uk
Feedback
ፈለገ ጥበባት +++

ፈለገ ጥበባት +++

Відкрити в Telegram

+++የቀደምት ኢትዮጵያውያን ስልጣኔን ማሳየት እንዲሁም ገዳማት እና አድባራትን ማሳወቅ፡፡+++ የተረሱ አድባራትና ገዳማትን ማስታወስ ፤የ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ጥበብ እውቀትን በምንችለው ሁሉ መመርመር የአባቶቻችን ልጆች በመሆን ትላንት በዛሬ እና በነገ ውስጥ ማስቀጠል ማስቻል ነው።

Показати більше
7 163
Підписники
-524 години
-267 днів
-7330 день
Архів дописів
ከዘመን ጫፍ ላይ ተንጠልጥየ በጠፍ ጨረቃ ቃጥቸ ደግሞ ዘመንን ቀምረው ሲያመሰጥሩ ተመልክቸ ጻፍ ጻፍ ሲለኝ ከ ሰሜን ባሻገር ባለች በባሩድ ሽታ በተመላች ከተማ ውስጥ ሁኝ እክተብላችሁ ዘንድ ተገደድኩ! ከለታት በአንዱ ቀን በድንገት ከቤቴ ተንስቸ መጓዝ ጀምርሁ....ሰው ወደ ለለበት፣ ድምጽ ወደ ማይሰማበት፣ ሁካታ ጠብ ክርክር  ንትርክ ወደ ማልሰማበት ወፌ ወደ መራችኝ ... ስለ እውነት ግን ደክሞኝ ነው.... መኖር ያደክማል አይደል? እልፍ መከራ መስማቱ ፣  የተጨነቀች ነብስ ብኩን የሆነችን ስጋ ማየቱ፣ ተስፋ የሌለውን ተስፈኛን መመልከቱ፣  ...ምህረት የማያመጣው ጸሎታችን.. የማያርግ መስውእታችን... የማን'ባረክበት ብኩርናችን .. ...ነጻ የማያወጣን ትምህርታችን...እያሰብኩ የኢትዮጵያ  የነጻነት ቀንዲሉ የሚለኮስበት ቀን አንገት የደፋችው አገር የምትቃናበት ጊዜ የደፈረሰው የሚጠራበት .... ጊዜ ይኖር ይሆን? እላለሁ ..በጠቆረው ዝናባማ ደመና ፣በሚያካፋ የዝናብ ነጠብጣብ፣ ጨርቁን ጥሎ እንደ አበደ ሰው የለበስኩት ፎጦ እየጎተትኩ ...ጯክ ብየ በ ምድረበዳ አወራለሁ .. እላለሁ ... 'የለህም እንዳልል ይመሻል ይነጋል        አለህም እንዳልል እንዲህ ይደረጋል'       እላለሁ.. ተስፋ የተሰጠን ተስፋችን  የት ሄደ? እላለሁ የማይነጋ ለሊት  ስንጠብቅ ...እንኖር ዘንድ ተውከን እላለሁ...ነጠብጣቡ ወደ ዶፍ ዝናብ ተቀይሮ መዝነብ ጀመረ... ከመምህሬ አድባር ዛፍ  ስር ከመሰለ ከወዲያ ማዶ ከ ገደሉ ጫፍ ከተንዘራፋው ዋርካ እጃቸውን  የሚያወዛውዙ ሰው ይታዮኛል.....ና ወዲህ ተጠለል በሚመስል ምልክት እየጠሩኝ... ወደ ዋርካው  ተጠጋሁ ...በል ከዚህ ይሻልሃል ሰላም ሁን ብለው ሲሰናበቱኝ ...መባርቅቱ በበዛበት ብልጭ ልጭታው በጸናበት ስአት የት ሊሄዱ ነው? አልኩ እና መመርኮዣ ዘንጋቸውን ያዝ አደረኩ.... ልጀ ሆይ የሰማይ ምሰሶዋ  ለቋል፤ የምድርም መሰርቷ ተናውጿል.... አመጸኛ በዝቷል   ሃጥያት ተንሳራፍቷል     የማያልፈው ዝናብ ከ ሚመታኝ የሚልፈው ዝናብ ያርጥበኝ ... ልጀ ሆይ ሰማዮን እንዳታየው ማን አይንህን ጋረደህ ? ልቡናህ እንዳያስተውል ማን አዚም አደረገብህ....?   እኔስ በቀን መሽቶብኛል፣ ከዚህ የባሰው ውሽንፍር ሳይመጣ   ወደ ማደርያየ ልገስግስ...አንተ ግን ሰው ሁን! ቀጠሉ..  አመጸናል እና ! ምን አልባት እንደ ኖህ ዘመን  ዛፉ ተቆርጦ ጉቶ እስኪ ቀር ይቆረጣል... መኪና ወዳልገባበት መንገድ ወደ ሌላለበት ልጓዝ .....እንደ ርብ ከመሆን ወሊሃንም ከመምሰል ግን ይሰውረን ልጀ ... ልብህ ከፈቀደ አንተም ሳይመሽ ተከተለኝ ..... ይህንን ከአመታት በፊት አልነገኩህም ወይ የሚል መልእክት በማላቃቸው አረጋዊ ዘንድ ተላከልኝ... ለጠቢብ አሃቲ ቃል ትብቁእ ! ለጥበበኛ ሰው አንድ ቃል ትበቃዋለች ! በሉ ደና ሁኑልኝ...   

በቀደም እለት እግሬ ወደ አመራኝ ቦታ በድንገት ከቤቴ ተንስቸ መጓዝ ጀምርሁ....ሰው ወደ ለለበት፣ ድምጽ ወደ ማይሰማበት፣ ሁካታ ጠብ ክርክር  ንትርክ ወደ ማልሰማበት ወፌ ወደ መራችኝ ... ስለ እውነት ግን ደክሞኝ ነው.... መኖር ያደክማል አይደል? እልፍ መከራ መስማቱ ፣  የተጨነቀች ነብስ ብኩን የሆነችን ስጋ ማየቱ፣ ተስፋ የሌለውን ተስፈኛን መመልከቱ፣  ...ምህረት የማያመጣው ጸሎታችን.. የማያርግ መስውእታችን... የማን'ባረክበት ብኩርናችን .. ...ነጻ የማያወጣን ትምህርታችን...እያሰብኩ የኢትዮጵያ  የነጻነት ቀንዲሉ የሚለኮስበት ቀን አንገት የደፋችው አገር የምትቃናበት ጊዜ የደፈረሰው የሚጠራበት .... ጊዜ ይኖር ይሆን? እላለሁ ..በጠቆረው ዝናባማ ደመና ፣በሚያካፋ የዝናብ ነጠብጣብ፣ ጨርቁን ጥሎ እንደ አበደ ሰው የለበስኩት ፎጦ እየጎተትኩ ...ጯክ ብየ በ ምድረበዳ አወራለሁ .. እላለሁ ... 'የለህም እንዳልል ይመሻል ይነጋል        አለህም እንዳልል እንዲህ ይደረጋል'       እላለሁ.. ተስፋ የተሰጠን ተስፋችን  የት ሄደ? እላለሁ የማይነጋ ለሊት  ስንጠብቅ ...እንኖር ዘንድ ተውከን እላለሁ...ነጠብጣቡ ወደ ዶፍ ዝናብ ተቀይሮ መዝነብ ጀመረ... ከመምህሬ አድባር ዛፍ  ስር ከመሰለ ከወዲያ ማዶ ከ ገደሉ ጫፍ ከተንዘራፋው ዋርካ እጃቸውን  የሚያወዛውዙ ሰው ይታዮኛል.....ና ወዲህ ተጠለል በሚመስል ምልክት እየጠሩኝ... ወደ ዋርካው  ተጠጋሁ ...በል ከዚህ ይሻልሃል ሰላም ሁን ብለው ሲሰናበቱኝ ...መባርቅቱ በበዛበት ብልጭ ልጭታው በጸናበት ስአት የት ሊሄዱ ነው? አልኩ እና መመርኮዣ ዘንጋቸውን ያዝ አደረኩ.... ልጀ ሆይ የሰማይ ምሰሶዋ  ለቋል፤ የምድርም መሰርቷ ተናውጿል.... አመጸኛ በዝቷል   ሃጥያት ተንሳራፍቷል     የማያልፈው ዝናብ ከ ሚመታኝ የሚልፈው ዝናብ ያርጥበኝ ... ልጀ ሆይ ሰማዮን እንዳታየው ማን አይንህን ጋረደህ ? ልቡናህ እንዳያስተውል ማን አዚም አደረገብህ....?   እኔስ በቀን መሽቶብኛል፣ ከዚህ የባሰው ውሽንፍር ሳይመጣ   ወደ ማደርያየ ልገስግስ...አንተ ግን ሰው ሁን! ቀጠሉ..  አመጸናል እና ! ምን አልባት እንደ ኖህ ዘመን  ዛፉ ተቆርጦ ጉቶ እስኪ ቀር ይቆረጣል... መኪና ወዳልገባበት መንገድ ወደ ሌላለበት ልጓዝ .....እንደ ርብ ከመሆን ወሊሃንም ከመምሰል ግን ይሰውረን ልጀ ልብህ ከፈቀደ አንተም ሳይመሽ ተከተለኝ ..... ለጠቢብ አሃቲ ቃል ትብቁእ ! ለጥበበኛ ሰው አንድ ቃል ትበቃዋለች !   

ሰላም!   በፈለገ ጥበባት ከሺ አመታት በፊት በ ነብያቱ በራዕይ ስለ ታየችው ዘጠነኛዋ የደም ጸሐይ ፤ ከዚህ ጋር ተያይዞ ስለ ተነገረው የአርማጌዶን ጦርነት የጦርነቱ ቦታው ጊዜው መቸ እንደሆን  እነማን በዚህ  ይሳተፋሉ በመጻህፍ ቅዱስ የተነገረው የጎግና ማጎግ ጦርነት እና ማጎጋዎያን የቶቤል ዘሮች እነማን እንደሆኑ ይቀርብላችኋል.. ፈለገ ጥበባትን በማስተዋወቅ  ሃላፊነታችሁን ተወጡ!

