uk
Feedback
አንጾኪያ ሚድያ

አንጾኪያ ሚድያ

Відкрити в Telegram
1 421
Підписники
Немає даних24 години
-87 днів
-1830 день
Архів дописів
ህይወት አዙሪት ናት።ረጅም ርቀት የተጓዝክ ቢመስልህ የምትጨርሰው ከጀመርክበት ነው።ራቁትክን ትወለዳለህ እርቃንህን ወደ መቃብር ትወርዳለህ።በጥርስ ዐልባው ድድህ እየጋጥክ ትጀምራለህ ጥርሱን ባረገፈው
ህይወት አዙሪት ናት።ረጅም ርቀት የተጓዝክ ቢመስልህ የምትጨርሰው ከጀመርክበት ነው።ራቁትክን ትወለዳለህ እርቃንህን ወደ መቃብር ትወርዳለህ።በጥርስ ዐልባው ድድህ እየጋጥክ ትጀምራለህ ጥርሱን ባረገፈው ድድህ እያልጎጠጎጥክ ትጨርሳለህ።የህይወት ትግል እየዳህ ትጀምራለህ አጎንብሰህ ትጨርሳለህ።ዘመንም ተምኔታዊ ነው።መስከረም ጥቅምት ብሎ ያስጀምርህና መስከረም ብሎ ይመጣብሀል።ሰኞ ማክሰኞ ብለህ ተጉዘህ እንደገና ሰኞ ትላለህ።ሕይወት አዙሪት ናት!መጀመሪያህ መጨረሻህ ነው።የጀመርክበትን አትርሳ መጨረሻህ ነውና።የጀመርክበትን አትናቀው ትጨርስበታለህና።ተራ ሰው ሆነህ ትጀምራለህ ተምረህ እውቀት ብትጨምር ነግደህ ሀብት ብታገኝ ተሹመህ በህዝብ ላይ ብትሰለጥን ክቡረ ክቡራን ሆነህ የወርቅ ካባ ብትለብስ የምትጨርሰው እንደ ተራ ሰው አፈር ለብሰህ ነው። ባለማወቅ ትጀምራለህ በመዘንጋት ትጨርሳለህ ዕውቀት አላመጣህምና ዕውቀትም ይዘህ አትሄድም።በለቅሶ ትጀምራለህ በጭንቅ ትጨርሳለህ።በሰው እቅፍ ትጀምራለህ በሰው ሸክም ትጨርሳለህ። ገፅ 314_315 ከመርበብት በዶ/ር አለማየሁ ዋሴ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! “አሐቲ ድንግል” በፈውስ መንፈሳዊ የዩቲዩብ ቻናል የህይወትን ቃል በሚመግቡን በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ ተጽፎ በ628 ገጾችና በ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! “አሐቲ ድንግል” በፈውስ መንፈሳዊ የዩቲዩብ ቻናል የህይወትን ቃል በሚመግቡን በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ ተጽፎ በ628 ገጾችና በ12 ምዕራፎች የተሰነደ መጽሐፍ ነው፡፡ ከኅሊና አምላክ እስከ ዕርገቷ ድረስ ያለውን የእመቤታችንን ሙሉ የሕይወት ጉዞና በርካታ ምሥጢራት የያዘ ድንቅ መጽሐፍ ነው፡፡ እመቤታችን በነገረ ድኅነት ያላት ድርሻ ምን ይመስላል? ስለ እመቤታችን የሚነሡ ጥያቄዎች በመጽሐፍ ቅዱሳዊ የአበው ትምህርት እንዴት ተዳሰሰ? እንዴትስ በፍቅሯ ማደግና መጽናት ይቻላል? ሌሎችም መልሶችን የያዘው ይህ ግዙፍ መጽሐፍ አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ጨምሮ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በተገኙበት የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 2/2017 ዓ.ም ከቀኑ 7 ሰዓት ተኩል ጀምሮ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አዳራሽ ይመረቃል፡፡  ሁላችሁም እንድትገኙ በአክብሮት ተጠርታችኋል።

