኛ ነበር። በጦር ሜዳ ብትሉ አንድ ባታሊዮን ጦር ጭጭ ምጭጭ ያደረገ ጀግና ሲሉት፣ “ኤዲያ ምን አላት እቺ” ይላል !! በከተማ ብትሉ" ጠላት መኝታ ቤት ሳይቀር የተቀመጠ ሚስጥር ፈልፍሎ ሲያወጣ አጀብ ያስብል ነበር። ታዲያ በአያቴና በቆራጥ አርበኞች ትግል ፋሺስት ኢጣሊያንን ከሀገር ከተባረረ በኋላ፣ ለአገር በሠራው ታላቅ ጀብዱ፣ በድል አጥቢያ ጃንሆይ ራሳቸው አስጠርተው አሁን የጣልያን ኤምባሲ የሚባለው የተገነባበትን ቦታ በሙሉ ከታላቅ ክብርና ምስጋና ጋር በሽልማት ለኢያቴ ሰጡት ! አያቴ እዚሁ በሽልማት የተሰጠው ቦታ ላይ ትንሽ ጎጆ ቀልሶና፣ የተረፈው ሜዳ ላይ የቆሎ ዘርቶ ሲኖር፣ አንድ ቀን የጃንሆይ መልዕክተኞች ሲገሰግሱ ቤቱ ድረስ መጡና፣ “እዚህ በቆሎ የዘራህበት ቦታ ላይ የንባሲዮን ሊሰራሰት ነውና መድረሻህን ፈልግ ብለውሃል ጃንሆይ አሉት። “ኧረ ውሰዱት ደሞ ለሞላ ቦታ አላቸው። ትንሽ ቆይቶ፣ “ይሄ ግን 'የንምባሲዮን' ያላችሁት ነገር መንግስት ነው ?” ሲል ጠየቀ። “አይደለም !" “አሃ ተማሪ ቤት መሆን አለበት :" “አይደለም!” ታዲያ ምንደን ነው ቤተስክያን ይሆን እንዴ ?" ሲል ግር ብሎት ጠየቀ። "ኤማቢሲዎን ማለትንጉሥ የፈቀዱላቸው የውጭ አገር መኳንት እና መሳፍንት አገራቸውን መስለው የሚቀመጡበት እና አንዳንድ የመንግሥት ሥራዎችን የሚከውኑበት ማረፊያ ነው" አሉት ሳኔ ዕክተኞቹ አንዱ። ከመልክተኞቹ አንዱ። "በቃ ?" ሲል ጠየቀ አያቴ በግርምት። "በቃ!" "እኮ ፈረንጆች ይሄን ሁሉ ቦታ አጥረው ቁጭ ሊሉ ነው” አለ እንደገና በታላቅ ግርምት። "አዎ ! ይሄ የምባሲዮን ... የወከላቸው አገር የማይደፈር ግዛት ነው” እንዲያ ድንበራችን ላይ ያባረርነውን ጠላት መናገሻችን ላይ አርደንለት ጋርደንለት ልናስቀምጠው ነው በለኛ አለ አያቴ በቁጭት። መልዕከተኞቹ አያቴ ላይ ሳቁበት። ስለኤምባሲ ያለው እውቀት አነስተኛ መሆኑን በመገንዘባቸው ድፍን ሁለት ሰዓት ስለኤምባሲ ተግባርና ለአጎራችን ስላለው ጠቀሜታ በዝርዝር አወሩት። ተግባብተው ሊለያዩ ሲሉ ግን ነገር ተበላሽ።ጉድፈላ። አገር ተሸበረ።ድንገት ነው ነገሩ የተመሰቃቀለው ከሆነስ ሆነና የማን አገር ኤምባሲዮን ነው ?" ሲል ጠየቀ አያቴ፣ “ጥልያን” ብለው መለሱለት። "ጥልያን ጥሊያን ... እኮ ጥሊያን ይሄ ፋሽስት የነበረው" አለ አያቴ ማመን አቅቶት። "እንዴታ አሁን በሰላም መጥተዋል” አያቴ ሰይጣኑ ተነሳ። ተንደርድሮ ምንሽሩን መዥረጥ አደረገና ለግማሽ ሰዓት ያህል ፎክሮ ሲያበቃ፣ "ባንዳ ሁላ…” ብሎ የጃንሆይን መልዕክተኞች ማሳደድ ጀመረ ! ጥሎብን መከተል እንወዳለን። መንገድ ላይ ድንገት አያቴን ያዩ ሁሉ፡ ገና የአርበኝነት ስሜቱ ያልበረደላቸው፣ እንዲሁም አርበኝነት ያመለጣቸው፣ እንደገና እድሉን አገኘን በማለት ምንሽራቸውን አፈፍ እያደረጉ፣ “ያዘው…" እያሉ ላይጠቅማቸው አያቴን ተቀላቅለው የንጉሱን መልእክተኞች ማሳደድ ጀመሩ። መቼስ አዲሳባ እንደዛን ቀን ተፎክሮባትም፣ ተሸልሎባትም አያውቅም ሲሉ ሁኔታውን የታዘቡ፡፡ አያቴ ቁጣው መለስ ሲል ዞሮ ቢመሰከት ድፍን የአዲስ አበባ ወንድ ተከትሎታል። “ምን ሆናችሁ” ቢላቸው አያቴ፣ “አይ ሩጫው ወደ ቤተ መንግሥት መሆኑን ስንሰማ ነው የተከተልኛችሁ” አሉ !! አያቴ የተከታዩን ብዛት አየና በዛው ሸፈተ ! ስሙ የገነነ ሽፍታም ሆነ ! ስሙ ከተጠራ እንኳን ኢትዮጵያ ምድር ያሉት ሮም የተቀጡትም ጥልያኖች