ህይወት ጂረት ናት ........ አንዳንዴ ጂርት በሆነች ህይወት መስመር ውሰጥ አባጣና ጎርባጣ ማግኘት ና ማጣት ፤ ከፍ ብሎ ኖሮ ዝቅ ማለት ፤ደስታና ሃዘን ...ሳቅና መራር ለቅሶ ..በሆነ ጊዜ ነጉስ ሁነን የኖረበት ምድር ፤  በሌላ ጊዜ ባርያ አድርጋ ቀንበሯን የጫነችብን  ሰወች አለን አይደል? ትላንት ሙሉ ተስፋ፣ ብርሃናዊ ኑሩ፣ ዛሬ ደግሞ በደቅድቅ ጨለማ ውስጥ የመኖር ያክል አለም ፊቷን ያዞረችብን አለን አይደል? በአደባባይ እየሳቅን በድንኳናችን ውስጥ ተወሽቀን የምናለቅስ፤ መኖር ከመሞታችን ጋር እኩል የሆነብን በተሰመረልን የምንጓዝ ፤ህይወት በመራችን ብኩን በሆነ ርምጃ  ፤ መዳረሻ በሌለው መነሻ የምንጓዝ ፤አለማው ላልታወቀ ሩጫ የምንሽቀዳደም ብዙወቹ አለን አይደል? በየ ጓዳችን ይህንን በመሰል የዢዋዢዌ ጨዋታ የምንናጥ ? በአመናቸው የተካድን፤ በወደድናቸው የተጠላን፤ ባከበርናቸው የተናቅን....ትዳር የእግር እሳት የሆነብን ፤ ልጆች ወልዶ ማሳዳግ የተሳነን፤ ኑሮአችን አልሞላልን ብሎ ቁርስን በልቶ ምሳ መድገም ቅንጦት የሆነብን ፤ እንደ አሽዋ ተበትነን የቤተሰብ ናፍቆት የሚያላውሰን ፤ ብዙ ሁነን አደገን  ብቻችን ቤት ታቀፍን በናፍቆት የምናለቅስ አለን አይደል?  የኢትዮጵያ ነገር አሳስቦን የምንቆዝም ...... በአንሶላና በትራሳችን እንባችን እየጠረግን   የማያጓጓውን ዛሬን፤  ሸከም የሆነብን  ነገን፤ እየፈራን የምንኖር አለን አይደል? ለጭንቀቶቻችን መፍትሔ፣ ለመከራችን መውጫ መንገድ፣  ጠፍቶን በሰው ተከበን ሰው ያጣን ከ አውላላ ሜዳ ላይ እንደ እንቦሳ ላም የምንቃትት አለን አይደል በየ መንደሩ?   አይዞህ ብሎ የሚበረታን ፤ ችግራችንን የሚጋራን ፤ሸክማችንን የሚሸከምልን፤ በእርምጃችን ልክ የሚጓዝ ፤ ህመማችን የሚያመው፤ ሳንነገርው የሚረ'ዳን ፤ሳንጠይቀው የሚሰጠን ሳንለምነው የሚመጸወተን .....ይህ ሁሉ ቀርቱ እህህህ በሎ የሚሰማን ጀሮ በማጣት ከ እበደት በረ ላይ የቆምን እንደ ሚያላዝን የለሊት ውሻ ፤እንደ ሚጮህ የቀትር ቁራ...የውስጥ ጩኸታችን የሚያደነቁርን የማንሸሸው ርግማን የሆነብን  .....አለን አይደል ከየጣሪያ ስር ከመጋረጃችን ጀርባ ተጠልለን ...... ከ አምላካችን ጋር የተኳርፍን፤ ለጸሎት ጥያቄወቻችን መልስ የላቸውም ብለን የደመደምን...ከኪዳኑ የራቅን፣ ከቅደሴው የሸሸን፣ የእጣኑ ሽታ ማዕዛው የጠፋብን ፣ ከሩቅ ቁመን የዕለት ጉርሱን እንደ አጣ ነዳይ ያቀረቀርን፣ አለን አይደል ብዙ ሁነን ጩኸታችንን ሊያሳብደን ዝምታችን ሊያፍነን የደረሰ..... አው ብዙ ነን በየቤታችን ያለን ......የተጨነቀችን ነብስ፤ አድማጭ ያጣችን  አንደበት .....ጅሮ ሰጥቸ  ልሰማ...የምችለውን መፍትሔም በእኔም በታላላቆቸም ልሞክር  እኔ አለሁ ለወገኔ ብያለሁ.... እኔን 👇👇👇 ታገኙኛላችሁ። @Nabuti21  ላይ ታገኙኛላችሁ!

በህልሜ ይመስለኛል..... በሰሜን ተራሮች በአንዱ ፣የሚስጥሩ አንባ ማህጸነ ደብረ ደደክ   ......ወ አመሳለ ሲና ራስ ደጀን አቀናሁ! ተፈጥሮው ድንቅ፣ ውበቱ ግሩም፣ ከሰማዮ ጋር የሚያወጉ ተራሮች ይታያሉ   ፤ከሸማኔ ጥበብ በላይ   ተፈጥሮ ራሱን  እንዴት ባለ ጥበብ ሸምኖ ያለብሳል ? የትኛው ጠቢብ እስትንፋስን አላብሶ እንዲህ እፁብ ድንድ አድርጎ ይፈጥራል ?    ራስ ደጀን ለ1500 ዓመታት በላይ የስውሩየቅዱስ ያሬድ መኖርያ  ሚስጥራዊው የአፍሪካ ጣሪያ ፤ ምድር የታመቀውን አየሯን ማስተንፈሻው አንዱ ይህ ራስ ደጀን ሲሆን  ሌላው ሜዲትራንያን ስር ... ያልተገለጠ እውነት ያልተነገረ ምስጢር ....አለ! የአፋሩ ኤርታሌ የበርባኖስ የሰሜኑ ራስ ደጀን የብሄረ ህያዋን የጎጃሙ ግዮን የገነት ትይዮ ናቸው.... ይህ ማለት ባህሪያቸውን የሚወራረሱ፣  ረቂቅ ሚስጥርን  የሚቃመሱ ፣ የ ሰማይ እና የምድር  ትይዮ ሀይል  የሚካፈሉበት ፣ድንቅ ተፈጥሮአዊ ኮድ ያላቸው ናቸው... አበ ቴውድሮስ  ወ ውሉደ  ኢትዮጵያ  ...ወደ ራስ ደጀን ሰሞኑን አቅንች አለሁ...እጂግ አድካሚ አንዲሁም አስደማሚ ከምድረ በዳ ላይ የሚያውድ የእጣን ጢስ ያሸተቱኩበት፤ ገቢረ ታምራቱ በተፈጥሮ ለዛ በግልጽ የሚታይበት ፤ ድምጻቸው ብቻ የሚሰሙ ስውራን  ሰወችን የሚያነጋግሩበት፤ ድምጻቸው እንጂ ፊታቸው ፈጽሞ ማየት የማያቻል   ወደ ቦታው ለሚያቀና  ለጨነቀው መጽናኛን፤ ለደከመው ረፍትን  ለህሙማን ፈውስን የሚያመጡ፤ ጸሎት ልመናቸው የሚደርስ ሃብተ ትንቢት የሞላባቸው ስውራን ....ከ ለሊቱ 9 ስአት የተጀመረ የእግር ጉዞ የሰሜን ተራሮችን በብረድና ቁር አቀበትና ቁልቁለት ከ 4600 ሜትሮች በላይ ከፍታን እየወጣሁ እጓዛለሁ  እወጣ እወርዳለሁ ....  ቅዱስ ያሬድ ያስተማረበት ሆጮው፤ ከየት መጣ የማይባል የ እጣኑ ሽታ የሚያውድበት  ፤ያሬድ በበትረ ሙሴው ያፈለቀውን  ጸበል አልፌ.... በስውራን  አባቶች  የተባረከን ቡራኬ አግኝቸ ..ከ መናንያን ጋር ልነጋገር ከስውራኑ ጋ በረከት ልካፈል ወደድኩ....ከቆላና ደጋ የተሰባሰበው ሰው ቀጭኗን መንድ ዘጋግተወ መተላለፊያ እስካጣ ድረስ መድረሻ አጣሁ..... እንደ ግማሽ ጎን ገበቴ የሚመስል ተራራ  ላይ የሚገኙትን መናንያን አግኝቸ የልቤን እጠይቃቸው ዘንድ ወደድሁ  ... ከድካሙ አንጻር የሚንቀጠቀጡ  እግሮቸን ዘርግቸ ከጋራው ላይ ተደግፌ ገደም አልኩ ... ወደ ሰማዩ አንጋጥጨ .... ያሬድ ያሬድ ያሬድ አደራየን እበላ ዘንድ ተውከኝ እላለሁ....የደብረ ደደኩ ምሲጥር ይፈታልኝ ዘንድ ደጂህ የቆምኩትን ከርታታ ስለምንስ ተውከው?  ከ ደገኞች ደብረ ጻድቃን  ዘር የሚወጣው ውሉደ ደደክ የት ነው ያለው?  አንተ ያሬድ  እውነትን ያውቅ ዘንድ ከ ራስ ደጀን እስከ ግዮን የተንከራተተው ጎስቋላ አደራየን እወጣ ዘንድ አትረዳኝም እላኣለሁ...ስውራኑን አገኝ ዘንድ ተመኘሁ ግን አልቻለኩም...አንገቴን አቀርቅሬ ቁልቁል ወደ ሸለቆው ልወርድ ስነሳ የያዝኩትን  ጸበል ለማገዝ መንገድ ላይ የተቀበለኝ ከዛም የተጠፋፋነው  ህጻን  ልጂ  ከ ጸበሉ ጋር በፌስታስ የታሰረች ወረቀትን አቃብሎኝ ከህዝቡ መሃል ገብቶ ተሰወረ.....መንገድ  ባናወዘው እግሮች ቁልቁል ወደ ዋሻው አቀናሁ.... ቅዱስ ያሬድ  የተሰወረበትን ዋሻ ተመልክቸ   ....... 13 ስአታት ቆይታ በኋላ ምሽት  11:30  ላይ ብዙሃኑ ሊያዮት የሚመኙትን የሰውራኑ መኖርያ የድንቅ ተፈጥሮ መገኛ ቅዱስ ያሬድ ገዳም ደረስኩ.... ጎኔን አሳርፌ በሃሳብ እንቀዋለላለሁ ለሰው የማልነግረው አደራ የማላካፍለው ምስጢር....እንቅልፍ ሲጥለኝ ከወዲያ በኩል በዜማ .. አሠርገዋ ለኢትዮጵያ ፤ በስብሐት ወበሃሌ ሉያ ፤ ያሬድ ካህን ፀሐያ ፤ አስተካልሐ በቅዳሴ ፤ በዘሱራፌል አርአያ ፤ ያሬድ ካህን ፀሐያ ፤ ለበግዕ በትንሣኤሁ ፤ ደመ ጥብሑ አርወያ ፤ ያሬድ ካህን ፀሐያ ፤ በመኃልይሁ አቅነያ .....እያሉ የሚያዜሙ ሊቃውንት ድምጽ  ቀሰቀሰኝ.... በትራሴ ካደረኳት ሻንጣየን ከኪሷ መዝዠ የተጻፈችውን የተጠቀለለች ወረቀት ተመለከትኩ..... "ለሁሉም ጊዜ አለው በደም የተገነባው ንግስና  በ ባርነት ይጠናቀቃል፤ ልቡ የደነደነች  ፈርኦን ቀኝ እጂ ትሰላለች፤ አቅም ያጣ ሽባ ሁኖ ይዋረዳል በወንድሙም ይገደላል፤ ማቅ የለበሰች ገላ እንደ ሃጫ በርዶ ትነጻለች።   የተመረጡት እስኪ ስቱ ዘመኑ ቢከፋም ጨለማው ቢረዝም፣ እረኞች በጎቻቸውን ለ ተኩላ ቢሰጡ እንኳ ቀኖቹ እንደ ደረሱ እወቅ! ከ ደጀን አንባ ፀሐይ ይወጣል ..ሙቀት ያለው የማያቃጥል ፤ብርሃን ያለው የማይጨልም ፀሐይ  ..ፀሐዩ ለተመረጡት ያበራላቸዋል ለግፉአን ይጨልማል ...   ግን ለወሊሃ እዘኑ ለርብ'ም አልቅሱ! ''ትላለች ከ ተደላደልኩበት ከሞቀ ቤቴ ቅጀ'ት የመሰለ የ ራስ ደጀን ጉዞየ  ተራ ህልም እንደሆነ አሰብኩ.....እስክነቃ ድረስ እንደ አቤሜሌክ እተኛ ዘንድ ወደድሁ፤ ያየሁትን ህልም 'ህልም እልም'  ብየ  ፀሐይዋ ወጥታ ከእንቅልፌ እስክነቃ ተኛሁ......

