ፈለገ ጥበባት +++
Відкрити в Telegram
+++የቀደምት ኢትዮጵያውያን ስልጣኔን ማሳየት እንዲሁም ገዳማት እና አድባራትን ማሳወቅ፡፡+++ የተረሱ አድባራትና ገዳማትን ማስታወስ ፤የ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ጥበብ እውቀትን በምንችለው ሁሉ መመርመር የአባቶቻችን ልጆች በመሆን ትላንት በዛሬ እና በነገ ውስጥ ማስቀጠል ማስቻል ነው።
Показати більше7 163
Підписники
-524 години
-267 днів
-7330 днів
Архів дописів
7 163
ጂ የጎጆ ቤት ነው። ጭል ያሉ የመነኮሳት ጎጆወችን እያለፍን ቁልቁል እንወርዳለን። ራቅ ራቅ ብሎ ከሚታዩት የ ኩራዝ መብራቶች እና ከወዲያ ማዶ ነፋስ ይዞት ከሚመጣ የእንጉርጉሮ መሰል ዜማ ውጭ ጭር ያለ ባለ እርጥበት ያዘለ ሞገድኛ ነፋስ ያየለበት ስፋራ ነበር።
ከ ዋርካው ስር በዘፈቀደ የተቀለሱ አምስት ባዕቶች አንዱ የአባ ገ/ሂወት ነበርና ወደ ባእታቸው ገባን ከ መቅረዙ ላይ ያለውን ኩራዝ በማንሳት ላንባ ጨምረው ለኩሰው መልሰው አስቀመጡት። ያለ ወጋግራ የቆመች ጎጇቸው በቀይ አፈር የተለቀለቀች በግራና በቀኝ በከል መደብ የተሰራባት በርካታ መጻህፍትና ከ ቅል የተሰራ ገንበራ(መጠጫ) እና በአክርማና ሰብዝ የተሰፋ የምግብ መመገቢያ የያዘች አነስተኛ ቤት ነበረች።
የ በግ ለምድ ከ መደቡ ላይ ዘርግተው እንደቀመጥ ጋበዙኝና በገንበራዎ ውሃ አዘግጂተው እኒያ አረጋዊ እግሬን ሊያጥቡ ተጎነበሱ። የገዳሙ ስርአት ቢሆን እንኳ ይህንን ፈጽሜ እሽ እንደማልላቸው በግድ አሳምኘ የገዳሙ ምግብ መኮሬታ በበርበሬ እንድባላ ሰጠው ወደ ጸሎታቸው ተመለሱ።
ከተዘጋጀልኝ ምኝታ በ ሳሩ በኩል የሚንጠባጠበው ዝናብ ከለበሱኩት የብርድ ልብስ ውስጥ ሰርጎ በመግባት አባነነኝ። ድቅድቅ ጨለማ ገርበብ ብሎ ከተከፈተው የ ጎጆዋ በር ጀርባ ሲታየኝ...። በሩን ሳይዘጉ ረስተውታል በማለት በለሁሳስ አባ አባ ብየ ብጣራ ምላሽ ግን የለም...ኩራዙን ለኩሰው ያስቀመጡትን ክብሪት በደበሳ አስሸ ኩራዙን ሳበራ አባ ከ ምኝታቸው የሉም....
ከሌሊቱ ግርማ ይልቅ እንደ ሙዜር የሚያፏጨው ነፋስና ምድርን የሚያናውጣት ነጎድጓድ በደሳሳዋ ጣሪያ የሚፈሰው ዝናብ በጎጆዋ ሽንቅር በኩል የሚያልፈው የመብርቅ ብልጭታ እለተ ምጻት የቀረበ እስኪ መስል ድርስ መድረሻ አሳጣኝ።
ከተኛሁበት ራስጌ በኩል በለሰለሰ አራት ምአዘን ወፍራም ብራና የተቀመጠች የወይን ፍሬ ተመለከትኩ ከ መተኛቴ በፊት ቢሆን አስተውል ነበር ግን ከባ ገ/ሂወት ለሆነ ጉዳይ በአጋጣሚ ያስቀመጣት መሰለችኝ።
ዶፍ ዝናብ የሚወርድባት፤ ወዥንብር የሚያወዛውዛት ጎጆ እንደ ቅቤ አንጋች ወደ ግራና ቀኝ ይንጧታል።
ከአንደበቴ የማትጠፋው ከብዙ መከራ የታደገችኝን ጸሎተ ማርያምን እንየጸለይኩ የ አባ ገ/ሂወትን መምጣት እጠባበቃለሁ።
ብዙ ጊዜ መነኮሳት ቀን ሲሰሩ ውለው ሰፋ ያለ ጸሎት የሚያደርሱት ለሊት ነው ይህ በተደጋጋሚ ስለገጠመኝ አውቀዋለሁ ስለዚህ ባዕታቸውን ስለያዝኩባቸው ቤተክርስትያን ለጸሎት ሂወደው እንደሆን ጠረጠርኩ በዚህ ዶፍ ዝናብ እንዴት ሁኖ የሚለው ሌላ ሃሳብ ሆነኝ..።
የነፋሱ አነፋፈስ ከሚያሰማው ድምጽ አንጻር የነፋሳቱ መነሻ መስኮት እንብርት ላይ ያለሁ እስኪመስለኝ ድረስ አጠራጠረኝ ስለ ገዳሙ ለማወቅ ያለኝን ጉጉት ይበልጥ ጨምሮልኛል።