ወባ እንደያዘው እየተንዘፈዘፉ ንሰሃ ይገባሉ ! ጭራሽ የኤምባሲው ግንባታ ሲጀመር በወርም በሳምንትም በል ሲለው በየሦስት ቀኑ ብቅ እያለ ይሄን ጣልያን ሁሉ ይፈጀው ጀመረ !! ጃንሆይ በበኩላቸው አያቴን በዲፕሎማሲ ማሳመን መርጠው መልዕክት ላኩበት። በድፍረት ከነጎፈረ ጸገሩና ከነምንሽሩ ፊታቸው ቀርቦ፤ "ጃንሆይ ትላንት ይሄን ፋሽስት፣ እንኳን አሳረርከው' ብዬ የሸለሙኝን ቦታ ዛሬ ከኔ ነጥቀው ላባረርኩት ሰላቶ በመስጠትዎ ተቀይሜዎታለሁ !! እማምላክን ተቀይሜዎታለሁ። እንዴት እንዴት ነው ነገሩ ... እዚህች አገር አባራሪው ከተባራሪው ተደባለቀ እኮ ዳር ላይ ያባረርነው ከመሐል እያባረረን ተቸገር?" አለ። ጃንሆይ በጥሞና ሲያደምጡ ቆዩና፣ “ቅሬታህን ሰምተናል። ካንተ የሚበልጥብን የለም። ያው አንተ ዳር ላይ ልክ ያስገባሃቸው ናቸው ዛሬ ወዳጅነታችንን ፈልገው በእንብርክክ ደጅ የጠኑን እንደምታውቀው ጀግና በጠብ የመጡበትን አንጂ በፍቅር የመጣን አይነኩም አሉና የአያቴን ቁጣ አበረዷት። “በል አሁን በቃህ ለማን ብለህ ነው መሬትህን ጥለህ የምትሄደው፡፡ እነሱ እያዩህ ይሸማቀቁ እንጂ ብለው እዛው ኤምባሲው ጎን ለአያቴ ሰፊ ቦታ ሰጡት። እርቅ ወረደ! ንጉሡ ብልህ ነበሩ። አንዳንዴ አያቴን ይጠሩትና፣ ጎረቤቶችህ ሰላም ናቸው ? ብለው ይጠይቁታል። አያቴን ሰላይ አደረጉት እንግዲህ የአያቴ ጎጆ እና የጣሊያን ኤምባሲ በግንብ አጥር ብቻ ነበር የሚለያዩት። አያቴ ጣልያኖቹን ባያቸው ቁጥር ደሙ እየፈላ፣ "ወይ ነዶ የማንም ፋሽስት ጋር እንዲህ ትከሻ ለትካሻ እየተጋፋሁ ልኖር” እያለ በብስጭት ሲግል ሚስቱ ወይዘሮ በልጅጌ መኮንን (የፊታውራሪ መኮንን እጅጉ የመጀመሪያ ልጅ እያባበለች ወደ መኝታ ቤታቸው ትወስደውና ከብስጭቱ አብርዳ በሌላ ጉዳይ ትለኩሰዋለች ! አቤት ማባበል ስታውቅበት …. ገና ስትታይ ነገር ታበርዳለች ... እሳት ፈገግታዋ እሳት ያጠፋል ... ይች ውብና አስተዋይ ሴት ሲበሳጭ ስታባብለው፣ ሲበሳጭ ስታባብለው .… አምስት ሴትና አንድ ወንድ ልጅ ወለዱ። ይሄ ብቸኛ ወንድ ልጅ የእኔ አባት ነበር። አያቴ ምንም እንኳን የልጆቹን አእምሮ በምክር አርሶና አለስልሶ የጣሊያንን ጥላቻ ቢዘራበትም አልፀደቀም። በተለይ ሴት ልጆቹ ያማረ መኪና ይዘው የሚገቡና የሚወጡ የጣልያን ጎረምሶች ላይ ልባቸው አልጨክን እያለ፣ ዓይናቸውም እየተንከራተተ አስቸገረው። ጭራሽ ይለይልህ ብለው ከአባቴ በስተቀር ሁሉም ሶላቶ' አግብተው ቁጭ አሉ። በዚሁ ብስጭት ሙሉ ቦታውን ለአባቴ ብቻ አውርሶና ጥልያን ያገቡ ልጆቹን ሁሉ ክዶ ሚስኪን አያቴ በደም ግፊት ሞተ !! አባቴም፡ 'ሙሉ' የምትባል ውብ ሴት አግብቶ እዚሁ ነገረኛ የወርስ ቦታ ላይ ቤት ሰርቶ መኖር ጀመረ (ሙሉ እናቴ ናት…)። እናቴ ሙሉ መቼስ ወላ በቁንጅና፣ወላ ሰባሕሪ ቢባል ይሄ ቀረሽ የማትባል ውብ ናት። ስትገባ ስትመጣ ተመልካቹ በዛ፣ የሚመኛት እልፍ ነበር። አባቴ ታዲያ እናቴ ስትደነቅና ስትሞገስ ደስ ቢለውም፣ ከተመልካቹ ሁሉ ደሙን የሚያፈላው የጣልያኖቹ አስተያየት ነበረ። እንግዲህ ጣልያኖቹ እናቴ ስታልፍ ፊታቸው እንደ ቲማቲም ቀልቶ አፋቸውንም፣ ዓይናቸውንም በልጥጠው በአጥራቸው ላይ እየተንጠላጠሉ በአጉል ምኞት ሲመለከቷት አባቴ ይሰሳጫል፤ በላቸው በላቸው ይለዋል። (ደግሞ ለማለት፣ አያቴ እንደሆነ ምንሽሩን አውርሶታል- መታገስ ደግ ነው ብሎ እንጂ…)
Показати все...
