Chabod Youth & Family counseling service/cyc/
Christian counseling service 👨👨👧👦 በዚህ ግሩፕ👪 🏃♀🏃👭👬🚶♀🚶 አላማ 👉 ተተኪውን ትውልድ ከምንጩ ለመድረስ 🗣🗣የምናስተጋባው እውነት👀👀 🤙🤙🤙 👆 ለቀና ትውልድ መሰረት መልካም ቤተሰብ ነው። 💐💐ተሳታፊ አካል 💐💐 👍በአንድም በሌላም በቀጣይ ትውልድ ላይ የሚሰሩ እና ስለ ትውልዱ ልብ ያላቸው ሰ
БільшеКраїна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
189
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
- Підписники
- Перегляди допису
- ER - коефіцієнт залучення
Триває завантаження даних...
Приріст підписників
Триває завантаження даних...
አራቱ የወላጅ አይነቶች
አራቱ የወላጅ አይነቶች እና በልጆች አስተዳደግ ላይ ያላቸው ተጽህኖ
- የልጆች የአስተዳደግ ሁኔታ በልጆች ሁለንተናዊ እድገት ላይ የሚያመጣው ተጽህኖ በጣም ከፍ ያለ ነው።
ሁለንተናዊ ማንነት ስንል
- አካላዊ ስነ ልቦናዊ ውቅር እና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ የሚያመጣው ተጽህኖ ከፍ ያለ ነው።
ስለዚህ ወላጆች ምን አይነት ያስተዳደግ ሁኔታ እንደሚከተሉ እራሳቸውን መመዘን አለባቸው።
በተጨማሪም ሆን ብለው ምን አይነት ያስተዳደግ ሁኔታ መከተል እንዳለባቸው ሊመርጡ ይገባል።
እንዲህ ማድረጋቸው ለጤነኛ ልጆችን ለማሳደግ ለአካባቢ ለቤተ- ክርስቲያን ብሎም ለአገር ትልቅ ውለታ እየዋሉ እንደሆነ ማስተዋል ይኖርባቸዋል።
💐በዛሬ ትውልድ ማንነት ላይ የነገን አገር እንደ መስታወት ማየት ይቻላል።💐
የተለያዩ ጥናቶች እንደሚያሳዩት አራት አይነት የወላጅ አይነቶች አሉ።
- Authoritarian/ ፈላጭ ቆራጭ
- Authoritative / ልጆችን የሚያምኑ
/ በልጆቻቸው እምነት የሚጥሉ/
- permissive / ለልጆቻቸው ከመጠን ባለፈ ሁኔታ ነጻ የሚያደርጉ/ እሺ ባዮች/
- Uninvolved / ለልጆቻቸው ትኩረትን ፈጽመው የሚነፍጉ/ ዞር ብለው የማያዩ/
ከላይ የተጠቀሱ የአስተዳደግ አይነቶች የራሳቸው የሆነ ልዩ ልዩ መገለጫዎች አሉት።
ይቀጥላል👉👉👉
ባለ አደራ
በወቅቱ ሊጠቀም ምርጥን ዘር ሊዘራ
ጎበዙ ገበሬ ወጣ ይዞ አዝመራ
እሸት ሆኖ በቅሎ ብዙ እንዲያፈራ
ማለዳ ጀመረ ስራዉን ይከዉን
ዘሩን ዘርቶ ሄደ ጠብቆ ጊዜዉን
ግና ምን ያደርጋል ሽር ጉድ ማለት
ግማሽ ስራ መስራት መና የቀረ ልፋት
አንዴ ዘሩን ዘርቶ በተስፋ መጠበቅ
ከናረሙ ትቶ መልካም ዘር መናፈቅ
እንደ ህልም እንጀራ ሳያገኙት ሲቀር
መሬቱን መርገም ፍሬዉን ማማረር
ትዉልድም እንዲሁ ከናረሙ በቅሎ
እሣቱን ስንጠብቅ አገኘነዉ ከስሎ
ልጄ ከየት ዋለ ከማን ተገናኘ?