-ሲኖሩ በሰማዕትነት ሲሞቱ በታሪካዊነት፦ በምድር ላይ መኖር የምንችለው ባአጭር ዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው። ከሞት በኋላ ሁለተኛ ለብዙ ዘመናት መኖር የምንችለው ግን በመልካም ታሪካችን ነው። ታሪክ የሠራ ሰው ዳግም በታሪክ ህልውና ውስጥ ሕያው ሁኖ ሲወሳ መኖር ይችላል። ህያው አድራጊ ታሪክ ደግሞ ዝም ብሎ በስንፍና አይሠራም። ራስን ሰጥቶ ሞትን ንቆ አጥቅቶ ነገን አልሞ በመሥራት ነው እንጂ። ይልቁንም ትንሣኤ ሙታን ያለው ሰው ሁልጋዜም ታሪካዊ ሕያውነትን በህሊናው ማየት ግድ ይለዋል። ስለሆነም ከሞት በኋላ በታሪክ ህልውና ውስጥ ለመኖር ምን እየሠራን ነው? ወይስ አሁናዊ ብቻ ሁነን ለመቅረት ነው የምንፈልገው? ክፉ ሰው ርኩስ መንፈስን አምኖ ምእመናንን ለማጥፋት ለክፉ ታሪክ ከተነሣ እኛ መንፈስ ቅዱስን አምነን ትናንትን ለትውልድ ለማስረከብ የነገ መልካም ታሪክን ለማንበር መነሣሣት ግድ ይለናል። ምክንያቱም ዛሬ ባለችን በዓላማ በቁርጠኝነት ራሳችንን ሰጥተን ካልሠራን ለነገ ትውልድ ታሪክም ሃይማኖትም አይኖረንም። በታሪክ ህልውና ውስጥ እንዳናይ የሚያደርገን ገርጋሪያችን ፍርሀት እና አስመሳይነት ነው። ፈሪ ሰው ደግሞ የክርስቶስ መስቀሉን መሸከም አይችልም። መስቀልን ያልተሸከመ ሰው ደግሞ መከራ አይንካኝ ሆዴ ይሙላ ደረቴ ይቅላ ሲል የሰማዕትነት ክብር ታመልጠዋለች። ሲኖሩ በሰማዕትነት ሲሞቱ በታሪካዊነት ለመገለጽ ካሰቡ ፍርሀትን እና አድርባይነትን እንደ ሸረሪት ድር ገፎ መጣል ግድ ይላል። መስሎ መኖር እና አድርባይነት ለስለላሳ ኑፋቄ ነው። በምድር ላይ ማን ይፈራል? ሞትን እንዳንፈራው? ትንሣኤ ሙታን አለን። አግባብስ ያለታሪክ ያለ ሃይማኖት እንዳይቀር የነገውን ትውልድ መፍራት ነው። ለነገ አለማሰብ የነገውን ትውልድ በግልጽ መበደል ነውና። ትናንትን እንደሚገባ ከአባቶቻችን እንደተቀበልነ ዛሬም በሰማዕትነት የተቀበልነውን አደራ እየጠበቅነ ለነገው ትውልድ የማስረከብ ሀላፊነት አለብን። የነገ ታሪክ ሰነፎች ተቀምጠው ሳሉ እንደ ፈጣን ወፍ ማረፊያ አጥቶ በጊዜ ነፋስ ላይ በርሮ መሄዱ አይቀርም። መሥራት ባይቻል እንኳን ለሚሠሩ ሰዎች እንቅፋት ላለመሆን መጣር ተገቢ ነው። ከህሊናም ከታሪክም ጋራ መጣላት ትልቅ ድክመት ነው። መሆን ያለብንን ሳንሆን መሆን ያለበት አይሆንም። #መምህር ገብረ መድኅን እንየው

photo content

እግዚአብሔር ሁልጊዜ ወደ መከራ እንዳትገባ አያደርግም። አንዳንድ ጊዜ በወጀብ ውስጥ መንገድ ያዘጋጅልሃል። ግፊው በሚበዛበት ዐውሎ ነፋስ እያለፍህ ተፍገምግመህ እንዳትወድቅ ጉልበትህን ያጸናል፤ ኃይልን
እግዚአብሔር ሁልጊዜ ወደ መከራ እንዳትገባ አያደርግም። አንዳንድ ጊዜ በወጀብ ውስጥ መንገድ ያዘጋጅልሃል። ግፊው በሚበዛበት ዐውሎ ነፋስ እያለፍህ ተፍገምግመህ እንዳትወድቅ ጉልበትህን ያጸናል፤ ኃይልን ያስታጥቅሃል። እንዲህ እያደረገ በመንፈስ ያጎለምስሃል። እግዚአብሔር ዳንኤልን በአናባስት ጉድጓድ ከመጣል፣ ሠለስቱ ደቂቅን ወደ እቶን እሳት ከመግባት፣ ጳውሎስና ሲላስን ወደ ወኅኒ ከመውረድ ሊያድናቸው ይችል ነበር። ይሁን እንጂ እንዲህ አላደረገም። አምላካችን ፈተና ካለባቸው ቦታዎች ሁሉ ሊያወጣን ቃል አልገባምና። ነገር ግን በመከራ ጊዜያችን ሁሉ ከእኛ እንደማይለይና በእውነት ይዘነውም እንደ ሆነ በድል ነሺነት እናጠናቅቅ ዘንድ እንደሚረዳን ቃሉን ሰጥቶናል። የጌታ እናት እመቤታችን የተወደደ ልጇን ይዛ በግብጽ በረሃ እንደ ወፍ ከተንከራተተች በኋላ ሕፃኑን የሚፈልገው ክፉ ሄሮድስ ሲሞት ተመልሳ ወደ ገሊላ ገብታለች። እንደ ድንግል ጌታን በመሐል እጅህ ብትታቀፍ እንኳን  ግብጽ መውረድ  አይቀርልህም። ይሁን እንጂ የመጣብህን መከራ ድል ነሥተህ ወደ ገሊላ መመለስህም እርግጥ ነው። "ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል"                               1ኛ ቆሮ 10፥13 ዲያቆን አቤል ካሳሁን

ድንግል ማርያም በድንጋይ ላይ ትገለጥልኝ ነበር እጅግ ግሩም ቆይታ #ከሰአሊ ቅዱስ ጋር ዛሬ ምሽት 12:00 ላይ በአንጾኪያ ሚድያ ይጠብቁ #አንጾኪያ ሚዲያ ሼር ሰብስክራይብ በማድረግ አገልግሎቱን ተደ
ድንግል ማርያም በድንጋይ ላይ ትገለጥልኝ ነበር እጅግ ግሩም ቆይታ #ከሰአሊ ቅዱስ ጋር ዛሬ ምሽት 12:00 ላይ በአንጾኪያ ሚድያ ይጠብቁ #አንጾኪያ ሚዲያ ሼር ሰብስክራይብ በማድረግ አገልግሎቱን ተደራሽ እናድርግ። ወደ ቴሌግራም ግሩፓችን ሰዎችን አድ እናድርግ. https://t.me/antsokia77 https://youtube.com/@antiochmedia77?si=2VhwMdVZIA3ib1X3