ምድረ ሰላቶ ከዘበኛ እስከ አምባሳደር ማፍጠጣቸው ሳያንስ፣ “ለደህንነት” በሚል ሰበብ ፊታቸውን ወደ እኛ ግቢ ያዞሩ አራት ካሜራዎች ተከሉ። እናቴ ግቢ ውስጥ በተንቀሳቀሰች ቁጥር አራቱም ካሜራዎች ወደሄደችበት ተከትለዋት ይዞራሉ (የምታጠባቸው መንታ ልጆቿ ነበር የሚመስሉት)። ሌላ ሰው ሲንቀሳቀስ ካሜራዎቹ ግኡዝ ናቸው። ካሜራዎቹ የተተከሉት ለደህንነት ይሁን ላጉል ምኞት አባቴ ግራ ገባው። ጭራሽ ጥልያኖች ባሳተሙት አንድ ዓመታዊ መጽሔታቸው ላይ እናቴ አጎንብሳ አሮጌ የመኪና ጎማ ላይ በተቀመጠ ጥሰት ልብስ ስታጥብ ከኋላዋ (ያውም አጭር የውስጥ ልብስ ብቻ ለብሳ) የሚያሳይ ባለቀለም ፎቶ ተካትቶ ነበር። ከእናቴ ፎቶ ጎን አንዲት ጥላ ቢስ፣ ሽርጥ ያሸረጠች ጣልያናዊት ኮረዳ ዘመናዊ የልብስ ማጠቢያ ማሽን ደገፍ ብላ የሚያሳይ ፎቶ አለ። ከፎቶዎቹ ሥር፣ “ኢትዮጵያ ከጣልያን ስድስት ዘመናዊ የልብስ ማጠቢያ ማሽኖች ለእርዳታ አገኘች ይህም የኢትዮጵያዊያንን ሴቶች ድካም በመቀነስ ጊዜያቸውን ለሌላ ጉዳይ እንዲያውሉት ይረዳሉ የሚል ጽሁፍ ሰፍሯል። ሌላው ጉዳይ' ምንድን ነው ሲል አባቴ አሰበ። እንዴት የሚስቴኝ ፎቶ ካለ እሷም ካለእኔም ፍቃድ መጽሔት ላይ ያትማሉ፣ ሲል ተብከነከነ፡ እንደውም አምባሳደሩን ራሱን ማብራሪያ እንዲሰጠው ሊጠይቀው ወሰነ። ሰውን ካለፍቃዱ፣ ያውም በገዛ ግቢው ውስጥ፣ እንዴት ፎቶ ያነሳሉ … ያውም በአጭር የውስጥ ልብስ ብቻ ይሄ ንቀት ነው አባቴ በቀጥታ ወደ ኤምባሲው ዋና በር ሄደና እንደ ግለሰብ መኖሪያ ቤት አስፈሪውን የብረት በር አንኳኳ፣ ጓጓጓጓጓ ዘበኛው አጨንቁሮ አባቴን ከተመለከተ በኋላ በሩን ከፍቶ ባለማመን እያየው፣ “ምን ፈለግክ ?” አለው እርዳታ የፈለገ ኢትዮጵያዊ ይሆናል ብሎ፣ “ጌታህን ጥራው ! ባልቻ በርህ ላይ ይፈልግሃል አለው" አለ አባቴ ቆፍጠን ብሎ። ዘበኛው ግራ ተጋባና፣ “ማንን ነው የጥበቃ አልቃውን ነው ?” አለ። “እሱ ምን ያደርግልኛል ? አምባሳደሩን ነው ያልኩሆ "እ ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ … በል ሂድ ወደዛ ደፋር ብሎት እርፍ አባቴ ባልቻን ! መንደሩ የተከበረውን ኣባቴን እንደ ምጽዋት ፈላጊ የሶላቶዎቹ ዘበኞ፣ ሂድ ወደዛ አለው ! በዛችው ቅፅበት ከአባቴ የተሰነዘረ ብርቱ ጥፊ ዘበኛውን አባቴ እግር ሥር ኩርምት አደረገው። የጥፊው ድምጽ ሮም ድረስ ስለተሰማ፣ የውቅቱ የጣሊያን መንግሥት፣ ኢትዮጵያ ዓለማቀፉን የኤምባሲዮን ውል እና አሰራር በመተላለፍ የተከበረ ዜጋዬን በጥፊ በመደርገም በአድዋ ካደረሰችብኝ ውርደት የበለጠ ውርደት አድርሳብናለች ሲል ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አቤት አለ። ጃንሆይም በዚሁ ጕዳይ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ ተጠይቀው፣ “በእርግጥ አፍሪቃ ኤሮፓዊያን ቅኝ ግዛት እየታመሰችበት ባለችበት በዚህ ወቅት፣ ብዛሃን የአፍሪቃ ልጆች በቆዳቸው ቀለም ምክንያት በግፍ እየተገደሉ እና እየተገፉ ባሉበት ወቅት፣ በአንዲት ኤሮፓዊት አገር ኤምባሲ የጥበቃ ሰራተኛ ላይ፣ ያውም በራሱ ስህተት፣ በተሰነዘረ ጥፊ ዓለም ይህን ያህል መንጫጫቱ ገርሞናል። ይህ ጥፊ የኢትዮጵያ መንግሥትን የማይወክል፣ በዕለት ግጭት የተከሰተ ድንገተኛ ጥረቀማ በመሆኑ ግለሰቦቹ በቀላል ሽምግልና ችግሩን እንዲፈቱት እናደርጋለን። አገራችንም ከጥፊው ባሻገር ለአፍሪቃ ብሎም ለዓለም ያበረከተችው ቀጎ ተግባር በዚህ ጥፊ ምክንያት ሊጠለሽ አይገባም” በማለት ዓለምን ያስደነቀ፣ አገሬውንም ያኮራ ንግግር አደረጉ። በዚህ ንትርክ መሃል የእናቴ ፎቶ ጉዳይ ተድበሰሰሰ። በጣልያኖች ተንኮል እልህ የተጋባው አባቴ፣ “ልጆቼ ስለበረከቱ ፎቅ ቤት እሰራለሁ…” አለና ማንንም ሳያስፈቅድ ባለ ሁለት ፎቅ ቪላ ወደ ኤምባሲው አጥር እስጠግቶ መሥራት ጀመረ። ይሁንና ጣልያኖች ለደህንነታችን ያሰገናል በማለት ክስ አቀረቡ። ኤምባሲ ጎን ፎቅ መሥራት ክልክል ነው ተብሎ አባቴ ታገደ አገሬ ላይ እስከ ጨረቃስ ፎቅ ብሥራ ምን አገባችሁ ?” በማለት ጠየቀ። “ለወዳጃችን የጣልያን መግሥት ስጋት ስለሚፈጥር፣ ለደህንነታቸውም ስለሚያሰጋ አይፈቀድልህም አቶ ሳልቻ” አሄሄ እነሱን ለመግደል ማን ፎቅ ይሰራል … ውቤ በረሃ ሲያውደለድሉ አይደለም የሚውሉት…” ሥርዓት ጌታው፣ እንግዶቻችንን ማክበር የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው” ጉዳዩ በጣም ተጋነነና በአባትና በጣልያኑ አምባሳደር መካከል የሁለትዮሽ ድርድር ሲካሄድ የተሻለ ነው በማለት በጃንሆይ ልዩ አማካሪዎች አስተባባሪነት በጣልያን መንግሥትና በአባቴ ባልቻ መካከል ታሪካዊ ድርድር ተካሄደ። ይህ ድርድር በታሪክ፣ አንቀጽ 17 - እኛም መስኮታችንን አንከፍትም እናንተም ሚስቶቻችንን አትዩ” በመባል ይታወቃል የውሉ ዋና ዋና ነጥቦች! አንቀፅ 1. አቶ ባልቻ ደመቀ ኤምባሲያችን ጎን የሚሰሩት ፎቅ መስኮቱ ወደ ጣልያን ኤምባሲ ላይ ላይዞር ከዞረም ላይከፈት። አንቀፅ 2. ጣልያኖች ወደ ኤምባሲው ሲገቡና ሲወጡ አሁን ያሉትንም ሆነ ወደፊት የሚወለዱትን የአቶ ባልቻን ሴት ልጆች በቃልም ሆነ በድርጊት ላይተናኮሱ፧ በመኪናም ሆነ በእግር በር ላይ ላይንጎማለሉ ሆን ብለው ስሜት ቀስቃሽ እና አማላይ ድርጊት ላይፈፅሙ። . . . . . . አንቀጽ 17. ወደ አቶ ባልቻ ቤት የዞሩት የኤምባሲው የቪዲዮም ይሁኑ የፎቶ ካሜራዎች ሙሉ በሙሉ እንዲነሱ። የዚህ ውል 17 ኛው አንቀጽ የጣልያኑ ትርጉም ግን እንዲህ ይል ነበረ፣ የኤምባሲያችን የቪዲዮም ይሁኑ የፎቶ ካሜራዎች፣ የሙሉን እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ ፎቶ ሊያነሳ ፈቃድ አላቸው ይላል። ታሪክ ራሱን ይደግማል !! እናቴ ሙሉ ታዲያ ከንፈሯን ሸምም አድርጋ የተንኮል ፈገግታ ፈገግ አለች። ማንም አላያት ከሰይጣን እና ከእኔ በስተቀር። ትንሽ ወንድሜ አባቴን አለመምሰሉ እንደውም ፈረንጅ መምሰሉ እስቋት ይሆን.! ✨አለቀ✨
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ምድረ ሰላቶ ከዘበኛ እስከ አምባሳደር ማፍጠጣቸው ሳያንስ፣ “ለደህንነት” በሚል ሰበብ ፊታቸውን ወደ እኛ ግቢ ያዞሩ አራት ካሜራዎች ተከሉ። እናቴ ግቢ ውስጥ በተንቀሳቀሰች ቁጥር አራቱም ካሜራዎች ወደሄደችበት ተከትለዋት ይዞራሉ (የምታጠባቸው መንታ ልጆቿ ነበር የሚመስሉት)። ሌላ ሰው ሲንቀሳቀስ ካሜራዎቹ ግኡዝ ናቸው። ካሜራዎቹ የተተከሉት ለደህንነት ይሁን ላጉል ምኞት አባቴ ግራ ገባው። ጭራሽ ጥልያኖች ባሳተሙት አንድ ዓመታዊ መጽሔታቸው ላይ እናቴ አጎንብሳ አሮጌ የመኪና ጎማ ላይ በተቀመጠ ጥሰት ልብስ ስታጥብ ከኋላዋ (ያውም አጭር የውስጥ ልብስ ብቻ ለብሳ) የሚያሳይ ባለቀለም ፎቶ ተካትቶ ነበር። ከእናቴ ፎቶ ጎን አንዲት ጥላ ቢስ፣ ሽርጥ ያሸረጠች ጣልያናዊት ኮረዳ ዘመናዊ የልብስ ማጠቢያ ማሽን ደገፍ ብላ የሚያሳይ ፎቶ አለ። ከፎቶዎቹ ሥር፣ “ኢትዮጵያ ከጣልያን ስድስት ዘመናዊ የልብስ ማጠቢያ ማሽኖች ለእርዳታ አገኘች ይህም የኢትዮጵያዊያንን ሴቶች ድካም በመቀነስ ጊዜያቸውን ለሌላ ጉዳይ እንዲያውሉት ይረዳሉ የሚል ጽሁፍ ሰፍሯል። ሌላው ጉዳይ' ምንድን ነው ሲል አባቴ አሰበ። እንዴት የሚስቴኝ ፎቶ ካለ እሷም ካለእኔም ፍቃድ መጽሔት ላይ ያትማሉ፣ ሲል ተብከነከነ፡ እንደውም አምባሳደሩን ራሱን ማብራሪያ እንዲሰጠው ሊጠይቀው ወሰነ። ሰውን ካለፍቃዱ፣ ያውም በገዛ ግቢው ውስጥ፣ እንዴት ፎቶ ያነሳሉ … ያውም በአጭር የውስጥ ልብስ ብቻ ይሄ ንቀት ነው አባቴ በቀጥታ ወደ ኤምባሲው ዋና በር ሄደና እንደ ግለሰብ መኖሪያ ቤት አስፈሪውን የብረት በር አንኳኳ፣ ጓጓጓጓጓ ዘበኛው አጨንቁሮ አባቴን ከተመለከተ በኋላ በሩን ከፍቶ ባለማመን እያየው፣ “ምን ፈለግክ ?” አለው እርዳታ የፈለገ ኢትዮጵያዊ ይሆናል ብሎ፣ “ጌታህን ጥራው ! ባልቻ በርህ ላይ ይፈልግሃል አለው" አለ አባቴ ቆፍጠን ብሎ። ዘበኛው ግራ ተጋባና፣ “ማንን ነው የጥበቃ አልቃውን ነው ?” አለ። “እሱ ምን ያደርግልኛል ? አምባሳደሩን ነው ያልኩሆ "እ ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ … በል ሂድ ወደዛ ደፋር ብሎት እርፍ አባቴ ባልቻን ! መንደሩ የተከበረውን ኣባቴን እንደ ምጽዋት ፈላጊ የሶላቶዎቹ ዘበኞ፣ ሂድ ወደዛ አለው ! በዛችው ቅፅበት ከአባቴ የተሰነዘረ ብርቱ ጥፊ ዘበኛውን አባቴ እግር ሥር ኩርምት አደረገው። የጥፊው ድምጽ ሮም ድረስ ስለተሰማ፣ የውቅቱ የጣሊያን መንግሥት፣ ኢትዮጵያ ዓለማቀፉን የኤምባሲዮን ውል እና አሰራር በመተላለፍ የተከበረ ዜጋዬን በጥፊ በመደርገም በአድዋ ካደረሰችብኝ ውርደት የበለጠ ውርደት አድርሳብናለች ሲል ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አቤት አለ። ጃንሆይም በዚሁ ጕዳይ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ ተጠይቀው፣ “በእርግጥ አፍሪቃ ኤሮፓዊያን ቅኝ ግዛት እየታመሰችበት ባለችበት በዚህ ወቅት፣ ብዛሃን የአፍሪቃ ልጆች በቆዳቸው ቀለም ምክንያት በግፍ እየተገደሉ እና እየተገፉ ባሉበት ወቅት፣ በአንዲት ኤሮፓዊት አገር ኤምባሲ የጥበቃ ሰራተኛ ላይ፣ ያውም በራሱ ስህተት፣ በተሰነዘረ ጥፊ ዓለም ይህን ያህል መንጫጫቱ ገርሞናል። ይህ ጥፊ የኢትዮጵያ መንግሥትን የማይወክል፣ በዕለት ግጭት የተከሰተ ድንገተኛ ጥረቀማ በመሆኑ ግለሰቦቹ በቀላል ሽምግልና ችግሩን እንዲፈቱት እናደርጋለን። አገራችንም ከጥፊው ባሻገር ለአፍሪቃ ብሎም ለዓለም ያበረከተችው ቀጎ ተግባር በዚህ ጥፊ ምክንያት ሊጠለሽ አይገባም” በማለት ዓለምን ያስደነቀ፣ አገሬውንም ያኮራ ንግግር አደረጉ። በዚህ ንትርክ መሃል የእናቴ ፎቶ ጉዳይ ተድበሰሰሰ። በጣልያኖች ተንኮል እልህ የተጋባው አባቴ፣ “ልጆቼ ስለበረከቱ ፎቅ ቤት እሰራለሁ…” አለና ማንንም ሳያስፈቅድ ባለ ሁለት ፎቅ ቪላ ወደ ኤምባሲው አጥር እስጠግቶ መሥራት ጀመረ። ይሁንና ጣልያኖች ለደህንነታችን ያሰገናል በማለት ክስ አቀረቡ። ኤምባሲ ጎን ፎቅ መሥራት ክልክል ነው ተብሎ አባቴ ታገደ አገሬ ላይ እስከ ጨረቃስ ፎቅ ብሥራ ምን አገባችሁ ?” በማለት ጠየቀ። “ለወዳጃችን የጣልያን መግሥት ስጋት ስለሚፈጥር፣ ለደህንነታቸውም ስለሚያሰጋ አይፈቀድልህም አቶ ሳልቻ” አሄሄ እነሱን ለመግደል ማን ፎቅ ይሰራል … ውቤ በረሃ ሲያውደለድሉ አይደለም የሚውሉት…” ሥርዓት ጌታው፣ እንግዶቻችንን ማክበር የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው” ጉዳዩ በጣም ተጋነነና በአባትና በጣልያኑ አምባሳደር መካከል የሁለትዮሽ ድርድር ሲካሄድ የተሻለ ነው በማለት በጃንሆይ ልዩ አማካሪዎች አስተባባሪነት በጣልያን መንግሥትና በአባቴ ባልቻ መካከል ታሪካዊ ድርድር ተካሄደ። ይህ ድርድር በታሪክ፣ አንቀጽ 17 - እኛም መስኮታችንን አንከፍትም እናንተም ሚስቶቻችንን አትዩ” በመባል ይታወቃል የውሉ ዋና ዋና ነጥቦች! አንቀፅ 1. አቶ ባልቻ ደመቀ ኤምባሲያችን ጎን የሚሰሩት ፎቅ መስኮቱ ወደ ጣልያን ኤምባሲ ላይ ላይዞር ከዞረም ላይከፈት። አንቀፅ 2. ጣልያኖች ወደ ኤምባሲው ሲገቡና ሲወጡ አሁን ያሉትንም ሆነ ወደፊት የሚወለዱትን የአቶ ባልቻን ሴት ልጆች በቃልም ሆነ በድርጊት ላይተናኮሱ፧ በመኪናም ሆነ በእግር በር ላይ ላይንጎማለሉ ሆን ብለው ስሜት ቀስቃሽ እና አማላይ ድርጊት ላይፈፅሙ። . . . . . . አንቀጽ 17. ወደ አቶ ባልቻ ቤት የዞሩት የኤምባሲው የቪዲዮም ይሁኑ የፎቶ ካሜራዎች ሙሉ በሙሉ እንዲነሱ። የዚህ ውል 17 ኛው አንቀጽ የጣልያኑ ትርጉም ግን እንዲህ ይል ነበረ፣ የኤምባሲያችን የቪዲዮም ይሁኑ የፎቶ ካሜራዎች፣ የሙሉን እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ ፎቶ ሊያነሳ ፈቃድ አላቸው ይላል። ታሪክ ራሱን ይደግማል !! እናቴ ሙሉ ታዲያ ከንፈሯን ሸምም አድርጋ የተንኮል ፈገግታ ፈገግ አለች። ማንም አላያት ከሰይጣን እና ከእኔ በስተቀር። ትንሽ ወንድሜ አባቴን አለመምሰሉ እንደውም ፈረንጅ መምሰሉ እስቋት ይሆን.! ✨አለቀ✨
Показати все...