በጎጆዋ ጭንቁር በኩል የሚነፍሰው ነፋስ በደሳሳዋ ጎጆ እያፈተለከ የለኮስኳትን ኩራዝ በተደጋጋሚ ያጠፋዋል። በዛ ላይ ኩራዟ ላንብ አንሷት እርግብ እርግብ ትላለች።
ወደ ዚህ ገዳም የሄድኩበት ምክኒያት ከሚከበረውን አመታዊ ክብር ባዕል ባሻገር የማስስውና የምፈልገውን እውነትና እውቀትን ከቦታው ካሉ መነኮሳት ለመካፈል ነው።
ቢሆንም እንዳሰብኩት ሳይሆን በሚያስፈራው ለሊት የመነኩሴው ድንገት መሰወር አይሎ የመጣሁበትን ከማሳካት ይልቅ ነግቶ ማየትን ተመኘሁ።
የእኒያ መነኩሴ በድንገት መሰወር ብዙ ሃሳብና ጭንቀት ውስጥ ጣለኝ ስሰማው ያደኩት ሰው መሰል የጂንና የቆሌ ታርኮች እውን የሆኑም መሰለኝ።
በሂወቴ ካሳለፍኳቸው ፈታኝ ለሊቶች ይህ የማይረሳ ዋናው የሂወት ገጠመኘ ነው።
ሰማዩ ወጋገን እየለበሰ ዝናቡም ቀለል ያለ ካፊያ እየሆነ ከ ዚያ ሁሉ ጭንቀት ምድሪቱ ተገላግላ የፀሐይዋን መውጣት ትጠብቃለች።
የጨለማው በርኖስ ተገፎ በደመና የተሸፍነ የብርሃን ወጋገን ቦታውን ሲይዝ እፎይ አልኩ።
አሁንም መነኩሴው አባ ገ/ሂወት አልተመለሱም....
በማለዳ ተነስቸ ምድሩ በሳር በተሞላው ጤዛማ ሜዳ አልፌ ወደ ቤተክርስትያኑ ውስጥ አቀናሁ ይህንን ብርሃን ያሳየኝ ጌታየን አመስግኘ የመነኩሴው ድንገት መጥፋት አሳስቦኝ ስለ ሁኔታው ላጠያይቅ በአቅራቢያ ወዳሉ ባዕቶች አቀናሁ አካባቢው ጸጥ ረጭ እንዳለ ነው። ድምጼን ጎላ አድርጌ ሰላምታ ሰጠሁ ከጎጆዋ ውስጥ ይመስገን ፈጣሪ የሚል መልስ አገኘሁ።
ቢጫ የመነኩሴ ፎጣ ደርበው የለበሱ ጎልማሳ መነኩሴ አስኪማቸውን እያስተካከሉ ከጎጆ ባእታቸው በቅ አሉ። እንደምን አሉ አንድ ነገር ጨንቆኝ ላወያይወት ነው የመጣሁ.. ከሩቅ ሃገር ነው የመጣሁት ብየ አንገቴን ስሰብር ምነው ምነው ምን ገጠምወት አሉኝ።
አባ ገ/ሂወት የሚባሉ መነኩሴ ያውቃሉ? እርሳቸው ለማስታወስ እየሞከሩ አባ ገ/ሂወት አባ ገ/ሂወት አይ አይ እንዲህ የሚባል መነኩሴ እዚህ አላውቅም በእጃቸው የመጋቢውን ቤት እያመለከቱ ግን በይበልጥ ከ መጋቢው ዘንዳ ሂዱና እሳቸው መነኮሳቱን በደንብ ያውቋቸዋል ይጠይቁ አሉኝ።
ከተጠቆምኩት ቤት ሄድኩ መጋቢውን ዘለግ ባለ ድምጽ ሰላምት ስስጣቸው መልስ የለም በጀርባ በኩል ስሄድ ከጎጆዋ ጀርባ ያሉ እጽዋቶችን ይኮተኩታሉ።
ሰላምታየን አቅርቤ አባ ገ/ሂወት የ ሚባሉ ሰውየ ጋ ትላንተ በምሽት ተጉዘን ከ ገዳሙ እንደደረስን በእጀ እየጠቆምኩ ከ ባዕታቸው እንዳሳረፉኝ መኮሬታ አቅረበውልኝ እራቴን እንደበላሁ እና እንደተኛሁ በለሊት ከእንቅልፌ ስነሳ መንኩሴውን እንዳጣዋቸው በመጥፍታቸውም እንደ ጠጨንኩ አስረዳሁ።
ልጀ አባ ገ/ሂወት የሚባል መነኩሴ እዚህ የለም ያ የጠቆምከኝ ቤት ሰው አይኖርበትም ገተዘጋ ረጂም ጊዜው ነው አዲስ መነኩሴ ሲመጣ ታይቶና ተመዝኖ ሊሰጠው የተዘጋ ቤት ነው ደግሞስ መኮሬታ ነው የተመገብከው አሉኝ? አው ከዳጉሳ የተዘጋጀ ምላስ ያዝ የሚያረግ አልኳቸው እንግዲያውስ የገዳሙ ምግብ ዳቤ እንጂ መኮሬታ አይደለም አካባቢው ደጋ ስለሆን በብዛት የገብስ ምርት እንጃ ዳጉሳ መሬታችን አያበቅልም አሉኝ።
ካለሁበት ደርቄ ፈዝዠ ስርበተበት ተመለከቱኝ ትላንትነት በቅጀቴ ውስጥ ያለፈ ህልም እንጂ ኑሬው ያለፈ አልመስል አለኝ።
ጤነኛ መሆኔ ተጠራጠርኩ ሰው መስሎ የተጫወተብኝ ባዕድ ፍጥረት የሆን ወይስ የአየር አጋንት እንደ ሰው የሚያወሩ የሚያናግሩ ሰውን የሚመስሉ ጂን እና ቆሌ ይሆን?
መጋቢው መነኩሴ መጨነቄን ሲመለከቱ አረጋገተው አስቀመጡኝ። ጸሎት አድርገው ጸብል እንዲተምቁኝ ተማጸንኳቸው ለረጂም ስአት ድርሳናትን ደግመው ጸበሉን ጠመቁኝ። ቢያንስ መንፈሴን የሚያውክ ስሜት ስላልተሰማኝ ተረጋጋሁ።
ስለ ሁኔታው ጠየቋቸው ምን ሊሆን ይችላል አልኳቸው? .....
ግራ በመጋባት ስሜት አንድ አንድ መነኮሳት ከኢትዮጵያ ጫፍ ጫፍ ወደ የገዳማቱ የሚጓዙት በእግር ነው በዚህም አጋጣሚ ሲመሽ የተለያየ ቦታ ያድራሉ። እኒህ መነኩሴ ድንገት ከዚህ የነበሩ ግን አሁን ሌላ ገዳም ውስጥ የሚኖሩ ሲጓዙ መሽቶባቸው ወደዚህ ሲያመሩ አንተ ጋ ተገናኝታችሁ እዚህ አርፈው ሰው ሳይነሳ በለሊት ጉዞ ጀምረው ሊሆን ይችላል አሉኝ። ለምን በለሊት መሄድ አስፈለገ? ለምን አይሰናበቱኝም? በዝናብና ነጎድጓዱ እንዴት ሊሄዱ ቻሉ? ሌላው ደግሞ የወይን ፍሬው ነገርስ ከመሄዳቸው ጋር የሚገናኝ ነገር ይኖረው ወይስ አጋጣሚ የሆነ ነው? መጋቢው መልስ ይሰጠኝ ዘንድ አይን አይናቸውን አያለሁ።
መጋቢያው ቀጠሉ እዚህ ቦታ ላይ ለእንግዶች በርካታ እንቆቅልሽ የሆኑ ክስተቶች በየጊዜው ይከሰታሉ.... ይቀጥላል
7 163
ከከእለታት በአንዱ ቀዝቃዛ እለት
ፀሐይ ከማደርያው ሳትወጣ ጨረቃና ከዋክብት ዝናብ ባዘለ በጥቁር ደመና ተሸፍነው በውርጭ የተመላ ካፊያ አግድም ይወርዳል። ከማደሪያየ ተነስቸ ጸሎተ ማርያምን አደረስኩ።
ለጉዞ የሚያገለግሉ እቃወቸን አሰናድቸ ለምግብነት የሚሆነኝን ቆሎ በፌሳታል ቋጥሬ ጭፍናውን መንገድ ለመጓዝ የሚያዳግት ደቅድቅ ዝናባማ ጨለማ መንገድ ተያያዝኩት ።...
የገዳማት የአመት ክብረ በአልን ለማክብር ሳስብ ከእለቱ ቀን ቀደም ብየ ገዳሙ ጋ የመገኘት እና የመሰንበት ልምዱ አለኝ ።
በዚህ ልምዴ በርካታ ገዳማውያንን ወዳጆች አፍርቻለሁ አለም ስታዝለኝ የማርፍባቸው፣ መንፈሴ ሲታወክ የሚያድሱኝ፣ በአለም ፈተና ስወድቅ በሃጥያት ቀንበር ስያዝ በተስፋ ና በጸሎት የሚያበረቱኝ አባቶችን አግኝቸበታለሁ። የገዳማዊነት ሂወት ፣ እራስን የመግዛት ጥበብ ፣አለምን ቀደመው የመረዳት ችሎታ፣ ትግስት ፣ የሂወት ፍሬዋን ለመብላት የሚደረግን ጽናት ፣ በገዳማውያኑ አኗኗር ዘየ ውስጥ አስተውያለሁ ። ለዚህም ነው ከ ክብረ በአል እለቱ ቀደም ብየ የምገኝበት ምክኒያት።
ይህንንም ታሳቢ አድርጌ ረጅሙን መንገድ ሳይመሽ ለመቋጨት ነበር በዝናባማው ለሊት መንገዴን የጀመርኩ።
ከተወሰነ የመኪና ጉዞ ከስአታት በኋላ ወደ ገዳሙ ለመሄድ በኮረብታማ ተራሮች በዛፍ በተጠቀጠቁ ደኖች ውስጥ ረዘም ያለ የእግር መንገድ መጓዝ ግድ ነበር። ይህ ጉዞ ደግሞ አብሮ የሚጓዝ መንገደኛ ከሌለ ለአደጋ ተገላጭ ያደርጋል። የተለያዪ አውሬ እንዲሁም ወንበዴ ሽፍቶች እንዳሉበት ስለሚወራ በዚህው አካባቢ መንገደኞች በአብሮነት የመጓዝ ልምድ አሏቸው።
ወደ ገዳሙ ለመጓዝ መንገደኞችን መጠበቅ ነበረብኝ እና ከአነስተኛ ከተማዋ ካለው ዳገት ወጥቸ ወደ ገዳሙ የሚወስደውን መንገድ ላይ ከሚገኝ ቋጥኝ ጥላ ስር ተጠልየ አብሮ የሚጓዝ መንገደኛን ይመጣ ብየ አይን አይን እመለከታለሁ...።
ለስአታት ከዚሁ ቋጥኝ ስር ካለው ጥላ አቅጣጫ እየቀያየርኩ በመጠለል መንገደኛ መጠባበቅ ጀመርኩ..... የመጣ ግን አልነበረም። በጥቁር ፌስታል ከያዝኳት የሽንብራ ቆሎ ዘግኘ እየቆረጠምኩ ከኮረብታው ስር ያለችውን ቀጭን መንገድ ሰው አይበት ዘንድ እየተመኘሁ አሻግሬ እመለከት ጀመርኩ የመጣ አንድም ሰው ግን አልነበረም።
ወደረኛዋ ከ ደመናው ስር በስሱ የወጣችው ጸሃይ ወደ ማደሪያዋ እየገሰከሰች ጀንበሯን እያዘቀዘቀች ነው።
ብቻየን ለመጓዝ በተደጋጋሚ ተነስቸ ከዚህም በፊት በዚሁ መንገድ ላይ ብቻቸውን የሄዱ ሰወች ያጋጠሟቸውን ችግሮች ስለሰማሁ ተመልሽ እቀመጣለሁ።
ከአነስተኛ ከተማ ቀመስ ገጠር ርቄያለሁ እና በመሸም ጊዜ ወዘልውጥን ሰው የማትቀበል ስለሆነች መመለስን ፈራሁ። ወደ ገዳሙም ብቻየን ለመሄድ ልቤ ተሸበር። ከቋጥኙ ላይ ወጥቸ አይኖቸን በየ አቅጣጫው እየወርወርኩ መጠለያ ቤተክርስትያን አገኝ ብየ በአይኖቸ አስሳለሁ ነገር ግን ከተጠቀጠቀ ጫኳ ውስጥ መርፌ እንደ መፈለግ ሆነብኝ።
የፀሐይ ጉዞዋ ያለ ወትሮዋ የፈጠነም መሰለኝ ምናለ የ ኢያሱ ወልደነዌን ጸጋ ባደለኝ ወይ ደግሞ ከጠቢባኑ ጥብብን ብካፍል እንደገባኦን ምድር ፀሐይን ከማደሪያዋ አዘገያት ጨረቃን ከቤቷ አጸናት ነበር ብየ ተመኘሁ ።
ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ከተቀመጥኩበት ቋጥኝ ስር አሻግሬ ስመለከት ወደ እኔ እየመጣ ያለ ነገር ተመለከትኩ ሰው ይሁን እንስሳ መለየት የማልችልበት ሁኔታ ነበር።
እየቀረበ ሲመጣ ሰው እንደሆነ ተረዳሁ ምን አይነት ሰው ይሆን የሚለው ሌላ ጭንቀት ሆነኝ...።
ለአንባቢ እንዳያሰለች ከፋፍየ ለማቅረብ ቀጣዩን በቀጣይ ጊዜ....
እንደ ዘኪወስ ያጠሩ የቆሸሸ ቡናማ አስኬማ(የምንኩስና ቆብ) አድርገው ግራጫ ቀሚስ ፣እንደ ነገሩ ትክሻቸው ጋ ያገለደሙት ቢጫ የመነኮሳት ፎጣ የለበሱ ፣ ከጀረባቸው ጆንያን ያዘሉ፣ በቀኝ እጃቸው ከስሩ ጦር መሰል ከላይ መስቀል ያለው የብረት መቋሚያን የያዙ መነኩሴ ነበሩ።....
እፎይ አልኩ ክርስቶስ የላከልኝ መላክ እንጂ ሰው እስከማይመስሉኝ ድርስ ተደስትኩ። ለውሳኔወቸ ሁሉ አማካሪ ለችግሮቸ ሁሉ የጋራ ወሳኝ ሰው በማግኝቴ እጂጉን ተደስትኩ። ...
የያዝኩት የእጂ ስልክ ባትሪ ዘግቶ የስአቱን ሁኔታ ከ ጸሐይ ይልቅ የምገምትበት አጋጣሚ አላገኘሁም.. ።
ጸሐይዋ ቀና ብየ ስመለከት ለይቶላት ወደ ምዕራቡ ማደሪያዋ በር ተቃርባ የመግቢያ መስኮቶቿን ታንኳኳለች ።
እንደ መላክ የወረዱልኝ መነኩሴ ሲጠጉኝ
እግዚአብሔር ለእኔ ሲል የላካቸው መላክ እንጂ ሰው አልመስል አሉኝ።
ካህን መነኩሴ መሆናቸውን በአንገታቸው ስር በወረደው በወፍራሙ በተገመደ ክር ያንጠለጠሉትን የብረት መስቀል አይቸ ከ ጉልበቴ በርከክ ብየ ቡራኬን ተቀበልኩ።
ለስለስ ባለ የደካማ ሰው ድምጽ ሰላምታ ሰጠውኝ በዚህ ስአት ብቻየን ለምን ከዚህ እንደተገኘሁ ጠየቁኝ። ወደ ገዳሙ ለመሄድ ፈልጌ መንገደኛ ስጠብቅ እንደመሸብኝ አስረዳዋቸው።
''በል እኔም ወደዚያው ነኝ ተከተለኝ ብለው ፈጠን ፈጠን አሉ ''...እንዴ አባቴ መሽቷል መንገዱ ኮ ከ ሶስት ስአታት በላይ የእግር መንገድ ነው ስለዚህ በአቅራቢያ መጠጊያ እንፈልግ አልኳቸው ''አይ አይ መነኩሴ ከባዕቱ( ከመኖሪያ ) ወጥቶ አያድርም በል አቋራጨ መንገድ ስላለ በዚያ እንሄዳለን ባይሆን ለ አውሬና ሽፍቶች ጸሎተ ማርያምን እየደገምን እንጓዛለን ''... በማለት መንገዳቸውን ቀጠሉ...እጂግ በሚገርም እምንነት በሙሉ ልቡና መንዱን ሲጀምሩ ወደራሴ እንዳይ የ ማንነቴን ዝቅታ የእምነቴን ወሃልክ እንድመለከት አደረጉኝ እንዲህ ያለ ባለጽኑ እምነት ክርስትያን ባለበት እኔም ክርስትያን ተብሎ የመጠራት የሞራል ልዕልና ከእኔ እራቀ።
ቢሆንም አማራጭ ስለሌለኝ ከአማኝ በጎደለ እምነት በፍራቻ በርኖስ ተሸብቤ ከኋላቸው መንገድ ጀመርኩ.... አባ ገብረ ሂወት እንደሚባሉ ተዋውቀን የእኔንም ስም ነግርያቸው ከያዝኳት ጥቁር ፌስታል ቆሎን ዘግነን እያወጋን ባለ ግርማውን ጫካ ደርት ደረቱን እየገመስን እንገሰግሳለን።
ስለ እርሳቸው ልጂነት የወጣትነት ሂወት ኑሮ የገዳማዊ ሂወትን እንዴት እንደመሰረቱ ሁሉ ከላይ ከላይ በጥያቄ ይዣቸዋለሁ......
