cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ዳጉ አዲስ

ከአገር ዉስጥ እና ከውጪ ወቅታዊ መረጃዎችን የሚያገኙበት ገፅ:: እዚ ቻናል ላይ ✍ የጥበብ ዜናዎች ✍ አዝናኝ እውነታዎች ✍ ትኩስ ትኩስ መረጃዎች በቀን በቀን አለም የምታስተናግደውን ክስተት ይከታተሉ፡፡ ❀ #ዳጉ_አንዳዴ የእርሶ ተቀዳሚ ምርጫ♥♥♥ @Dagu Admins @Yofnan @PPOGBA6 @ዳጉ

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
1 289
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Фото недоступнеДивитись в Telegram
በ2 መቶ ሺህ ብር በመቀበል ሰነድ አልባ የሆነን መኖሪያ ቤት ህጋዊ ካርታ ለመስጠት ሲል የተያዘው ኃላፊ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 የቤቶች ሀላፊ የሆነ አመራር አገልግሎትን በገንዘብ ለመሸጥ 2 መቶ ሺህ ብር ሲቀበል እጅ ከፍንጅ መያዙን ፖሊስ አስታውቋል። ሰነድ አልባ የሆነን መኖሪያ ቤት ህጋዊ ካርታ ሰጥሻለሁ በሚል የማጭበርበር ቃል ከአንዲት ግለሰብ አትላስ አካባቢ ከአንድ ግለሰብ ሱቅ በር ላይ ገንዘቡን ሲቀበል እጅ ከፍንጅ ተይዞ ጉዳዩ እየተጣራ ነው ተብሏል። በክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የወንጀልና የትራፊክ አደጋ ምርመራ ዘርፍ ሀላፊ የሆነት ዋና ኢንስፔክተር ባህሩ ተክሌከ ጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ሌሎች ግለሰቦችን በማጣራት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። bbc_amharic @Daguadise
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
" የእኔ እናትና አባት ሲደሰቱ ብሰማና ባያቸው ደስ ይለኝ ነበር " ለሀገራችን ሶስተኛውን ወርቅ በማራቶን ያስገኘችው ጎይትቶም ገ/ስላሴ ከድሉ በኋላ አስተያየቷን ሰጥታለች ። " ደስ ብሎኛል ደስታዬ ግን የተዘበራረቀ ነው ፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደተደሰተው የእኔ እናት እና አባትም ሲደሰቱ ብሰማና ባያቸው ደስ ይለኝ ነበር ። እግዚአብሔር ሰላሙን ያምጣ ደስታው ትልቅ ነው ፣ ግን ደግሞ ትንሽ ተዘበራረቀብኝ አምና በዚህ ጊዜ የት እንደነበርኩ አውቃለሁ መንገድ ተከፍቶ ነው የወጣሁት ። በመጀመርያ እግዚአብሔር ነው የረዳኝ ፣ ከዚያም በማሰልጠን ብቻ ሳይሆን እንደ ወንድም ሆነው እንዳይከፋኝ እያገዙ ለዚህ ያበቁኝ አሰልጣኞቼ ናቸው አይዞሽ ሁሉም ያልፋል እያሉ እዚህ አደረሱኝ ። አመሰግናቸዋለሁ! ምንጭ :- አብይ ወንዲፍራው @Daguadise
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
#Update #ኢትዮጵያ🇪🇹 የሴቶች ማራቶን ውድድር ቀጥሏል። ቅድም በፊት መስመር ስምንት የነበሩት አትሌቶች አሁን 3 ቀርተዋል። ከሶስቱ ሁለቱ የሀገራችን 🇪🇹 ልጆች ናቸው። 🇪🇹 ጎይቶቶም ገ/ስላሴ 🇪🇹 አባብል የሻነ አንዷ የኬንያ አትሌት ናት። Addis_Mereja @Daguadise
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
Enter a caption here!