#አድዋ_ዛሬ_ናት_አድዋ_ትላንት ፡ ፡ #በአሌክስ_አብርሃም (አንቀፅ 17 ፡ እኛም መስኮታችንን አንከፍትም፣ እናንተም ሚስቶቻችንን አትዩ ፡) ጣሊያን ኢትዮጵያን ወርራ አምስት ዓመት ፍዳዋን በልታ፣ ፍዳችንን ስታሰበላን አያቴ እሳት የላሰ የውስጥና የውጭ አርበኛ ነበር። በጦር ሜዳ ብትሉ አንድ ባታሊዮን ጦር ጭጭ ምጭጭ ያደረገ ጀግና ሲሉት፣ “ኤዲያ ምን አላት እቺ” ይላል !! በከተማ ብትሉ" ጠላት መኝታ ቤት ሳይቀር የተቀመጠ ሚስጥር ፈልፍሎ ሲያወጣ አጀብ ያስብል ነበር። ታዲያ በአያቴና በቆራጥ አርበኞች ትግል ፋሺስት ኢጣሊያንን ከሀገር ከተባረረ በኋላ፣ ለአገር በሠራው ታላቅ ጀብዱ፣ በድል አጥቢያ ጃንሆይ ራሳቸው አስጠርተው አሁን የጣልያን ኤምባሲ የሚባለው የተገነባበትን ቦታ በሙሉ ከታላቅ ክብርና ምስጋና ጋር በሽልማት ለኢያቴ ሰጡት ! አያቴ እዚሁ በሽልማት የተሰጠው ቦታ ላይ ትንሽ ጎጆ ቀልሶና፣ የተረፈው ሜዳ ላይ የቆሎ ዘርቶ ሲኖር፣ አንድ ቀን የጃንሆይ መልዕክተኞች ሲገሰግሱ ቤቱ ድረስ መጡና፣ “እዚህ በቆሎ የዘራህበት ቦታ ላይ የንባሲዮን ሊሰራሰት ነውና መድረሻህን ፈልግ ብለውሃል ጃንሆይ አሉት። “ኧረ ውሰዱት ደሞ ለሞላ ቦታ አላቸው። ትንሽ ቆይቶ፣ “ይሄ ግን 'የንምባሲዮን' ያላችሁት ነገር መንግስት ነው ?” ሲል ጠየቀ። “አይደለም !" “አሃ ተማሪ ቤት መሆን አለበት :" “አይደለም!” ታዲያ ምንደን ነው ቤተስክያን ይሆን እንዴ ?" ሲል ግር ብሎት ጠየቀ። "ኤማቢሲዎን ማለትንጉሥ የፈቀዱላቸው የውጭ አገር መኳንት እና መሳፍንት አገራቸውን መስለው የሚቀመጡበት እና አንዳንድ የመንግሥት ሥራዎችን የሚከውኑበት ማረፊያ ነው" አሉት ሳኔ ዕክተኞቹ አንዱ። ከመልክተኞቹ አንዱ። "በቃ ?" ሲል ጠየቀ አያቴ በግርምት። "በቃ!" "እኮ ፈረንጆች ይሄን ሁሉ ቦታ አጥረው ቁጭ ሊሉ ነው” አለ እንደገና በታላቅ ግርምት። "አዎ ! ይሄ የምባሲዮን ... የወከላቸው አገር የማይደፈር ግዛት ነው” እንዲያ ድንበራችን ላይ ያባረርነውን ጠላት መናገሻችን ላይ አርደንለት ጋርደንለት ልናስቀምጠው ነው በለኛ አለ አያቴ በቁጭት። መልዕከተኞቹ አያቴ ላይ ሳቁበት። ስለኤምባሲ ያለው እውቀት አነስተኛ መሆኑን በመገንዘባቸው ድፍን ሁለት ሰዓት ስለኤምባሲ ተግባርና ለአጎራችን ስላለው ጠቀሜታ በዝርዝር አወሩት። ተግባብተው ሊለያዩ ሲሉ ግን ነገር ተበላሽ።ጉድፈላ። አገር ተሸበረ።ድንገት ነው ነገሩ የተመሰቃቀለው ከሆነስ ሆነና የማን አገር ኤምባሲዮን ነው ?" ሲል ጠየቀ አያቴ፣ “ጥልያን” ብለው መለሱለት። "ጥልያን ጥሊያን ... እኮ ጥሊያን ይሄ ፋሽስት የነበረው" አለ አያቴ ማመን አቅቶት። "እንዴታ አሁን በሰላም መጥተዋል” አያቴ ሰይጣኑ ተነሳ። ተንደርድሮ ምንሽሩን መዥረጥ አደረገና ለግማሽ ሰዓት ያህል ፎክሮ ሲያበቃ፣ "ባንዳ ሁላ…” ብሎ የጃንሆይን መልዕክተኞች ማሳደድ ጀመረ ! ጥሎብን መከተል እንወዳለን። መንገድ ላይ ድንገት አያቴን ያዩ ሁሉ፡ ገና የአርበኝነት ስሜቱ ያልበረደላቸው፣ እንዲሁም አርበኝነት ያመለጣቸው፣ እንደገና እድሉን አገኘን በማለት ምንሽራቸውን አፈፍ እያደረጉ፣ “ያዘው…" እያሉ ላይጠቅማቸው አያቴን ተቀላቅለው የንጉሱን መልእክተኞች ማሳደድ ጀመሩ። መቼስ አዲሳባ እንደዛን ቀን ተፎክሮባትም፣ ተሸልሎባትም አያውቅም ሲሉ ሁኔታውን የታዘቡ፡፡ አያቴ ቁጣው መለስ ሲል ዞሮ ቢመሰከት ድፍን የአዲስ አበባ ወንድ ተከትሎታል። “ምን ሆናችሁ” ቢላቸው አያቴ፣ “አይ ሩጫው ወደ ቤተ መንግሥት መሆኑን ስንሰማ ነው የተከተልኛችሁ” አሉ !! አያቴ የተከታዩን ብዛት አየና በዛው ሸፈተ ! ስሙ የገነነ ሽፍታም ሆነ ! ስሙ ከተጠራ እንኳን ኢትዮጵያ ምድር ያሉት ሮም የተቀጡትም ጥልያኖች ወባ እንደያዘው እየተንዘፈዘፉ ንሰሃ ይገባሉ ! ጭራሽ የኤምባሲው ግንባታ ሲጀመር በወርም በሳምንትም በል ሲለው በየሦስት ቀኑ ብቅ እያለ ይሄን ጣልያን ሁሉ ይፈጀው ጀመረ !! ጃንሆይ በበኩላቸው አያቴን በዲፕሎማሲ ማሳመን መርጠው መልዕክት ላኩበት። በድፍረት ከነጎፈረ ጸገሩና ከነምንሽሩ ፊታቸው ቀርቦ፤ "ጃንሆይ ትላንት ይሄን ፋሽስት፣ እንኳን አሳረርከው' ብዬ የሸለሙኝን ቦታ ዛሬ ከኔ ነጥቀው ላባረርኩት ሰላቶ በመስጠትዎ ተቀይሜዎታለሁ !! እማምላክን ተቀይሜዎታለሁ። እንዴት እንዴት ነው ነገሩ ... እዚህች አገር አባራሪው ከተባራሪው ተደባለቀ እኮ ዳር ላይ ያባረርነው ከመሐል እያባረረን ተቸገር?" አለ። ጃንሆይ በጥሞና ሲያደምጡ ቆዩና፣ “ቅሬታህን ሰምተናል። ካንተ የሚበልጥብን የለም። ያው አንተ ዳር ላይ ልክ ያስገባሃቸው ናቸው ዛሬ ወዳጅነታችንን ፈልገው በእንብርክክ ደጅ የጠኑን እንደምታውቀው ጀግና በጠብ የመጡበትን አንጂ በፍቅር የመጣን አይነኩም አሉና የአያቴን ቁጣ አበረዷት። “በል አሁን በቃህ ለማን ብለህ ነው መሬትህን ጥለህ የምትሄደው፡፡ እነሱ እያዩህ ይሸማቀቁ እንጂ ብለው እዛው ኤምባሲው ጎን ለአያቴ ሰፊ ቦታ ሰጡት። እርቅ ወረደ! ንጉሡ ብልህ ነበሩ። አንዳንዴ አያቴን ይጠሩትና፣ ጎረቤቶችህ ሰላም ናቸው ? ብለው ይጠይቁታል። አያቴን ሰላይ አደረጉት እንግዲህ የአያቴ ጎጆ እና የጣሊያን ኤምባሲ በግንብ አጥር ብቻ ነበር የሚለያዩት። አያቴ ጣልያኖቹን ባያቸው ቁጥር ደሙ እየፈላ፣ "ወይ ነዶ የማንም ፋሽስት ጋር እንዲህ ትከሻ ለትካሻ እየተጋፋሁ ልኖር” እያለ በብስጭት ሲግል ሚስቱ ወይዘሮ በልጅጌ መኮንን (የፊታውራሪ መኮንን እጅጉ የመጀመሪያ ልጅ እያባበለች ወደ መኝታ ቤታቸው ትወስደውና ከብስጭቱ አብርዳ በሌላ ጉዳይ ትለኩሰዋለች ! አቤት ማባበል ስታውቅበት …. ገና ስትታይ ነገር ታበርዳለች ... እሳት ፈገግታዋ እሳት ያጠፋል ... ይች ውብና አስተዋይ ሴት ሲበሳጭ ስታባብለው፣ ሲበሳጭ ስታባብለው .… አምስት ሴትና አንድ ወንድ ልጅ ወለዱ። ይሄ ብቸኛ ወንድ ልጅ የእኔ አባት ነበር። አያቴ ምንም እንኳን የልጆቹን አእምሮ በምክር አርሶና አለስልሶ የጣሊያንን ጥላቻ ቢዘራበትም አልፀደቀም። በተለይ ሴት ልጆቹ ያማረ መኪና ይዘው የሚገቡና የሚወጡ የጣልያን ጎረምሶች ላይ ልባቸው አልጨክን እያለ፣ ዓይናቸውም እየተንከራተተ አስቸገረው። ጭራሽ ይለይልህ ብለው ከአባቴ በስተቀር ሁሉም ሶላቶ' አግብተው ቁጭ አሉ። በዚሁ ብስጭት ሙሉ ቦታውን ለአባቴ ብቻ አውርሶና ጥልያን ያገቡ ልጆቹን ሁሉ ክዶ ሚስኪን አያቴ በደም ግፊት ሞተ !! አባቴም፡ 'ሙሉ' የምትባል ውብ ሴት አግብቶ እዚሁ ነገረኛ የወርስ ቦታ ላይ ቤት ሰርቶ መኖር ጀመረ (ሙሉ እናቴ ናት…)። እናቴ ሙሉ መቼስ ወላ በቁንጅና፣ወላ ሰባሕሪ ቢባል ይሄ ቀረሽ የማትባል