በ ደጋው አካባቢ በ1940ወቹ መጀመርያ እንደተወለዱ እና በልጂነታቸው አባታቸው እንደሞተ በእረኝነት ኑሮ የልጂነት ሂወታቸውን እንዳሳለፉ በእረኝነትም ላይ የእግዚአብሄር ጥሪን ሰምተው ወደ ገዳም ሊሄዱ ሲያስቡ እያለ ቤተሰብ ሊድሯቸው ሲሉ በለሊት ሸሽተው እንደሄዱ ለረጂም አመታት በተለያዩ ቦታወች እንደተዘዋወሩ እና ይህንን የምንኩስና ሂወትም ከፈጸሙ ከ አርባ አመታት በላይ እንደሆናቸው ደስ በሚል አረጋዊ ድምጽ በሹክሹክታ እየተረኩልኝ መንገዳችንን ቀጠልን..
ከብዙ ድካም በኋላ ጋራ ሸንተረሩ ዱርና ባህሩን የአራዊቱን ጩሆት አሳልፈን በድንገዝጋዛ ምሽት ግርማው በሚያስፈራ ጨለማ ውስጥ አልፈን ከሩቅ የሚታይ ቦቀታ ብልጭ ድርግም የሚል የኩራዝ ጭላንጭል ሲታየኝ ሌላ አለም የገባሁ የተስፋዋን የከንአንን ምድር አሻግሬ ያየሁ ያክል ደስታ እና ሲቃ ተሰማኝ።......
''ደርሰናል ደርሰናል አሉ በዝግታ....በል ዛሬ ወደ እንግዳው ቤት ለመሄድ ስአት ስለመሸ ከእኔ ዘንዳ ታርፋለህ''....
''ከጫካው ስር ቤተክርስቲያኑ አለ ክብ ሰርቶ አምሮ እና አብቦ የሚታየው ዛፍ ከልሎታል አሉ''
ቤተክርስቲያኑ አለበት ወዳሉኝ አቅጣጫ ተሳልሜ እሳቸው ከፊት እኔ ከኋላ ወደ ባእታቸው ተጓዝን።
የመነኮሳቱ ባዕት ጣሪያው ከሳርን ከ አገዳ የተሰራ ቋሚው ደግሞ ከባህር ዛፍ እንጨት የሚዘጋ
7 163
በህልሜ ይመስለኛል.....
በሰሜን ተራሮች በአንዱ ፣የሚስጥሩ አንባ ማህጸነ ደብረ ደደክ ......ወ አመሳለ ሲና ራስ ደጀን አቀናሁ!
ተፈጥሮው ድንቅ፣ ውበቱ ግሩም፣ ከሰማዮ ጋር የሚያወጉ ተራሮች ይታያሉ ፤ከሸማኔ ጥበብ በላይ ተፈጥሮ ራሱን እንዴት ባለ ጥበብ ሸምኖ ያለብሳል ?
የትኛው ጠቢብ እስትንፋስን አላብሶ እንዲህ እፁብ ድንድ አድርጎ ይፈጥራል ?
ራስ ደጀን ለ1500 ዓመታት በላይ የስውሩየቅዱስ ያሬድ መኖርያ ሚስጥራዊው የአፍሪካ ጣሪያ ፤ ምድር የታመቀውን አየሯን ማስተንፈሻው አንዱ ይህ ራስ ደጀን ሲሆን ሌላው ሜዲትራንያን ስር ... ያልተገለጠ እውነት ያልተነገረ ምስጢር ....አለ!
የአፋሩ ኤርታሌ የበርባኖስ
የሰሜኑ ራስ ደጀን የብሄረ ህያዋን
የጎጃሙ ግዮን የገነት ትይዮ ናቸው....
ይህ ማለት ባህሪያቸውን የሚወራረሱ፣ ረቂቅ ሚስጥርን የሚቃመሱ ፣ የ ሰማይ እና የምድር ትይዮ ሀይል የሚካፈሉበት ፣ድንቅ ተፈጥሮአዊ ኮድ ያላቸው ናቸው...