በህልሜ ይመስለኛል..... በሰሜን ተራሮች በአንዱ ፣የሚስጥሩ አንባ ማህጸነ ደብረ ደደክ   ......ወ አመሳለ ሲና ራስ ደጀን አቀናሁ! ተፈጥሮው ድንቅ፣ ውበቱ ግሩም፣ ከሰማዮ ጋር የሚያወጉ ተራሮች ይታያሉ   ፤ከሸማኔ ጥበብ በላይ   ተፈጥሮ ራሱን  እንዴት ባለ ጥበብ ሸምኖ ያለብሳል ? የትኛው ጠቢብ እስትንፋስን አላብሶ እንዲህ እፁብ ድንድ አድርጎ ይፈጥራል ?    ራስ ደጀን ለ1500 ዓመታት በላይ የስውሩየቅዱስ ያሬድ መኖርያ  ሚስጥራዊው የአፍሪካ ጣሪያ ፤ ምድር የታመቀውን አየሯን ማስተንፈሻው አንዱ ይህ ራስ ደጀን ሲሆን  ሌላው ሜዲትራንያን ስር ... ያልተገለጠ እውነት ያልተነገረ ምስጢር ....አለ! የአፋሩ ኤርታሌ የበርባኖስ የሰሜኑ ራስ ደጀን የብሄረ ህያዋን የጎጃሙ ግዮን የገነት ትይዮ ናቸው.... ይህ ማለት ባህሪያቸውን የሚወራረሱ፣  ረቂቅ ሚስጥርን  የሚቃመሱ ፣ የ ሰማይ እና የምድር  ትይዮ ሀይል  የሚካፈሉበት ፣ድንቅ ተፈጥሮአዊ ኮድ ያላቸው ናቸው... አበ ቴውድሮስ  ወ ውሉደ  ኢትዮጵያ  ...ወደ ራስ ደጀን ሰሞኑን አቅንች አለሁ...እጂግ አድካሚ አንዲሁም አስደማሚ ከምድረ በዳ ላይ የሚያውድ የእጣን ጢስ ያሸተቱኩበት፤ ገቢረ ታምራቱ በተፈጥሮ ለዛ በግልጽ የሚታይበት ፤ ድምጻቸው ብቻ የሚሰሙ ስውራን  ሰወችን የሚያነጋግሩበት፤ ድምጻቸው እንጂ ፊታቸው ፈጽሞ ማየት የማያቻል   ወደ ቦታው ለሚያቀና  ለጨነቀው መጽናኛን፤ ለደከመው ረፍትን  ለህሙማን ፈውስን የሚያመጡ፤ ጸሎት ልመናቸው የሚደርስ ሃብተ ትንቢት የሞላባቸው ስውራን ....ከ ለሊቱ 9 ስአት የተጀመረ የእግር ጉዞ የሰሜን ተራሮችን በብረድና ቁር አቀበትና ቁልቁለት ከ 4600 ሜትሮች በላይ ከፍታን እየወጣሁ እጓዛለሁ  እወጣ እወርዳለሁ ....  ቅዱስ ያሬድ ያስተማረበት ሆጮው፤ ከየት መጣ የማይባል የ እጣኑ ሽታ የሚያውድበት  ፤ያሬድ በበትረ ሙሴው ያፈለቀውን  ጸበል አልፌ.... በስውራን  አባቶች  የተባረከን ቡራኬ አግኝቸ ..ከ መናንያን ጋር ልነጋገር ከስውራኑ ጋ በረከት ልካፈል ወደድኩ....ከቆላና ደጋ የተሰባሰበው ሰው ቀጭኗን መንድ ዘጋግተወ መተላለፊያ እስካጣ ድረስ መድረሻ አጣሁ..... እንደ ግማሽ ጎን ገበቴ የሚመስል ተራራ  ላይ የሚገኙትን መናንያን አግኝቸ የልቤን እጠይቃቸው ዘንድ ወደድሁ  ... ከድካሙ አንጻር የሚንቀጠቀጡ  እግሮቸን ዘርግቸ ከጋራው ላይ ተደግፌ ገደም አልኩ ... ወደ ሰማዩ አንጋጥጨ .... ያሬድ ያሬድ ያሬድ አደራየን እበላ ዘንድ ተውከኝ እላለሁ....የደብረ ደደኩ ምሲጥር ይፈታልኝ ዘንድ ደጂህ የቆምኩትን ከርታታ ስለምንስ ተውከው?  ከ ደገኞች ደብረ ጻድቃን  ዘር የሚወጣው ውሉደ ደደክ የት ነው ያለው?  አንተ ያሬድ  እውነትን ያውቅ ዘንድ ከ ራስ ደጀን እስከ ግዮን የተንከራተተው ጎስቋላ አደራየን እወጣ ዘንድ አትረዳኝም እላኣለሁ...ስውራኑን አገኝ ዘንድ ተመኘሁ ግን አልቻለኩም...አንገቴን አቀርቅሬ ቁልቁል ወደ ሸለቆው ልወርድ ስነሳ የያዝኩትን  ጸበል ለማገዝ መንገድ ላይ የተቀበለኝ ከዛም የተጠፋፋነው  ህጻን  ልጂ  ከ ጸበሉ ጋር በፌስታስ የታሰረች ወረቀትን አቃብሎኝ ከህዝቡ መሃል ገብቶ ተሰወረ.....መንገድ  ባናወዘው እግሮች ቁልቁል ወደ ዋሻው አቀናሁ.... ቅዱስ ያሬድ  የተሰወረበትን ዋሻ ተመልክቸ   ....... 13 ስአታት ቆይታ በኋላ ምሽት  11:30  ላይ ብዙሃኑ ሊያዮት የሚመኙትን የሰውራኑ መኖርያ የድንቅ ተፈጥሮ መገኛ ቅዱስ ያሬድ ገዳም ደረስኩ.... ጎኔን አሳርፌ በሃሳብ እንቀዋለላለሁ ለሰው የማልነግረው አደራ የማላካፍለው ምስጢር....እንቅልፍ ሲጥለኝ ከወዲያ በኩል በዜማ .. አሠርገዋ ለኢትዮጵያ ፤ በስብሐት ወበሃሌ ሉያ ፤ ያሬድ ካህን ፀሐያ ፤ አስተካልሐ በቅዳሴ ፤ በዘሱራፌል አርአያ ፤ ያሬድ ካህን ፀሐያ ፤ ለበግዕ በትንሣኤሁ ፤ ደመ ጥብሑ አርወያ ፤ ያሬድ ካህን ፀሐያ ፤ በመኃልይሁ አቅነያ .....እያሉ የሚያዜሙ ሊቃውንት ድምጽ  ቀሰቀሰኝ.... በትራሴ ካደረኳት ሻንጣየን ከኪሷ መዝዠ የተጻፈችውን የተጠቀለለች ወረቀት ተመለከትኩ..... "ለሁሉም ጊዜ አለው በደም የተገነባው ንግስና  በ ባርነት ይጠናቀቃል፤ ልቡ የደነደነች  ፈርኦን ቀኝ እጂ ትሰላለች፤ አቅም ያጣ ሽባ ሁኖ ይዋረዳል በወንድሙም ይገደላል፤ ማቅ የለበሰች ገላ እንደ ሃጫ በርዶ ትነጻለች።   የተመረጡት እስኪ ስቱ ዘመኑ ቢከፋም ጨለማው ቢረዝም፣ እረኞች በጎቻቸውን ለ ተኩላ ቢሰጡ እንኳ ቀኖቹ እንደ ደረሱ እወቅ! ከ ደጀን አንባ ፀሐይ ይወጣል ..ሙቀት ያለው የማያቃጥል ፤ብርሃን ያለው የማይጨልም ፀሐይ  ..ፀሐዩ ለተመረጡት ያበራላቸዋል ለግፉአን ይጨልማል ...   ግን ለወሊሃ እዘኑ ለርብ'ም አልቅሱ! ''ትላለች ከ ተደላደልኩበት ከሞቀ ቤቴ ቅጀ'ት የመሰለ የ ራስ ደጀን ጉዞየ  ተራ ህልም እንደሆነ አሰብኩ.....እስክነቃ ድረስ እንደ አቤሜሌክ እተኛ ዘንድ ወደድሁ፤ ያየሁትን ህልም 'ህልም እልም'  ብየ  ፀሐይዋ ወጥታ ከእንቅልፌ እስክነቃ ተኛሁ......

በቀደም እለት እግሬ ወደ አመራኝ ቦታ በድንገት ከቤቴ ተንስቸ መጓዝ ጀምርሁ....ሰው ወደ ለለበት፣ ድምጽ ወደ ማይሰማበት፣ ሁካታ ጠብ ክርክር  ንትርክ ወደ ማልሰማበት ወፌ ወደ መራችኝ ... ስለ እውነት ግን ደክሞኝ ነው.... መኖር ያደክማል አይደል? እልፍ መከራ መስማቱ ፣  የተጨነቀች ነብስ ብኩን የሆነችን ስጋ ማየቱ፣ ተስፋ የሌለውን ተስፈኛን መመልከቱ፣  ...ምህረት የማያመጣው ጸሎታችን.. የማያርግ መስውእታችን... የማን'ባረክበት ብኩርናችን .. ...ነጻ የማያወጣን ትምህርታችን...እያሰብኩ የኢትዮጵያ  የነጻነት ቀንዲሉ የሚለኮስበት ቀን አንገት የደፋችው አገር የምትቃናበት ጊዜ የደፈረሰው የሚጠራበት .... ጊዜ ይኖር ይሆን? እላለሁ ..በጠቆረው ዝናባማ ደመና ፣በሚያካፋ የዝናብ ነጠብጣብ፣ ጨርቁን ጥሎ እንደ አበደ ሰው የለበስኩት ፎጦ እየጎተትኩ ...ጯክ ብየ በ ምድረበዳ አወራለሁ .. እላለሁ ... 'የለህም እንዳልል ይመሻል ይነጋል        አለህም እንዳልል እንዲህ ይደረጋል'       እላለሁ.. ተስፋ የተሰጠን ተስፋችን  የት ሄደ? እላለሁ የማይነጋ ለሊት  ስንጠብቅ ...እንኖር ዘንድ ተውከን እላለሁ...ነጠብጣቡ ወደ ዶፍ ዝናብ ተቀይሮ መዝነብ ጀመረ... ከመምህሬ አድባር ዛፍ  ስር ከመሰለ ከወዲያ ማዶ ከ ገደሉ ጫፍ ከተንዘራፋው ዋርካ ጭራቸውን የሚያወዛውዙ ሰው ይታዮኛል.....ና ወዲህ ተጠለል በሚመስል ምልክት እየጠሩኝ... ወደ ዋርካው  ተጠጋሁ ...በል ከዚህ ይሻልሃል ሰላም ሁን ብለው ሲሰናበቱኝ ...መባርቅቱ በበዛበት ብልጭ ልጭታው በጸናበት ስአት የት ሊሄዱ ነው? አልኩ እና መመርኮዣ ዘንጋቸውን ያዝ አደረኩ.... ልጀ ሆይ የሰማይ ምሰሶዋ  ለቋል፤ የምድርም መሰርቷ ተናውጿል.... አመጸኛ በዝቷል   ሃጥያት ተንሳራፍቷል     የማያልፈው ዝናብ ከ ሚመታኝ የሚልፈው ዝናብ ያርጥበኝ ... ልጀ ሆይ ሰማዮን እንዳታየው ማን አይንህን ጋረደህ ? ልቡናህ እንዳያስተውል ማን አዚም አደረገብህ....?   እኔስ በቀን መሽቶብኛል፣ ከዚህ የባሰው ውሽንፍር ሳይመጣ   ወደ ማደርያየ ልገስግስ...አንተ ግን ሰው ሁን! ቀጠሉ..  አመጸናል እና ! ምን አልባት እንደ ኖህ ዘመን  ዛፉ ተቆርጦ ጉቶ እስኪ ቀር ይቆረጣል... መኪና ወዳልገባበት መንገድ ወደ ሌላለበት ልጓዝ .....እንደ ርብ ከመሆን ወሊሃንም ከመምሰል ግን ይሰውረን ልጀ ልብህ ከፈቀደ አንተም ሳይመሽ ተከተለኝ ..... ለጠቢብ አሃቲ ቃል ትብቁእ ! ለጥበበኛ ሰው አንድ ቃል ትበቃዋለች !         