ውብ ናት። ስትገባ ስትመጣ ተመልካቹ በዛ፣ የሚመኛት እልፍ ነበር። አባቴ ታዲያ እናቴ ስትደነቅና ስትሞገስ ደስ ቢለውም፣ ከተመልካቹ ሁሉ ደሙን የሚያፈላው የጣልያኖቹ አስተያየት ነበረ። እንግዲህ ጣልያኖቹ እናቴ ስታልፍ ፊታቸው እንደ ቲማቲም ቀልቶ አፋቸውንም፣ ዓይናቸውንም በልጥጠው በአጥራቸው ላይ እየተንጠላጠሉ በአጉል ምኞት ሲመለከቷት አባቴ ይሰሳጫል፤ በላቸው በላቸው ይለዋል። (ደግሞ ለማለት፣ አያቴ እንደሆነ ምንሽሩን አውርሶታል- መታገስ ደግ ነው ብሎ እንጂ…)
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
“የምኒልክ ፈረስ በክንፎቹ ሔደ” ምኒልክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ ግብሩ እንቁላል ነበር ይኸን ጊዜ አበሻ፡፡ በሠራው ወጨፎ ባመጣው እርሳስ ተፈጠመ ጣልያን አበሻ እንዳይደርስ፡፡ ምኒልክ ተጉዞ የምትጠይቁኝ ፊትም አላለፈ ኋላም አይገኝ፡፡ መድፋን መትረየሱን ባድዋ መሬት ዘርቶ እንክርዳዱን ነቅሎ ስንዴውን ለይቶ የዘራውን እህል አጭዶና ወቅቶ ላንቶኔሊ አሳየው ፍሬውን አምርቶ፡፡ እንዳቀና ብሎ ለምኖ መሬት ንግድ ሊያሰፋበት ሊዘራ አትክልት እየመጣ ሊሰጥ ግብሩን ለመንግሥት ለጓዙ ማረፊያ አገር ቢሰጡት ተጠማኝ ሰንብቶ ሆኖ ባለርስት ወሰን እየገፋ ጥቂት በጥቂት እውነት እርስት ሆነው ተቀበረበት፡፡ ባሕር ዘሎ መምጣት ለማንም አትበጅ እንደ ተልባ ስፍር ትከዳለች እንጂ አትረጋምና ያለተወላጅ፡፡ የዳኛው አሽከሮች እየተባባሉ ብልት መቆራረጥ አንድነት ያውቃሉ #ዓድዋ ከከተማው ሥጋ ቆርጠው ጣሉ፡፡ የእስክንድር ፈረስ መቼ ተወለደ የምኒልክ ፈረስ በክንፎቹ ሔደ፡፡ ደንገላሳ ሲዘል እየተንጓደደ የሮማውን ኩራት በእግታ አሰገደ፡፡ አገርህን ምኒልክ እንዳሁን ፈትሻት እጁን ቀምሼ አላውቅም እያለ ሲያማህ ቀመሰና እጅህን መጥቶ ጠላትህ ሮም ላይ ተሰማ ለጋስ መሆንህ፡፡ አባተ በመድፋ አምሳውን ሲገድል ባልቻ በመትረየስ ነጥሎ ሲጥል የጐጃሙ ንጉሥ ግፋ በለው ሲል እቴጌ ጣይቱ እቴጌ ብርሃን ዳዊቷን ዘርግታ ስምዓኒ ስትል ተማራኪው ባዙቅ ውሃ ውሃ ሲል ዳኛው ስጠው አለ ሠላሳ በርሜል፡፡ እንደ በላዔ ሰብአ እንደመቤታችን ሲቻለው ይምራል የኛማ ጌታችን፡፡ 🔘ተክለ ጻድቅ መኩሪያ🔘
Показати все...
Repost from MK technology
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ፈታ በሉልን ይሄ ነገር በጣም ያጋጥማል 😂😂😂😂😂😂 @MKtech19
Показати все...
ማጣቀሻ 😁 ❤️❤️❤️ሜተራሊዮን❤️❤️❤️ ደራሲ- ዓለማየሁ ዋሴ ...........ወዲያው ወደ አፋፉ ሩጥ ሩጥ የሚለኝ መጣ።''እንዴት ያለ በሽታ ነው?"አልኩ ለራሴ ችኮላዬ ታውቆኝ በአግባቡ አመሰገንኳቸውና በዚች ውሃ ጠጡ ብዬ ትንሽ ብሮች እጃቸው ላይ አድርጌ ወደ ነቢል እየተጣደፍኩ ስሄድ እስራኤል ኒታንያ ከተማ ከኢትዮጵያውያን አይሑድ መንፈሳዊ መሪ ከአባ ዮናታን ጋር ያደረኩት ውይይትና ምሪት በአዕምሮዬ እየተመላለሰ ነበር። @MKtech19 @MKtech19 🌸#Share🌸
Показати все...
Join👆👆👆👆👆👆👆👆
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.