አበ ቴውድሮስ ወ ወሉደ ኢትዮጵያ ...ወደ ራስ ደጀን ሰሞኑን አቅንች አለሁ...እጂግ አድካሚ አንዲሁም አስደማሚ ከምድረ በዳ ላይ የሚያውድ የእጣን ጢስ ያሸተቱኩበት፤ ገቢረ ታምራቱ በተፈጥሮ ለዛ በግልጽ የሚታይበት ፤ ድምጻቸው ብቻ የሚሰሙ ስውራን ሰወችን የሚያነጋግሩበት፤ ድምጻቸው እንጂ ፊታቸው ፈጽሞ ማየት የማያቻል ወደ ቦታው ለሚያቀና ለጨነቀው መጽናኛን፤ ለደከመው ረፍትን ለህሙማን ፈውስን የሚያመጡ፤ ጸሎት ልመናቸው የሚደርስ ሃብተ ትንቢት የሞላባቸው ስውራን ....ከ ለሊቱ 9 ስአት የተጀመረ የእግር ጉዞ የሰሜን ተራሮችን በብረድና ቁር አቀበትና ቁልቁለት ከ 4600 ሜትሮች በላይ ከፍታን እየወጣሁ እጓዛለሁ እወጣ እወርዳለሁ .... ቅዱስ ያሬድ ያስተማረበት ሆጮው፤ ከየት መጣ የማይባል የ እጣኑ ሽታ የሚያውድበት ፤ያሬድ በበትረ ሙሴው ያፈለቀውን ጸበል አልፌ.... በስውራን አባቶች የተባረከን ቡራኬ አግኝቸ ..ከ መናንያን ጋር ልነጋገር ከስውራኑ ጋ በረከት ልካፈል ወደድኩ....ከቆላና ደጋ የተሰባሰበው ሰው ቀጭኗን መንድ ዘጋግተወ መተላለፊያ እስካጣ ድረስ መድረሻ አጣሁ..... እንደ ግማሽ ጎን ገበቴ የሚመስል ተራራ ላይ የሚገኙትን መናንያን አግኝቸ የልቤን እጠይቃቸው ዘንድ ወደድሁ ...
ከድካሙ አንጻር የሚንቀጠቀጡ እግሮቸን ዘርግቸ ከጋራው ላይ ተደግፌ ገደም አልኩ ...
ወደ ሰማዩ አንጋጥጨ .... ያሬድ ያሬድ ያሬድ አደራየን እበላ ዘንድ ተውከኝ እላለሁ....የደብረ ደደኩ ምሲጥር ይፈታልኝ ዘንድ ደጂህ የቆምኩትን ከርታታ ስለምንስ ተውከው? ከ ደገኞች ደብረ ጻድቃን ዘር የሚወጣው ውሉደ ደደክ የት ነው ያለው? አንተ ያሬድ እውነትን ያውቅ ዘንድ ከ ራስ ደጀን እስከ ግዮን የተንከራተተው ጎስቋላ አደራየን እወጣ ዘንድ አትረዳኝም እላኣለሁ...ስውራኑን አገኝ ዘንድ ተመኘሁ ግን አልቻለኩም...አንገቴን አቀርቅሬ ቁልቁል ወደ ሸለቆው ልወርድ ስነሳ የያዝኩትን ጸበል ለማገዝ መንገድ ላይ የተቀበለኝ ከዛም የተጠፋፋነው ህጻን ልጂ ከ ጸበሉ ጋር በፌስታስ የታሰረች ወረቀትን አቃብሎኝ ከህዝቡ መሃል ገብቶ ተሰወረ.....መንገድ ባናወዘው እግሮች ቁልቁል ወደ ዋሻው አቀናሁ....
ቅዱስ ያሬድ የተሰወረበትን ዋሻ ተመልክቸ ....... 13 ስአታት ቆይታ በኋላ ምሽት 11:30 ላይ ብዙሃኑ ሊያዮት የሚመኙትን የሰውራኑ መኖርያ የድንቅ ተፈጥሮ መገኛ ቅዱስ ያሬድ ገዳም ደረስኩ....
ጎኔን አሳርፌ በሃሳብ እንቀዋለላለሁ ለሰው የማልነግረው አደራ የማላካፍለው ምስጢር....እንቅልፍ ሲጥለኝ ከወዲያ በኩል በዜማ ..
አሠርገዋ ለኢትዮጵያ ፤ በስብሐት ወበሃሌ ሉያ ፤ ያሬድ ካህን ፀሐያ ፤ አስተካልሐ በቅዳሴ ፤ በዘሱራፌል አርአያ ፤ ያሬድ ካህን ፀሐያ ፤ ለበግዕ በትንሣኤሁ ፤ ደመ ጥብሑ አርወያ ፤ ያሬድ ካህን ፀሐያ ፤ በመኃልይሁ አቅነያ .....እያሉ የሚያዜሙ ሊቃውንት ድምጽ ቀሰቀሰኝ....
በትራሴ ካደረኳት ሻንጣየን ከኪሷ መዝዠ የተጻፈችውን የተጠቀለለች ወረቀት ተመለከትኩ.....