ምናልባት የዘመን ጫፍ ላይ ነን ምናልባትም ጽዋው እየሞላ ይሆናል ምናልባት....ጊዜው ደረሶ ይሆናል ! ምናልባት ምናልባት ምናልባት ዛፉ ሊቆረጥ ጉቶው ሊቀር ነው...... ነፋሱን አይቸ የጠፏን ጨረቃ ተመልክቸ አመሻሸን በጹሑፍ እመለስ ይሆናል!

The secret of zion chalice የጽዮናዊዝም ጸዋ ማህበር ሚስጥር! ፍለጋ አያልቅም የሰው ልጂ ከ ስጋዊ ምኞትና ፍላጎት በዘለለ ለሚኖረበት ጽኑ  አላማና  እውነተኛ ማንነትን  በጥብቅ የመፈለግ የማሰስ የመጠየቅ የመ'መራመር ባህሪ ሊላበስ ይገባዋል። እንደ እድል ሁኖ የተፈጠርንባት ምድር በአንጡረ ሀብቷ ወደር የማይገኝላት ተፈልጎ እና ታስሶ የማያልቅ  እጂግ ጥንታዊ ማንነት ያላት ፤ የተለየች ምድር ነች ኢትዮጵያ። እንደ መረገም ሆኖ የመጣንባቸው መንገዶች ደካማ የፖለቲካ  አመራሮቻችን እንዲሁም የሃይማኖት አባቶቻችን ቸልተኝነት ብዙ ዋጋ ቢያስከፍልም  ያረፈደብን የማንነት ፍለጋወች ግን ዛሬም ከተዳፈኑበት የሚገልጣቸውን ይፈልጋሉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ የ አለምን ታላላቅ ሚስጥራት ዶሴን በመሰብሰብ፣ በማጥናት፣ እንዲሁም በረቀቀ መንገድ የራስ ለማድረግ በተለያየ ዘመን እጂግ ሚስጥራዊ የስለላ ድርጅቶች እና የጸዋ ማህበራት ተመስርተዋል። ከማህበራቱ ጥንክርና የተነሳ ለበርካታ መቶ አመታት ሰንሰለታቸው ሳይቋረጥ፣ ሚስጥራቸው ሳይገለጥ፣ ማንነታቸውም ይፋ ሳይወጣ፣ ዘመንን ያስረጁ፣ እጂግ ተጽኖ ፈጣሪ የስለላ ድርጅቶች ሆኑ የጸዋ ማህበራት ይገኛሉ። ዛሬም ድርስ ጓዳችን የምትፈጸም እያንዳንዷን የሀገር ህልውና በቀላሉ ለማወቅ እጂግ ሚስጥራዊ በሆነ የስለላ መረብ ይጠቀማሉ ሀገራችን በዚህ ተንኮለ ከተጠለፈች ቆየች ። በተለይ የጽዋ ማህበራት አንዳንዶቹ እጂግ በረቀቀ መልኩ ከመከናወናቸው የተነሳ ህልውናቸው ያለ እስከማይመስል ድረስ ህቡዕ ናቸው። ሚስጥራቸውም ከማህበራቸው የሚወጣው ከማህበሩ በድንገት አፈንግጦ የወጣ በሌሎች ማህበራት የተሰለበ ሰው ሲኖር ብቻ ነው ። ከእኒህ ሚስጥራዊ የጽዋ ማህበራት አንዱ እና ዋናው የጽዮን የጽዋ ማህበራት ነው። ጸዮናዊነት በሂብሪው እየሩሳሌም የሚል ትርጉም ሲኖረው ይህም ግንደ ቃሉ የተወረሰው ከመጻህፍ ቅዱስ ነው። ይህ ሃይማኖታዊነቱ የገነነ፣ በፖለቲካውም ስር የሰደደ፣ እንቅስቃሴ በዘመናዊ መልክ በ19 ኛው ክፈለ ዘመን ቢቋቋምም ለበርካታ መቶ አመታት ከጀርባው ሚስጥራዊ እንቅስቃሴወችን ሲያከናውን የኖረ ማህበር ነው። አሁን አሁን ይህንን ጽዮናዊነት መጠሪያ አለም እንዲረዳው የተደረገው በቋሚነት እስራኤላውያንን እንደ አሽዋ ከተበተኑበት አህጉራት ወደ አገራቸው ለመሰበሰብ የተቋቋመ ታላቅ ዝና ያለው ማህበር እንደሆነ ብቻ ነው። ነገር ግን ይህ የጽዋ ማህበር እንደ አውሮፖ የዘመን ስሌት በ 1099 ወይም 11ኛው መቶ ክ/ዘመን በ አውሮፓ የተበተኑት ሊቃውነት በሚስጥር ተሰባስበው የመሰረተቱ የጽዮን ቤተ እምነት የተሰኘው ሃይማኖታዊ ተቋም በገሃዱ አለም የሚገኝ ሚስጥራዊ የሆነ ድርጂት ነው። በ1975 በፖሪስ ብሄራዊ ቤተ መዛግብት (ቢብልዮቴክ ናስዮናስ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው ና ሚስጥራዊው ሰነድ( ሌ ዶስዮ ስክሬ) ተብሎ የሚታወቀው የብራና ጽሁፍ እንደ ሰረ አይዛክ ኒውተን፣ ሳንድሮ ቦቲቼሊ፣ ቪክቶር ሂዩጎ፣ እና ገናናው ሊኦናርዶ ዳ ቬንች፣ ያሉ በርካታ በርካታ የጽዮን ቤተ እምነት አባላትን ስም ይፍ አድርጓል። እኒህ አለም ላይ በዘመናቸው ገናና የነበሩ ሰወች ከተመሰረተበት ከ1099 እስከ 21ኛው ክ/ዘመን በተለያየ ዘመናት ተጽኖ ፈጣርያን ግለ ሰቦች የሆኑ የሚስጥሩ የጽዮን ማህበር መሪወችም ነበሩ። ይህ ማህበር ለ900አመታት አካባቢ ሚስጥሩ እንደ ተጠበቀ፣ ህቡዕ እንቅስቃሴው እንደ ቀጠል ፣ አለም ላይ የነበሩ ሚስጥራዊ ኩነትና ታቦተ ጽዮንን ጨምር የቅዲስ ጽዋውን ቅርሶችን እንቅስቃሴወችን ሲመረምሩ ለመውሰድም ሲጥሩ እና ፍላጎታቸውን በስውር ሲያስፈጸሙ ኑረዋል። ይህ ህቡዕ ድረጂት ሚስጥሩ በፖሪሱ ቢብልዮቴክ ናስዮናል ሚስጥራዊ ሰንድ እስከተጋለጠ ድረስ በርካታ እንቅስቃሴወቹን ከውኗል። የእስራኤሉ የስለላ ድረጂት ሞሳድ ን ጨምሮ የጽዮን ፕሮቶኮሎች ከፍተኛ የመንግስት አካላት ና ፖለቲከኞች ጭምር ያሉበት አይሁዳውያኑ ስብስብ ወደ ፊት ክርስቶስ ይወለዳል በሚል አሁን በቅረብ የሰሎሞን ቤተ መቅደስን ገንበተው የሰሎምንን ታቦት የጽዮንን ጽላት ይጠባበቃሉ። በእርግጥ የሌዋዊው ሙሴ ጽዮን፣ የሰሎሞን መጽናኛ ታቦተ ጽዮን፣ ከ እስራኤም ምድር ወደ ኢትዮጵያ ከመጣች እንሆ ሶስት ሺ አመታትን ስላስቆጠረች በረከት ከ እስራኤል ምድር ጸጋም ከእየሩሳሌም ተነስቷል...ወደ ሀገሯ ትመለስ ዘንድ የቅዱስ ሰሎሞን ምኞቱም ነበረች! በሰሎሞን ስረወ መንግስት ከመነበሯ የተነሳችውን ጸዮን ወደ ፊት ይወለዳል በሚሉት በመሲሁ ኢየሱስ ትመለሳለች ብለው በቀቢጸ ተስፋ ቤተመቅደሱን አንጸው ጽዮንን ከመነበሯ ኢየሱስን ከዙፋኑ እስኪ መጡ ይጠበቃሉ። ይህ ታቦተ ጽዮንን ከ ኢትዮጵያ ለመውስድ በተለያዩ አዝማናት ቢሞከርም ከመንበሯ ትነሳ ዘንድ ፈቃደ እግዚአብሔር አይደለምና ፈጽሞ ሊያገኟት አልተቻላቸውም። በተለይ እስራኤል ከተበታተነችበት አገግማ በ1948 እንደ ሃገር ከተመሰረተች ወዲህ የጽዮን ጽዋ ማህበር ጨምሮ ሞሳድና የተለያዩ ሚስጥራዊ ተቋማት እንደ ኦፐስ ዴይ ያሉ የቫቲካን የካቶሊክ ሚስጥራዊ ማህበር እምነትን ከመመረዝ አንስቶ ታቦተ ጽዮንን ለመውስድ ቢታሰብም ታቦተ ጽዮን የነበረችበት፣ ያለችበት፣ ወደ ፊትም የምትኖርበት፣ ሁኔታ እጂግ መግነጢሳዊ ሃይሏ በጊዜ የሚገለጥ ሚስጥር ነው እንዳሉት አበው ተሰውራባቸዋለች። እንዲሁም በዚህ ዘመኝ በረካታ ሚስጥራዊ እቃወችን እንዲሁም የአዳምን ኤዶም ''ቅዱሱን ምድር '' ለመውረስ ይሞክራሉ.. .. ግን አይችሉም ። ይህ የታቦተ ጽዮን ሁነት ለሁለት ሶስት ሽ አመታት ለኢትዮጵያ ፈተና የሆነባት ነገር ቢሆንም አሁን ላይ አላማና ግቡ ተጠምዞ የፖለቲካ አሰላለፉ ተቀይሮ ኢትዮጵያ ለሽ ዘመናት ያጸናትን የወጠራትን ጂማት ለመበጣጠስ እጂግ አሳዘኝ በሆነ ሴራ ተጠልፋለች። ባልተፈጠርኩ የሚያስብለውን ይህን እለት ይህን ዘመን ይህ ክስተት ሀገሪቱን ሊያፈርስ ህዝቦቿን ሊያጠፋ የመጣብን ውስብስብ ሴራ በእውኑ ያልፍልን? ይህ ፈለገ ጥበባት ነው ያላችሁን ሃሳብ አስተያየት @Nabuti21 ላይ አድረሱኝ።

መቸስ የዝች አገር ሃብት ተዝቆ አያልቅ በአለም ታላላቅ ከተሞች በሚስጥር ስለ ሚጠበቁ የኢትዮጵያውያን ቅርሶች ምይ ያክል ታውቁ ይሆን........ ከደቂቃወች በኋላ አስደናቂ ማብራርያየን ይዠ እመጣለሁ.......