በምን ፋንታ ምን ጥሎ ደሞስ ምን አገኘ
ሳይለዉ ላንዳፍታ ዞር ብሎ ሳያየዉ አሳደኩኝ ይላል ጉዱን ያላወቀው
እሱኑ ለማኖር እሱኑ እየረሳ
ትዉልድ ወደቀ ፈርሶ እንደኩይሳ
ወጣት መረን ወቶ ልቅነቱ ሲታይ
ማነዉ ባላደራ ተጠያቂ ነኝ ባይ
ልጃ ላይ ተኝታ እንደገደለችዉ ሴት
ጠዋት ላይ ተነስቶ ልጄ ልጄ ማለት
ማስመሰል ይመስላል አይደለም የእዉነት
ከምር ከወደደው ግድ ካለዉ እሱ
ወደ ልቡ ቀርቦ ቢያደምጠው ከነፍሱ
አለ የሚላችሁ አለ ዉስጡ ጩኸት ቀርቦ ለጠየቀዉ ላዋየዉ ሚከፈት
ስሚኝ እናት አለም
ስትመክሪ በጥበብ አፍሽን ስትከፍቺ
ዉስጡን እንዲያዋይሽ በፍቅር እንድትረቺ
አባ እንዲሰበር ሳይሆን ህይወቱ እንዲነበብ
ምራዉ በትዕግስት በሔደበት መንገድ።
mihret tesfu.
--------------------
መጽሐፈ ምሳሌ 226፤
ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥
በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም። ይል አይደል ቅዱሱ መፀሐፍ አንዱና ትልቁ የወላጅነት ጅማሬ ነው::
--------------------
አንዳንዴ ወላጆች የሚጠበቅባቸውን ሁሉ አድርገው ምናልባት የልጆች ባህሪ ጥሩ የማይሆንባቸው ጊዜያት አሉ።
ይህ ማለት የልጆችን ባህሪ ለመቅረጽ ትልቁ ማና ያለው ወላጅ ሆኖ ሳለ ወላጅ ብቻ ነው ማለት አንችልም።
ሌሎች ተጽህኖዎች አሉ። እነርሱም የአካባቢ ተጽህኖ ውሎ,የትምህርት ቤት እንደ አስተማሪ ወይም ተማሪ, የጉዋደኛ ተጽህኖ የመሳሰሉት,,,
በድጋሚ ማስታወስ የምፈልገው ነገር የወላጅ ተጽህኖ ከሁሉ የላቀ እንደሆነ ነው።
ያልዘራነውን አናጭድም።ምንም አንኩዋን አንድንዴ በማይታወቅ ምክኒያት ልጆች ሊበላሹ ቢችሉም አብዛኛውን ግዜ ልጆች ወላጆችውቸውን ይመስላሉ። ይህ ግን በጣም ጥሩ ወላጆች ሆነው ባጋጣሚ ልጆች የሚበላሹባቸውን ወላጆች አይመለከትም። ልጆችን አላፈናፍንም ብሎ ማሳደጉም የጥሩ ወላጅነት ማሳያ ላይሆን ይችላል።ወላጆቹ አላማቸው ግልጽ ቢሆንም የሚከተሉት የማሳደግ መንገድ ግን ውጤቱ አሳዛኝ ነው። ልጆች እራሳቸውን በሚችሉበት ወቅት መጀመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር የተከለከሉትን ሁሉ ማሳደድ ነው። ስለዚህ ቁጥጥሩንም ሆነ ነጻነቱን በልክ ማድረግ ወሳኝ ነው ብዪ አምናለሁ።
❝ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ ወላጆች የሌላቸውን ልጆች ባልቴቶችንም በመከራቸው መጠየቅ፥ በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ ነው።❞ ያዕቆብ 1: 27