"ለሁሉም ጊዜ አለው በደም የተገነባው ንግስና በ ባርነት ይጠናቀቃል፤ ልቡ የደነደነች ፈርኦን ቀኝ እጂ ትሰላለች፤ አቅም ያጣ ሽባ ሁኖ ይዋረዳል በወንድሙም ይገደላል፤ ማቅ የለበሰች ገላ እንደ ሃጫ በርዶ ትነጻለች።
ከ ደጀን አባን ፀሐይ ይወጣል ..ሙቀት ያለው የማያቃጥል ፤ብርሃን ያለው የማይጨልም ፀሐይ ..ፀሐዩ ለተመረጡት ያበራላቸዋል ለግፊአን ይጨልማል ...
ግን ለወሊሃ እዘኑ ለርብ ወንዝም አልቅሱ! ''ትላለች
ከ ተደላደልኩበት ከሞቀ ቤቴ ቅጀ'ት የመሰለ የ ደጀን ጉዞየ ተራ ህልም እንደሆነ አሰብኩ.....እስክነቃ ድረስ እንደ አቤሜልክ እተኛ ዘንድ ወደድሁ፤ ያየሁትን ህልም 'ህልም እልም' ብየ ፀሐይዋ ወጥታ ከእንቅልፌ እስክነቃ ተኛሁ......
7 163
አስደናቂ የገዳም የጉዞ ታሪኬን ይዠላችሁ እቀርባለሁ...ፍለጋ ..ፍርሃት... ጭንቀት.. ተስፋ... ፈታኝ አጓጊና አስጨናቂ በሚስጥራት የተከበበ ፍለጋ.....ዮቲብ መከታተል ለማትልሉ በጹሑፍ የሚቀርብ ይሆናል...
7 163
አለም ላይ ተጽኖ ፈጥረው አልፈዋል ከሚባሉ አስደናቂ ምሁራን አንዱ የሆነው ጀምስ ብሩስ ነው።
ጀምስ ብሩስን አለም የሚያውቀው ታላቁ የሚስጥር መጽመፍ መጽሐፍ ሄኖክ ለአለም በማስተዋወቁ ነው።
የአለምን ሚስጥራዊ ኮድ ይፈታል የሚባልለት የአለም ልሂቃን ተሰባሰብ በየ አመቱ በ ቫቲካን የሚወያዩበት ይህንን ድንቅ በሚስጥር ከ ኢትዮጵያውያን በመስረቅ መጽፍን ለንግስት ቪክቶርያ በማበርከት ሙገሳን ያገኘው ጀምስ ብሩስ....
በ ኢትዮጵያ ገዳማትና አድባራት ግዕዝን ጨምሮ ለአመታት ጥበብና እወቀትን በመማር በመ መርመር አሳልፏል።
ጀምስ ብሩስ የተማረበት በርካታ ሚስጥራዊ መረጃወችን የበረበረበት የቁም ስእልና ጽሑፍ ሲሰራበት የነበረው...የመጽሐፎቹ መደርደርያ.. የምኝታ ክፍሉ የጠባቂወቱ መቆሚያ ላሳያችሁ ወደድሁ .....ይህንን በፈለገ ጥበባት የዮቲብ ቻናል documentary ተሰርቶሎት ከቦታው ድርስ ተጉዘን ይዘንላችሁ እንቀርባለን....
7 163
ጥንታዊያኑ ኢትዮጵያዊያን ከሥጋዊ ህይወታቸው አልፈው በመንፈሳዊ ህይወታቸው እና ማንነታቸው ከአለሙ ሁሉ ቀድመውና ልቀው በሃያልነት ይኖሩ እንደነበር ድንበር ተሻጋሪ የእጅ አሻራዎቻቸው ይመሰክራሉ።
አለማችን በአግባቡ ያልተረዳናት በረቂቅ ቀመር የተዘጋጀች አስደናቂ ናት። በተለይ በቀደምት ኢትዮጵያዊያን እወቀተ ስጋዊ ከእወቀተ መንፈሳዊ ጋር አዳምርው እና አሰናስለው በስጋዊ አይን የሚታዮም የማይታዮም ረቂቅ ስራወችን ሰርተውልን አልፈዋል።
አንዳንዶቹ በዘመናዊው ቴክኖሎጂ በ Arifical intelligence (AI) clocking device በኢትዮጵያውያን እጸ መሰውር ውስጥ ነገሮችን ከእይታ ውጭ እንደሆኑ ይነገራል።
በመንፈሳዊ እይታ እና ኃይል ከተጻፈው ከመጽሐፈ ምስጢር አዶናይ ራፋኤል መጽሐፍ ላይ ምንጭ በማድረግ ኢትዮጵያ ላይ በአራቱም አቅጣጫዎች ስውር ፒራሚዶች እንዳሉ ይነገራል.... ታዲያ እነዚህ የፒራሚድ ከተሞች ምንም እንኳ ስውር ይባሉ እንጂ ለጥቂቶች በግልጥ እንደሚታዩ ይናገራሉ ይህ ማለት እንዴት ነው? ስውር የሚባለው ለብዙኃን ተሸፍኖ ወይንም ድብቅ ሆኖ ለጥቂቶች ግን ግልጥ የሆነ እንደማለት ነው። ታዲያ እነዚህን ፒራሚዶች ግልጥ ሆነው ለመመልከትና ለማየት የተለየ አይን ( ሦስተኛ አይን ወይንም መንፈሳዊ አይን ) እንደሚያስፈልገን ይነገራል ፤ በነገራችን ላይ እነዚህ የፒራሚድ ከተሞች የረቀቀ መንፈሳዊ ትስስር ከሰው ልጆች ጋር አላቸው።
አለማችንን አሁን ከሚታየው ግዘፍተ ከነሳው አካል ባሻገር በረቂቅ እይታ ውስጥ የተቀመር አስደናቂ አለም አለ። ረቂቃኑን አለም እንዴት ማየት ይቻላል የሚለውን በሌላ ፕሮግራም እጸፍላችሁ አለሁ....