እናንተ ኦርቶዶክሳውያን ሸር በማድረግ  የቤተክርስቲያኒቱን ልዕልና ከፍ የሚያደርጉ ትንታኔወች በሚገባ የሚገልጡ ስራወች በዚህው ገጽ የሚቀርቡ ሲሆን በቅንነት ለ ምዕመናኑ ሸር በማድረግ አጋሩ ። ይህ ገጽ የመከፈቱ አላማም እያየናት ያላስተዋልናት፤ እየሰማናት ያላዳመጥናት፤ በገዝፍቷ ብቻ የምንለካት፣ ረቂቅነቷ ያልገባን፣ ቅድስት ቤተክርስትያንን በጥቂቶች ብቻ ከሚታወቀው የህቡዕነት ማንነት ህልውና  አካልና ግዝፈት ሰጥተን በምዕመኑ አእምሮ  ወደ ምትዳሰስ ምልኡነት መግለጥ ነው። ወንጌሉን ሊቃውንቱ ያስተምሩናል ለነብስም ለስጋም የሚበጁ የቤተክርስቲያን የትም የማይገኝ  ሀብታቷ እና ጥበቦን እኛው በምንችልው መንገድ ደግሞ ፈጣሪ በፈቀደ  እንገልጣለን ። ስለዚህ ወደ አንባብያን ያለ ንፉግነት የማቃብላችሁን እውቀት ፣ያለ ስስት አጋሩ ፣በመተባብር አብሮ በመቆም በተመጋጋዝ  በቅንነት አብረን ከተጓዝን የማንገልጠው እውቀት የማንፈታው ሚስጥር የማንሻገረው ውጣ ወርድ የለም! ..... ይህ ፈለገ ጥበባትነው ነው ሃሳብ አስተያየት ካለ @Nabuti21 ማድረስ ይቻላል!

ከደቂቃወች በኋላ ...... ''በሬሳ ሳጥን የመጣው ሰው በታምር ተነስቶ ሲሄድ አየሁት፤ ይህ ቦታ በ ስውራን ነው ቅዳሴ የሚቀደስበት '' የገዳሙ አገልጋይ ምስክርነትን ከሰሜን ተራሮች አንባ ከምትገኝ ድንቅ ቦታ ተገኝቸ ይዠላችሁ እቀርባለሁ.......

ር የሚመጣ አንዳችም ጥበብ ሆነ እውነት የለም። በአንድ ዘመን የተገለጠው በሌላኛው ጊዜ ስወር ይሆናል በዘመን ውስጥ መታሰር ሆነ መፈታት አለ። ከጊዜ መቅደምመ ሆነ መዘግየትም ዋጋ ያስከፍላል በጊዜ ከመዘግየት ይልቅ ግን ከጊዜ መቅደም ይሻላል። ለዛ ነው የዛሬቱ ኢትዮጵያ ከ ጊዜ መዘግየቷ ይህንን ሁሉ ዋጋ ሚያስከፍላት። እኒህ መነኩሴ የተናገሩት ነገር ጥልቅ መልዕክት ያለው የሂወት ዘመን ስንቄ ሊሆን ይቻላል። መነኩሴው ልክ ናቸው ሁሉም በተወሳሰበ ሚስጥር የተገነባ እንጂ በዘፈቀደ የተመሰረተ አይደለም። ፍጻሜ የሚመስሉን ነገሮች እልፍ መንታ መንገዶችን ይወልዳሉ። ቢሆንም ግን እውነትና እውቀትን ታላቋን ጥበብ መፈለጌ የሂወት ዘመን ስንቄ ነው። ከኖራ መደብ ላይ እንደተቀመጥኩ ጎጆዋን በአይኖቸ አስሳለሁ ወደ ተደረደሩት መጻህፍት ተጠግቸ በትኩረት ስመለከት፤ ስለ መጻህፍት የሚገልጽ የገጽ ሽፋን ባለመኖራቸው የውስጡን ቀለም አይተው አንበበው ካአልተረዱ ምንነቱን ለማወቅ ይዘቱን ለመረዳት አዳጋች ነው። የተወሰኑትን እያነሳሁ እመለከት ጀመር ከዚህ በፊት የማላውቃቸው ያልተለመዱ መጻህፍት ናቸው። ስለ ስነ ፍጥረታት፣ ፕላኔቶች፣ ስለ እጽዋቶች ፣ እሳት ስለ ሚተፉ ድንቅ ፍጥረታት፣ ብረትን ስለሚያቀልጡ ማዕድናት ፣ ስለ ዘረ መል፣ መርበበተ ሰሎሞን( ዲያቢሎስን በመረብ የመያዝ ጥበብ)፣ ስለ አለማት ክፍል ፣ስለ ዘመናት አቆጣጠር፣ስለ ከዋክብቶች.. የተለያዩ ይዘት ያላቸው መጻህፍትን በግርምት ተመለከትኩ። እንዴት ከአንድ ግለሰብ ቤት እኒህን የመሳሰሉ ድንቅ መጻህፍት ሊገኘ እንደቻሉ ግራ ገባኝ ። በድንቅ መገረም ውስጥ ሁኞ የእነሱ እና የእኛ አለመገናኘት የፈጠረው ትልቅ የታሪክ ክፍተት መኖሩን ተረዳሁ ይህ ክፍተት ደግሞ እንደ አገር የዉድቀታችን ምክኒያት ሁኗል። አለም ተመራምሮ ያልደረሰባቸው እንቆቅልሾችን የሚፈቱ መጻህፍት እንደ ዘበት በየ ጎጆው ቤት ተወሽቀው ተረካቢ ጠፍቶ ሚገልጣቸው አጠው የሸረሪት ድር እያደራባቸው ያረጃሉ ። ስለ መጻህፍቱ እያሰብኩ ከመደርደሪያው ስር ያየሁት ነገር ትኩረቴን ሳበኝ እና ከተቀመጥኩበት በዝግታ ተነሳሁ። አራት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ነገር ትኩረት እንዳይስብ ተደርጎ በአረጀ ጥቁር ፍጦ ተጠቅልሎ ተቀምጧል። ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት አልተቻለኝም የሰውን ዕቃ ያለፈቃድ መንካትም አላስፈላጊ ነው። ሐምራዊ ቀለም የለበሰችው ፀሐይ ሮዝ ቀለም ካለው የኮክ ዛፍ ስታርፍ አካባቢውን ሙሉ በሙሉ የተለየ ገጽታ አልብሳዋለች። በበርካታ የዛፍ እና የእጽዋት እንክብካቤ የማትታማው ቅድስት ቤተክርስትያን በዚሁ ገዳም ውስጥም በርካታ ዛፎች ይገኛሉ። በተለይ እስከ ስምንት ሜትር የሚረዝመው የኮክ ዛፍ በሰፊና በተበታተኑ ሮዝ ቅጠሎቹ ለገዳሙ ሞገስን አልብሰውታል ። ፀሐይዋ ወደ ማደሪያዋ እየገባች ትገኛለች ቅዝቃዜን ያዘለ ነፍስ ከ ሚፈሰው ወንዝ ከበስተ ደቡብ በኩል የሚመጣው እርጥበቱን እያራገፈ በየ ዛፎች ይወሸቃል የቅጠሎችንም ሰለም ያውካል ለእኔ ግን ፍጹም ሰላምን ለግሶኛል። ከጎጆዋ መግቢያ በር በስተቀኝ ለመቀመጫ የምታገለግል የባህር ድንጋይ ላይ ተቀምጨ ቀዝቃዛውን ነፋስ እምጋለሁ። ቢጫ ፎጣ የለበሰ በገዳሙ ስርአት የአሞክሮ ቆብ የለበሰ ለመመንኮስ የፈተና ጊዜ የተሰጠው ልጂ እግር አባ አባ እያለ እየተጣራ ወደ እኔ ተጠጋ እንደምን ዋሉ አለኝ ለየት ባለ የአነጋገር ዘየ ይመስገን ፈጣሪ አልኩ '' አባ ወየት ሂዲው ነው የሉም ወይ''? የት እንደሄዱ አላውቅም ቅድም ነው የወጡት። ''ከደጀ ሰላሙ መቁነን ሳይወስዱ ሲቀሩ እኮ ምን ገጠማቸው ብጌ ነው መቁነናቸውን ይዠላቸው ወዲህ የመጣሁ '' መቁንን ማለት ለገዳማውያኑ የተመጠነ ምግብ ከደጀ ሰላሙ የሚሰጡት ዳቤ ነው። ''አንቱ አለኝ ለመነኩሴው የመጣላቸውን ምግብ እንዳስቀምጥ እያቀበለኝ። ''እንግዳ ነወት መሰል እኔም መቸ እንግዳ ያለ መስሎኝ ይበሉ ለእርስውም ይዠ መጣሁ '' በጥቅጥቁ ዛፍ እየተሽሎከሎከ ወደ መመገቢያ ቤቱ ነጎዶ..። ምን አይነት ራስን የመግዛት ችሎታ ቢኖር ነው ይህን የመሰለ ለጋ ልጂ ለመመንኮስ የአሞክሮ ቆብና መቁጠርያ ተሸክሞ በጉብዝናው ወራት እግዚአብሄርን ያስቀደመ። የዛሬው ዕለት እንደ ትላንቱ ዝናባማ አይደለም በስሱ በደመና የተጀቦነችው ጨረቃ ብርሃኗን አልነፈገችንም። ከተወሰን ደቂቃ በኋላ መነኩሴው ከእጃቸው አቧራ እያራገፉ አንቱ እንዳይሉኝ ስለነገረኳቸው ወፈር ባለ ልሳን ''እንደምን አመሸህ እንዴው ስራ እኮ ብዝቶብኝ እንግዳየን በሚገባ ባለማስተናገዴ ይቅርታ ይደረግልኝ'' አሉ በፈገግታ በታጀበ አነጋገር ። ምንም ችግር የለውም ያው አንዳንድ ነገሮችን ሳነብ ስመለከት ዋልኩ መነኩሴው ቀጠሉና ድንቅ ድንቅ ጥሩ ስራ ይዝህ ወልሃሏ..የእጃቸውን አቧራ ሳያራግፉ ወደ ጎጆቸው ገቡና የሆነ ነገር ላይ አተኮሩ.. በትንሹ የታመነ በብዙ ይሾማል አሉኝ በቀልድ መሰል አነጋገር። ምን ለማለት እንደፈለጉ ባይገባኛም የገባኝ ይመስል አንገቴን ልክ ንወት በሚል እንቅስቃሴ ገለጽኩላቸው። ጸሎት ካደረጉ በኋላ የመጣልንን ዳቤ አቅረበው ተመገብን። መጻህፍቶች ላይ ስላየዋቸው ውስብስ የአሳሳል ስነ ዘዴወች ፤መልዕክትን በህቡዕ በመከተብ ሰወች በቀላሉ እንዳይረዷቸው በኮዲንግ የአጻጻፍ ስነ ዘዴወች የተጻፉ እኒህ ሁሉ መጻህፍት መች ነበር የተጻፉት የሚል ጥያቄ አቀርብኩላቸው። መጻህፍቱን እየተመለከቱ በእርግጥ አብዛኛወቹ ከአያሌ ምዕተ ዓመታት በፊት ነበር የተጻፉት ፤የብዙሃኑ ጸሐፊ ማንነት በውል አይታወቅም፤ ንብረትነቱ የቤተክርስትያኗ ነው ብለው ስለሚያምኑ ስማቸውን አያሰፍሩትም። ከ ጎጆዋ በር ላይ ካሉት የባህር አለቶች ላይ ተቀምጠን ጋንብራ በሚባል የቅል ኩባያ ሞልተው ከሱፍ የተዘጋጀወን ጭልቃ አቀረቡልኝ። ከቅድሙ በተሻለ መልኩ የተጀቦነው ደመና ከ ጨረቃዋ ገለል ብሎላታል ። አልፎ አልፎ ብልጭ ብልጭ የሚሉ ከዋክብቶች በሰማይ ላይ ይታያሉ። ከወንዙ የሚነሳ ቀዝቃዛው ነፋስ በዛፎቹ እየሾለከ በረከቱን ያደርሰናል። እኔም ትኩርት እንደሰጡኝ ስረዳ ታድያ ለምን ይሆን እንዲህ የተወሳሰበ ነገሮችን የሚወዱት? በሚስጥራዊ ኮድ የቆላለፉት ምክኒያት አልገባኝም? ዓመታትን የወሰዱ የጥንት ምርምሮች፣ ምትሃታዊ ተምሳሌቶቼ ፣እንግዳ ቃላትና የቤተሙከራ ግብአቶች ለምን አንብበን በቀላሉ እንድንረዳው እና ለሀገር ተገቢውን ጥቅም እንድናወለው አያደርጉትም ነበር? በተረጋጋ ሙህራዊ ሁነት ውስጥ በጽሞና ከሰሙኝ በኋላ ንግግራቸውን ቀጠሉ። ይህን የመረዳት ስልጣን የተሰጣቸው ሰወች ብቻ እንዲረዱት ነው የሚፈለገው። ማንኛውም ሰው ወርቅን በፈለገበት ስአት ቆፍሮ እንደልቡ ቢያገኘው ወርቁ እሴትነቱን ያጣና ከአፈር ይረክሳል የወርቅ ተፈላጊነቱ እንደ ልብ አለመገኘቱ ነው። ''ጠቢብ ሰው ከሚነግርህ ይልቅ ያልነገረህን አድምጠው'' ፤ ጥበብ እንዲሁ ናት ክብሯን ለሚጠብቅ ብልህ ሰው ብቻ ነው ራሷን የምትገልጥ። ጥበባዊ ዕውቀትን በጊዜው ብልሆቹ ኢትዮጵያውያን በሚገባ ተጠቀሙበት፤ ሀገራቸውን በአለም የወረቅ መንበር ላይ ለዘመናት አስቀምጠዋት አልፈዋል፤ ሃያላን ጠቢባን ተከባሪወች አለም የሚርድላቸው ልዕለ ሃያል አገርን መስረተውበት እስከነ ክብራቸው አልፈዋል። ያ ሃያልየት በአባቶችችን ድንቅ ጥበብ ይገለጥ ዘንድ አገራችን ሰወቿን ትፈልጋለች በተስፋም ትጠብቃቸዋለች። ያኔ ኢትዮጵያ ተነሳች ጥበብ ተገለጠች ይባላል...። ያ የሚሆነው ግን በስጋ ነፍስና መንፈስ ትበብር ነው....''ልብ በል አሉ መነኩሴው ጠቢብ ሰው ከሚነግርህ ይልቅ ያልነገረህን አድምጠው '' ለሁለተኛ ጊዜ ይህንን ቃል ደገሙልኝ..