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ኢራን ኒውክለር ቦንብ ለመስራት የሚያስፈልጋት ነገር ቢኖር የፖለቲከኞቿ ውሳኔ ብቻ ነው ሲሉ ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡ በቴክኒክ እና በሌሎች የዘርፉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎቿን አጠናቀዋል ያሉት እነኚህ ባለሙያዎች፣ የኒውክለር ቦንቡን ለማምረት የፖለቲከኞች ውሳኔ ብቻ እየተጠበቀ እንደሚገኝም አመላክተዋል፡፡ ከማል ካራዚ የተባሉት የሃገሪቱ ከፍተኛ የደህንነት አማካሪ ሃገሪቱ በጥቂት ቀናት ዩራኒየም የማበልፀግ አቅሟ ወደ 60 ከመቶ መድረስ መቻሉን አስታዉሰዋል፡፡ በቀጣይም 90 ከመቶ ለማድረስ ከፍተኛ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡ የባይደንን ጉብኝት ተከትሎ ይህንን አስተያየት የሰጡት ከማል ካራዚ፣ ኢራን ሃገራቸው የፖለቲከኞቿ ውሳኔን ማጣቷ እንጂ ኒውክለርን ለመታጠቅ እሩቅ ሆና አይደለም ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ከሰሞኑ አሜሪካ እና እስራኤል በሃይልም ቢሆን የኢራንን የማብላያ አቅም ለመስበር እያቀዱ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ Addis_Mereja @Daguadise
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በሱዳን በጎሳ ግጭት የተነሳ የሟቾች ቁጥር 70 ደረሰ‼️ በሱዳን ብሉ ናይል ግዛት ለቀናት በዘለቀው የጎሳ ግጭት የሞቱት ሰዎች ቁጥር ቢያንስ 65 መድረሱን የግዛቱ የጤና ኃላፊ አስታዉቀዋል። በደቡባዊ የሀገሪቱ ክፍል በሃውሳ እና በቢርታ ብሄረሰቦች መካከል በነበረው ግጭት ከተግደሉት ሰዎች በተጨማሪ 150 የሚጠጉ ሰዎች መቁሰላቸውን ገማል ናስር አል ሰይድ በትላንትናዉ እለት ተናግረዋል። ከሟቾቹ መካከል አብዛኞቹ በጥይት የተመቱ እና በስለት የተወጉ ወጣቶች እንዳሉበት ተነግሯል፡፡በብሉ ናይል የሚገኙ ሆስፒታሎች የተራቀቁ መሳሪያዎች እና የህይወት አድን መድኃኒት እጥረት ስላለባቸዉ በዋና ከተማዋ ካርቱም የሚገኙ ባለስልጣናት 15 ክፉኛ የተጎዱ ሰዎችን በአየር መጓጓዣ በማንሳት እንዲረዷቸው አል ሰይድ አሳስበዋል። ቅዳሜ ዕለት ባለሥልጣናቱ የሟቾች ቁጥር ቢያንስ 31 መሆኑን ተናግረዋል ።በአካባቢው መረጋጋት ለማምጣት ባለስልጣናት ወታደራዊ ፈጣን ድጋፍ ሰጭ ሃይሎችን አሰማርተዋል። እንዲሁም ግጭቱ በተከሰተባቸው የግዛቱ ዋና ከተማ ሮዝሬስ እና አል-ዳማዚን ከተሞች ከቅዳሜ ምሽት ጀምሮ የሰዓት እላፊ ገደብ ተጥሏል፡፡ የብሉ ናይል ገዥ አህመድ አል ኦምዳ ለአንድ ወር ማንኛውንም ስብሰባ ወይም ሰልፍ የሚከለክል ትእዛዝ አስተላልፈዋል። bbc_amharic @Daguadise
Показати все...
Yegnawochu
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
" ቡድናችን በአንድነት እና በፍቅር መንፈስ ላይ ይገኛል " ደራርቱ ቱሉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮ/ር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ከጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ጋር ባደረገችው ቆይታ አስደሳች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልፃለች ። "ልጆቻችን አስደሳች ውጤት እያስመዘገቡ ነው፣ ልፋታቸው ላይ እግዚአብሔር ተጨምሮበት ውጤት እያገኘን ነው። ቡድናችን በአንድነት እና በፍቅር መንፈስ ላይ ይገኛል ፣ ስፖርት ምን አይነት ሀይል እንዳለው እያየን ነው። ዛሬ ምሽት የ10 ሺህ የወንዶች ውድድርም አለ ፣ ተመሳሳይ ውጤት እንጠብቃለን ። ቡድኑ ከምንግዜውም በላይ በመደጋገፍ እና በመተባበር ስሜት ላይ ነው ። ባንዲራችንን ከፍ ማድረግ ችለዋል ፣ ጥሩ መንፈስ ሲኖር ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ ነው " በማለት ከጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ጋር በተደረገ የስልክ ቆይታ ተናግራለች ። ምንጭ :- ኤልያስ መሰረት tikvahethsport @Daguadise
Показати все...
ከአገር ዉስጥ እና ከውጪ ወቅታዊ መረጃዎችን የሚያገኙበት ገፅ:: እዚ ቻናል ላይ ✍ የጥበብ ዜናዎች ✍ አዝናኝ እውነታዎች ✍ ትኩስ ትኩስ መረጃዎች በቀን በቀን አለም የምታስተናግደውን ክስተት ይከታተሉ፡፡ ❀ #ዳጉ_አንዳዴ የእርሶ ተቀዳሚ ምርጫ♥♥♥ @Daguadise Admins @Yofnan @PPOGBA6 @ዳጉ
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ኢትዮጵያ ከአለም ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች ! በኦሪጎን እየተካሄደ በሚገኘው የአለም ሻምፒዮና ሀገራችን ኢትዮጵያ #ሶስት ሜዳሊያዎችን መሰብሰብ ችላለች ። ኢትዮጵያ በሁለት ወርቅ እና አንድ ብር በአለም ሻምፒዮናው #ከአለም ሁለተኛ እንዲሁም ከአፍሪካ ቀዳሚውን ደረጃ ይዛለች ። tikvahethsport @Daguadise
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.