ቀደምት ኢትዮጵያዊያን በዚህ ረቂቅ መንፈሳዊ ትስስር ተጽዕኖ ምክንያት የበርካታ የጥበብ ባለቤቶችም ሆነው ኖረዋል።
ጥያቄው የሚሆነው በስጋዊው አይን ማየት የማይቻሉ ረቂቅ እወቀትና ጥበቦችን እንዴት ማየት እንችላለን የሚለው ነው......
እኔ ግን ይህንን እላለው ከልባችን ከሻትነው ተሰውሮ የሚቀር አንዳችም ነገር የለምና ፍለጋውን ተቀላቀሉ...
7 163
ሰላም.....
ብዙወቻችሁ ማወቅ መስማት የምትፈልጉትን አስደናቂው ፍካሬ ኢየሱስ የተባለው የትንቢት መጻህፍ በድምጽ ይዠላችሁ እቀርባለሁ....
ፈለገ ጥበባትን ሸር በማድረግ ይተባበሩ
7 163
ወሊሃ ወዮላት ለርብም እንጃ ያን ዕለት ....
ከተራራው ጫፍ ላይ ቁማ በእዳፊ ጨረቅ አካሏን ለመሸፈን የምታታገል የተጎሳቀለች እናት አይቸ ወደ ተራራው ጫፍ አመራሁ....የአመድ ብናኝ በጠጉሮቿ መልቶ ገላዋ በውርጭና ቁር ተሰነጣጥቆ እርቃኗን ለመሸፈን እጣፊው ጨርቅ አልበቃት ያለች ምስኪን እናት ....እግሮቿ መርቅዘው እዠ እሲያወጡ አይኞቿ ከሞቱት በነቁ ካሉት በደከሙ እርግብግቢት የሚዋትቱ ፤ የአይኖቿን መክደኛ ለማንሳት አቅም ያጣች እናት...ወደ ተራራው ጫፍ ተጠጋሁ ምን እንደሆነች ለመጠየቅ ዳዳሁ ''ሰላም የእኔ እናት'' አልኩ በለሁሳስ ድምጽ ከተራራው ስር የሚፈስ የደም ወንዝ ይታየኛል... .....ከጉልበቶቿ እንደተጣበቀች ከአቀረቀረችበት ሳትነሳ ፊቷን መለሰችብኝ እንኳን ልታነግረኝ ልታየኝ እንኳ ፍቃደኛ አይደለችም።
...የሰው ነገር በቃኝ ያለች በምድረ በዳ ልትኖር የተገደደች ምስኪን.... ጤናዋ የታወከ ልጆቿ የከዷት ትሆንን ?
እርስትና ና ጉልቷ የተውሰደባት ልጆቿን መ'መገብ የተሳናት ትሆንን? ቤቷ ላይዋ ላይ የፈረሰ? ባሏ የከዳት እናት ትሆንን አላለሁ....
እናቴ ሆይ አልኩ በድጋሚ ምን ሁነሽ ነው ምን ደረሰብሽ ?...መልስ የለም እንባዋ በተራቆተው ገላዋ በጉልበቶቿ ሲወርድ አየዋለሁ..አይኖቸ አይኖቿን ተጋ'ሩ እንባወቿን ላለ'ማንባት አቅም አጡ..መልስ ትሰጠኝ ዘንድ ደጋግሜ ስጠይቃት በአገጯ ከተራራው ስራ ወዳሉት ሰወች ጠቆመችኝ በእጆቿም የተጠቀለል ወረቀት አቃበለችኝ ......ሁለት ወጣቶች እና ከኋላቸው የሚከተል አንድ አዛውንት ተመለከትኩ...መልሱን ከእነሱ ታገኛለህ የሚል መልእክት ነበር የሰጠችኝ ....
አቀበቱን ሲወጡ ወደ ተራራው ለመድረስ ሲታገሉ...
እንዲህ ይባባላሉ ''ደከመን ከተራራረው ጫፍ ለመድረስ ተሳነን እንረፍ'' ተባባሉ አረጋዊው አባታ ከኋላቸው ደረሱና ምን ሁናችሁ ቆማችሁ ቢሏቸው ''መንገዱ ከበደን ፀሐዩ ጸናብን እሾሁ አስቸገርን '...ጥቂት ብናርፍ ብለን'' አሉ...አረጋዊው ሰው ፈገግ አሉ '' ፀሐዮ ሐረሩ እሾሁ አሚካላ አቀበቱም ጸኑ ነው የምታርፉበት ጊዜ አልደረሰም ተነሱ ከተራራው ጫፍ ለመድረስ ጽኑ ታገሉ.. ቀኑ የሚጨልምበት ወንዙም ደም የሚሆንበት ቀን ሳይመጣ ተነሱ ተነሱ... አረጋዊው አባት አንገታቸውን አቀርቅረው ወደ ተራራው ጫፍ ሲሄዱ ግራ በመጋባት ተመለከትኳቸው ...
ከተራራው ላይ የተቀመጠችው እናት የሰጠችኝ ወረቀት ጸሑፉ እንዲህ ይል ነበር.....
ለወሊሃ እዘኑላት ለርብ ወንዝ አልቅሱ ....
ህልሙ ቅጀት ይሆን ዘንድ ተመኘሁ!
ከትውልዱ ማን አስተዋለ......በሉ ሰላም ሁኑ!