ሆነ ፤የሚሰማውም፣ ድምጽ የሚያሰማውን ብቻ ከሆነ ፤በእውነት ይህ ህዝብ ያያል ወይስ ይሰማልን? ጽሞናችንን የሚያደምጥ ነግግራችንን ይሰማል፤ በዝምታችን ውስጥ ብዙ ሚስጥራትን እንናገራለን ፣ በከናፍሮቻችን እስክንገልጥላችሁ የምትጠብቁ ከሆን የልቦናችን ሚስጥር ፈጽሞ ልታውቁት አትችሉም። በልባችን ያሉትን ሚስጥራት ለማየት የሚችሉት በልቦናቸው ሚስጥሮችን የያዙ ብቻ ነው። አለም ላይ እንዳሉ የአለሙ ጠቢባን የኪሶቻችንን እየሰጠን የልባችሁን አንወስድባችሁም። ይሉቁንስ ለመሸከም ብቁ በሆናችሁበት ጊዜ ያለስስት የልባችንን እንሰጣችሁ አለን እንጂ። ጥበብ ሻማ ስር እንደተወሸቀች ክር ማለት ነች፤ ፈጽማ መገለጥም ሆነ ፈጽማ መሰወርን አትፈቅድም፤ ፈጽማ ከተሰወረች ለኩሶ የሚያበራትን ታጣለች፤ ፈጽማም ከተገለጠችም ሳትበራ ትጠፋለች። ለዚህም ነው ጥበብ ጅማሬዋ እንጂ ፍጻሜዋ አትገለጽም የሚባለው። ስለዚህ እውነትን ለማግኘት አንዳችን እንድንናገር ሌላችን እንድንረዳው ሲሆን ብቻ ነው። ታድያ ጥበብ ተገለጠች የሚባለው የተነገረው በሰሚው ልቦና ቦታ አግኝቶ ቃሉ ህያው ሲሆን ነው። አው እውነት ነው እውነትና ጥበብን ምንገልጠው ለራሳችን ብቻ ነው፤ ያልመረመርናቸው በርካታ ድንቅ እውነቶች ስላሉ፣ ፈልገን ባገኘናቸው ጊዜ የምንናገረው ለራሳችን ብቻ ነው። ግን ሁሌም በዝምታችን ውስጥ ጮክ ብለን ስንናገር በልባቸው የሚያዳምጡ ሰወች ያዳምጡናል። ታድያ ወዳጀ የእኛ አለመናገር ሳይሆን የሰወች የልቡና ጆሮ አለመከፈት ነው ፤ታድያ ለዚህ ተጠያቂው ማን ነው? ለመነኮሳት ጽሞናቸው ልብሳቸው ነው ፤ሰው እኮ የሚያወራው ከውስጡ ከራሱ ከህሊናው ጋር መስማማት ሳይችል ሲቀር ሰላምን ሲያጣ ነው። መነኮሳያቱ ደግሞ በልቦናቸው ጋ ካለው እግዜሩ ጋር ስለሚያወሩ በከናፍሮቻቸው የሚገለጥ ቃላት የላቸውም። ጽሞናቸው ለአይኖቻቸው ብርሃን ለልቦናቸው ደስታን ያጎናጽፏቸዋል። በርካታ መነኮሳት በውስጣቸው እውቀትን በልቦናቸው ጥበብን ቢይዙም በአደባባይ የማይገልጡት በኣፋ የማይናገሩት ምክኒያት የጥበብን ክብሯን ላለማሳጣት ነው''።....አሉና ከተቀመጡበት አርጩሜ አንገታቸውን ወደ ምድር ቀርቅረው ዝም አሉ.. እኔም ከንደበታቸው የሚወጣው ቃላት የልቦነየን ፍላጻ እየመታ ለጠየኩት ተጠያቂነት ምክኒያቱ ራሴው እንደሆንኩ ተረዳሁ.... አባ አልኮቸው ከአቀረቀሩበት ቀና እያሉ አቤት አሉኝ... ከትላንት ማታ ጀምሮ ያልጠበኩት ነገር ተከስቶ ነበር.. ዛሬ ማለዳ ያገኘኋቸው መነኩሴ ባልገባኝ ነገር ሌላ ጊዜ ከተመለሰሰክ ''ዛቲ ይእቲ መካንየ '' ይች ነች ቦታየ ብለው ወደ አቀጠቀጠች የወይን ተክል ጠቆሙኝ። በመገርም ስሜት ይመለከቱኛል ያልኳቸው መነኩሴ ነገሩ አዲስ ስላልሆነባቸው አንገታቸውን ነቅንቀው ዝም አሉኝ። እጂግ አስጨንቆነኛል አባ ገ/ሂወት የሚባሉ አጠር ያሉ መነኩሴ ያውቃሉ? ማን አልከኝ አሉ በመገረም ስሜት እኔም ቀጠልኩና አባ ገ/ሂወት... አጠር ያሉ ሙሉ ነጭ ጢም ከአስኬማቸው የተረፉ ጸጉራቸው ሉጫ የሆነ ... መጡ እንዴ? አሉ ማለቴ አሉ መነኩሴው የት አገኘሀቸው? ማለት እንዴት አሉና ለተወሰነ ጊዜ ዝምታ ነገሰ...ምነው ምነው ያውቋቸዋል አልኩ ነገሩን ለመስማት ካለኝ ጉጉት የተነሳ። አይ አይ አሉና የሚያውቁት ነገር እንዳለ ከሁኔታቸው ብረዳም ሊገልጡልኝ ፈቃዳቸው አለመሆኑን ተረዳሁ። የውይን ፍሬ ሃረግ ትርጉሙ ምን ይሆን አልኳቸው እኒህ መነኩሴ እውነትን ለመገለጽ ቢከብዳቸውም ከተቀመጡበት በዝግታ ተነስተው ወደ ተደረደሩት መጻህፍት አመሩ ረጂም ዘመናት ያስቆጠር የብራና መጻህፍ አውጥተው እያራገፉ ገልጠው ለጥያቄየ ድንገት መልሱን ካገኘህ ብለው ሰጡኝ ፣ ይህንን የጥንት ብራት ገልጨ በጽሞና ሳነብ ከተወሰነ ገጾች በኋላ በተለያየ ቀለማት የተሳሉ የተለያዪ እጽዋቶች ስምና ጥቅሞቻቸው እንዲሁም ውክልናቸው በስርአት ተቀምጠው ተመለከትኩ። ከ ተዘረዘሩት እጽዋቶች አንዱ የሆነውን የወይን ዛፍ ከድርብርብ ፍሬወቻቸው ጋር ተመለከትኩ ፤ ወክልናውን ስመለከት ፤ የዘር ልምላሜ፣ መለወጥ ፣ አንድነት ፤የሚሉ ትርጉሞችን ተመለከትኩ። ግራ እንደተጋባሁ ቀና ብየ ተመለከትኳቸው የራሴን አንድምታ ሳስቀምጥ... በእነዚህ ቃላት መሪ ቃልነት የተመሰረተ አንድ ስውር ማህበር ይኖርን የሚል ጥያቄ አቀረብኩላቸሰው....አንገታቸውን በመሰበቅ እንጃ አይነት ንግግር ተናገሩኝ። ይቅርታ አሁን ትንሽ ስራ ስላለብኝ ልሄድ ነው ማደርያ ካላገኘህ ከዚህው ታድራለህ ሰላም ዋል....አሉና ከ ጎጆዋ በር ላይ ቁመው ዞር አሉ.. በሂወትህ የሚያጋጥሙህን ሚስጥሮች በሙሉ ስትፈታቸው ፍችው ዞሮ ዞሮ የሂወት ሌላው ሚስጥር በመሆኑ ሞትን ያስናፍቃል እና ተጠንቀቅ! አሉኝ.. እየሆነ ያለው ነገር ግራ ገባኝ ይህ ነገር አጋጣሚ አይደለም። መጨረሻውን ካላወኩ በዘመኔ ሁሉ ያቅበዘብዘኛል። የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን አይሁን በሙከራየ ይረጋገጥ ብየ አሰብኩ፤ የመንኩሴው ንግግር ጠንከር ያለ ነው በእርግጥ በዚህ ጉዳይ ላይ እንድገባበት ባይፈልጉ ኑሮ ለምንስ ከተደረደሩት መጻህፍት አውጥተው ስለወይኑ ሃረግ ፍሬ ትርጓሜ እንድረዳ ፈለጉ? ስለምንስ በፍለጋየ ወቅት በምፈታው ሚስጥር የሌላ ሚስሮች በርን እነደሚከፍት እና ተስፋ እንዳልቆርጥ አስተነቀቁኝ?። ይህ ነገር አጋጣሚ አይደለም በዘፈቀደ የተገጣጠሙ ነገሮች ሊሆኑ አይችሉም። እሽ ይሁን በተጨነኩበት ሰወ አጥቸ በባዘንኩበት ስአት የአባ ገ/ሂወት መምጣት ፤ባልተለመደ አደገኛ በሆነ መንገድ ረጅሙን ጉዞ በአጭር ማጠናቀቅ ፤ለበርካታ አመታት ያልተከፈተ የተዘጋ ነው ከተባለው ጎጆ ቤት ውስጥ መገኘቴ ፤የአባ ገ/ሂወት በለሊት ድንገት መሰወር፤ የወይን ፍሬ ከትራሴ ላይ ማግኘቴ ፤የአረጋዊዉ መነኩሴ ''ዛዕቲ ይዕቲ መካንየ '' የወይን አትክልት እየጠቆሙ ያች ናት ቦታየ ያሉት ፤ ከ ጋራው ስር የተመለከትኩት የሸራ ላይ ስእል የተሰናሰለ ወይና ሀረግና እና ፈሬው....ይህ ሁሉ እንዴት ተራ ግጥ ጥሞሽ ነው ልበል? ከዚህ ቦታ በ ዘፈቀደ የሚሆነ አንዳችም ነገር የለም ነበር መነኩሴው ያሉኝ። ስለዚህ መዳረሻውን ባላወኩት መንገድ መቋጫው ባልተገለጠልኝ ውስብስብ ጉዞ የተዳፈነ ሚስጥር ዙርያየን እንደከበበኝ ይሰማኛል። የሂወት ዘመን አላማየ ከእወቀት መካፍል፣ ከጥበብ መቅመስ ነውና ፤የምፈልገው ነገር እኔንም ይፈልገኝ ይሆናል በሚል አቋም የነገሮችን መቋጫ ለማግኘት ከቀደመው መበርታት እንዳለብኝ ተሰማኝ። ''በሂወትህ የሚያጋጥሙህ ሚስጥሮችን በሙሉ ስትፈታቸው ፍችው ዞሮ ዞሮ የሌላኛው የሂወት ሚስጥር ሲሆንብህ ተጠንንቅ ሞትህን እንዳትናፍቅ''። ይህ ቃል ምን ማለት ነው? ሚስጥሮች እንድትፈታ አግዝሃለሁ ፣የተፈታ የመሰለህ ነገር ግን ሌላ ውስብስብ ነገር ያመጣብሃል ለማለት ይሆን? በእርግጥ አልኩኝ ለራሴ ከተቀመጥኩበት ከኖራ አፈር ከተሰራች መደብ እየተደላደልኩ። በእርግጥ በትንሿ እድሜየ የተገነዘብኩት አንድ እውነት አለ። በአይነ ስጋ ከተገለጠችው አለም ከሚታየውና ከሚሰማው ውጭ በስጋ ብቃት የማትመዘን ና የማትገለጥ ሌላ ሌሎች የሚኖሩባት አለም አለች። የምንም ነገር መጨረሻ ወይም መደምደሚያ ራሱ ምንም ነው። የማይቋጭ ጉዞ ፣መጨረሻ የለሌው ፍለጋ ፣ ከተጀመረበት ፈቅ ሳይሉ ከተነሱበት መገኘት የሂወት አካል ናቸው። በእርግጥ ፍለጋ ለሰዋዊ ስሜት አዲስ የሚመስል የነበር ግን ያልተገለጠን ግኝት ታስገኛለች ፣ የተሰወረ ሲገለጥ ያለተገለጡ እልፎችን አዝሎ ይመጣል። በግትልትሏ አለም ምንም አዲስ የሚባል ነገር የለም፤ ድሮም የነበረ በጊዜ ውስጥ እስረኛ የሆነ ራሱ ጊዜ የሚፈታው እንጂ ፣ ካለመኖር ወደመኖ

ጓሮዋ በአትክልቶች የተሞላች ስትሆን ከውስጧ እንደገባሁ ለአይንም ለ ልብም የሚደንቅ ነገርን ተመለከትኩ። ወለሏ በቀይ አፈር ከተለቀለቀችው ጎጆ ይልቅ በኖራ አፍርና በተጠረቡ እንጨቶች ዙሪያውን ግድግዳው ጋ የተሰራችው የመጻህፍ መደርደሪያ መሉ መጻህፍ ሞልቶባት በተመለከትኩ ጊዜ የህዝብ ቤተ መጻህፍት ውስጥ እንጂ ከ አንድ የመነኩሴ ቤት የገባሁ አልመስል አለኝ። በተለያዩ ቋንቋወች የተጻፉ በርካታ መጻህፍ በስርአት ተደራርበው ተቀምጠው ሳይ በመገረም መንኮሴውን ተመለከትኳቸው እሳቸው አንዳች ነገር እያዜሙ ለእኔ ምግብን ለማዘጋጀት ደፋ ቀና ይላሉ... ሰበዝና አክርማ በማዋህድ በወስፌ እየተነደለ በማሰናሰል በባህላዊ መንገድ የሚሰራ ቆለምሽሽ በሚባል መ መገቢያ ላይ የገዳሙን ዳቤ በበርብሬ ለውሰው ከ ሱፍ የሚዘጋጂ ጭልቃን ከእንስራው አንቆርቁረው ይመገቡ ይመገቡ ብለው አቀረቡልኝ። ከጀርባ የሆነ ነገር እንደ ተመለከትኩ ውስጥ ገብቸ ባየሁትም እንደተገረምኩ እና ሀሳብ ውስጥ እንደጣለኝ የገባቸው ይመስላሉ ካለሁበት ጭንቀት ለመገላገል በሚመስል ሁኔታ ስለተለያዩ ነገሮች እያነሱ ይጠይቁኝ ጀመር። ወደ ገዳሙ ከመጣሁ ሶስት ድንቅ መነኮሳትን አገኘሁ አንደኛው ምንነታቸውን እንኳ ሳለውቃቸው የማይፈታ እንቆቅልሽ አሸክመው ተለዪኝ ፤ሁለተኛው ምን እንዳሉኝ እንኳ ጭራሹን ሳልረዳቸው ሸኙኝ፤ ሶስተኛው ደግሞ ቁምነገርን እንደ ቀልድ እያወሩ ከ አምሮየ በላይ በሆነ ልሳን ግራ በሚያጋባ የሂወት ፍልስፍና ይንጡኝ ጀመር። በሶስቱም ቦታ ላይ የወይን ሃረግ ፍሬን በተለያየ አጋጣሚ እና ሁኔታ መመልከቴ ደግሞ ሌላ ጥርጣሬ ውስጥ ከቶኛል። ወደ ምፈልገው ጥያቄ ለመውሰድ እያኮበኮብኩ ይህንን ያህል መጻህፍ የእርሰው ነው? አባ አልኳቸው የማያውቁት ይመስል ቀና ብለው እየተመለከቱት በፈገግታ አወን ያለኝ ትልቁ ውዱ ሃብቴ ይህ ነው ለበርካታ አመታት የሰበሰብኳቸው ልጆቸ ማለት ናቸው። መነኩሴው የተማሩ፣ ብዙ የተመራመሩ፣ አለም ላይ በነበራቸው ሂወት የስኬትን ቁንጮ የተቀዳጁ ሰው መሆናቸው ከሁኔታቸው ከንግግራቸው ከሁለንተናዊ ማንነታቸው መረዳት ይቻላል። በገዳሙ ውስጥ የተለያዩ የእጂ ስራ ውጤቶችን በመስራት፣ የጸሐይ ብርሃን መሰብሰቢያወችን በመገጣጠም፣ ለገዳሙ ዘመናዊ የእርሻ እና የመስኖ ግባእቶችን በማዘጋጀት ፣ እንዲሁም የተለያዩ ምድር ውስጥ የሚገነቡ ሚስጥራዊ የዕቃ ማስቀመጫ የህንጻ ዲዛይኖችን ያለ ብረትና ሲሚኖት መገንባት፣ በቋሚነት በገዳሙ ውስጥ የሚሰሩት ስራ ነው። ከዛ ውጭ ብዙ መጻህፍትን በመጻፍ ከአፋዊ የእውቀት ሽግግር ወደ መጻህፍዊ ሰንደው በማዘጋጀት ለተተኪው ትውልድ ለማቃበል ብራና ዳምጠው ቀለም በጥብጠው ብዕር ቀርጸው የብራና መጻህፍትን ያዘጋጃሉ ። ከሂወታቸው አኗኗርን፣ ከኖራቸው ብርታትን ፣ከርዕዮተ አለማቸው የኑሮ ስነ ዘዴያቸውን፣ በአጠቃላይ የሂወትን ልምዳቸውን ያጫዉቱኝ ዘንድ ልቤ ፈልጓል ምን ብየ እንደምጀምር ግራ ቢገባኝም አባ ይህንን የምንኩስና ሂወት እንዴት እንደመረጡት ቢያጫዉቱኝ? በመቀጠልም እኔ እንደተረዳሁት እርስው በአለሙ የኖሩ፣ በእውቀትም የተራቀቁ፣ እንደሆኑ ነው ይህ ያሉበት ደግሞ ከዚያኛው እጂጉን የተለየ በእግዚአብሔር መመርጥ ነውና ከቁሳዊዋ አለም ይህኛውን ሂወት እነዴት መረጡ? መልሱን ለመስማት ከመጓጓቴ የተነሳ ደረቴን ከ እግሮቸ ለጥፌ ጀሮየን እንደ ቆቅ አቁሜ አይን አይን እመለከት ጀመርኩ.. በእርግጥ አሉ ጠይሙ መነኩሴ በተንጀረገገ ጥቁር ጢማቸው ያሉ ነጫጭ ሽብቶች እየነካኩ። ሃብት ፣ንብርት፣ ገንዘብ፣ ሁሉም ቁሳዊ ናቸው ቁሳዊ ህላዊነት ደግሞ ከንቱ ነው። ማንኛውም ቁስ አካል የሚገለጸው ባሉት የአይነት መገለጫወች አይደለምን? ማለቴ የስሜት ህዋሳቶቻችን ተገዢ ከሆን ሁሌም ቢሆን የቁስ ባሪያወች ነን የቁስ ባርነት ደግሞ ዘላለማዊ ሞትን ታመጣለች። እንግዲህ በአለሙና በ ገዳማዊያኑ ያለው ትልቁ ልዩነት ለቁሳዊነት ያለን አመለካከት ልዩነት የፈጠረው ነው። ከቀለም፣ ሽታ፣ አይነት ፣መጠን፣ ቅርጽ ፣ውበት ፣ድምቀት፣ ምቾት፣ ለእነዚህ ያለን አመለካከት ነወ እንግዲህ የሰውን ሁለንተናዊ የሂወት ኡደቱን የሚወስኑት። ቁሳዊነት ከመንፈሳዊ አለም ጋር የማይወዳደር የማይለካካ መሆኑን ለመረዳት አስተውሎት ያስፈልጋል፤ ለዚህም ነው ይህንን አለም የመርጥኩት...በእርግጥ ንግግራቸው ልቤን ቢማርከኝም የምፈልገውን ነገር እንዳልነገሩኝ ለእኔም ለእርሳቸውም ገብቿቸዋል...ንግግራቸው እጂግ ማራኪ እና ውብ እውቀትና ብልሃት የተሞላበት ስለሆን ቢዘገይም የችግሮቸን መፍትሄወች እሳቸው ጋ እንደማገኝ እርገጠኛ ሁኛለሁ። ጀሮ አቸውን እንደሰጡኝ ሲገባኝ ጥያቄየን ቀጠልኩ.. በየ ባዕቱ ስዞር መነኮሳት ከጎጇቸው እንኳ ሳይወጡ በጽናት እና በጽሞና ያለ ማውራት በአርምሞ እንዴት መኖር ተቻላቸው? ለምንስ ስንፈልጋቸው አናገኛቸውም? ለጥያቄወቻችን መልሶችንስ ስለምን አርቀው ይቀብሩብናል? ለምን ጥበብን ለመግለጥ በሚስጥር የተሞላ መንገድን ይመርጣሉ? በእርግጥ ለመቀበል እኛ ስለማንችል ነው ወይስ እነሱ ንፉግ ሁነው? የእኛ ትውልድ እርግማን ተሸካሚ ሁኖ ይሆን ከተካፈላችሁት ሚስጥርና ጥበብ ማታካፍሉን? ከተቀበላችሁት የማታቃብሉን ከተገለጠላችሁ ማትገልጡልን ? የሚወራልን ነገር በእውነተ አለ? ወይም በዘመናት የተሸበበ ዘመን ያስረጀው የአፈ ታሪክ ባለቤቶች ነን? ጠቢባን አባቶቻችን ፀሐይን ያቆሙ፣ መላከ ሞትን ያወገዙ፣ በደመና የተጓዙ፣ ሰማያትን የ መረመሩ ፣ምድርነንም ያጠኑ፣ በእወቀት የነጠቁ፣ መዳሃኒትን አዋቂወች፣ እጂግ የተራቀቁ ፣ ከ አንድ አለት ላሊበላን የገነቡ፣ በንፋስ አውታር አክሱምን ያቆሙ ፣ ፍልሱፎች፣ ስልጡኖች ፣ ከስልጣኔ የተቋደሱ፣ ከአለም የቀደሙ ሃያላን ነበሩ ትሉናላችሁ...ከእውቀታቸው እንድንካፈል ከጥበባቸው እንደንቋደስ በፈለግን ጊዜ ጥበቡን አርቃችሁ ትቀብሩብናላችሁ..ሁሉንም በጽሞና ታልፉታላችሁ...ዝምተው ምንድን ነው? የአባቶቻችን ልጆች እንድንሆን ትፈልጋላችሁ መንገዱን ደግሞ ትሰውሩብናላችሁ፤ የጥበብ ጫፏን ትነግሩን እና መዳረሻዋን ግን ትሸሽጉናላችሁ? ስንርቃችሁ ጎተት ስንጠጋችሁ ገፋ ታደርጉናላችሁ፤ የአንድን እውነት መዳረሻ የሌሎች አልቆ መሳፍርት ጥያቆወች መጀመሪያ ይሆንብናል ፤ እና እኛ ወይስ እናንተ ነን የታሪክ ተጠያቂወች? የእኛ አለመቀበል ወይንስ የእናንተ አለመስጠት ነው ክፍተቱ ?... ለበርካታ ጊዜያት የሚሰማኝን ነገር ስሜታዊነት በተቀላቀለበት አነጋገር ነበር የተናገርኳቸው...። እጂግ በተረጋጋ ሁኔታ አድምጠው ከናፍሮቻቸውን በፈገግታ አጂበው ከፈቱና ''አብዝተው ዝም የሚሉት ድንገት ስንናገር የማሰብ ችሎታችን ይቀንሳል ብለው ይሆናላ '' አሉና ፈገግ አሉ... በአቅማችሁና በምኞቶቻችሁ መካከል ያለው ክፍተት አላስተዋላችሁም ፤ ምኞቶቻችሁ ሁሉ ከአቅሞቻችሁ የገዘፉ ናቸው ፤ በምኞት ብቻ የሚገኝ በፍላጎት ብቻ የሚመጣ እውቀትና ጥበብን ከወዴት ነው የምትፈልጉት? በአቅማችሁ እና በምኞቶቻችሁ መካከል ያለውን ክፍተት ሁለት ነገር የሞላዋል አነሱም እውቀትና እምነት ናቸው ። እውቀትና እምነት ወደ ምኞቶቻችሁን ሲገፏችሁ ያኔ ከእኛ እንደ አንዱ ትሆናላችሁ፤ ከእውቀታችን እውቀትን፣ ከጥበባችንም ጥበብን ፣ትከፈሉ ዘንድ ፈቃዳችን ይሆናል። ለዚህ ብቁ ላልሆነ ምኞት ብቻ ለናጠው፣ ሰሜት ብቻ ለገፋው ትውልድ ፣ ስለምን እኛነታችንን እንግለጥ? በልቦናው ለማያዳምጥ በሆዱ ለሚሰማ ስለምን ብልን ሚስጥራችንን እንግለጥ? ምዕመኑ መስማትና ከሚፈልጋቸው ነገሮች ውጭ ብትነግረው አይሰማም ፤ ማየት የሚችለው ፣ ብርሃን የሚያሳየውን ብቻ ከ

ከላይ የቀጠለ........ ስንት ስአት ነበር ወደዚህ የመጣችሁ, አሉ መጋቢው እንኳ አላየሁም ነገር ግን መንገድ የጀመርነው ጸሐይዋ ከመግባቷ ነው ቢያንስ የሁለት ስአት የእግር መንገድ ተጉዘን ይሆናል...ዳገቱን በስተቀኝ ትተን በጥቅጥቁ ደን ውስጥ ነበር የመጠነው ። መጋቢው እጃቸውን አፋቸው ላይ ጭነው በመገረም በጫካው በኩል ነው እንዴ አልፋችሁ የመጣችሁ? ጭንቅላታቸውን በመወዝወዝ ሃዘን መሳይ ግርምታቸውን ገለጡት። ሁኔታቸውን ተመለሰክቸ ምነው አባቴ ምነው ችግር አለ? መጋቢው ግን እያዳመጡኝ አልነበረም በነገርኳቸው ነገር ተገርመው አእምሮአቸው የፈጠረባቸው ጥያቄ ጋር ትግል የገጠሙ ይመስላሉ። እስኪ የሆነ ቦታ ደርሸ ልምጣ ብለው ከአለቱ ላይ ያስቀመጡትን የመነኩሴ ፎጣ በስርአቱ ተላብሰው ሄዱ። የሆነ ህልም ውስጥ የምዋዢቅ መሰለኝ እየሆነ ያለውን እውነት ከመረዳት ይልቅ ምህታትዊ ምዕናብ ውስጥ እንዳለሁ ይሰማኛል። በእርግጥ በሂወቴ በርካታ ገዳማት ዙርያለሁ፣ ብዙ እውቀትንም ተካፍያለሁ፣ የተለያዩ አስደናቂ የአኗኗር ዘየወች፣ የአበው የገዳማቶ የአምልኮ ስርአቶችንም ተመልክቻለሁ፣ አለም ላይ ተጽኖ ፈጣሪ የነበሩ አለማውያን ራሳቸውን ለፈጣሪ አስገዝተው በመንኩስና ስርአት ሂወታቸውን ሲመሩ በተረጋጋ ሁኔታ ገዳማዊ ሂወታቸውን ሲያስኬዱ ተመልክቸ እጹብ እጹብም ብያለሁ። በማያገባኝ እየገባሁ በማይ'ገባኝም እየዘባረኩ ሂወቴን አደጋ ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ክስተቶችም ገጥመውኝ በእግዚአብሔር ቸርነት አልፌያለሁ። የተዘዋወርኩባቸው ቦታወች እጂግ በርካታ ልዮነት ቢኖራየውም አንድ የሚያደርጋቸው ነገር የመነኮሳት ሂወት፣ ማነነት ፣ እና ጥበባቸው፣ እጂግ የተሰወር ሚስጥራዊ መሆኑ ነው። ከዚህ ቦታ ላይ የገጠመኝ ነገር መድረሻ ሆነ መጀመርያው ያልተገጠ የተቆላለፍ ነገር መሆኑ ግን ግራ አጋብቶኛል።... ከተቀመጥኩበት አይኖቸን ወደተለያየ አቅጣጫ ስወረውር ከመጋቢው ቤት ራቅ ብለው ሁለት መነኮሳት አጥራቸውን ያጥራሉ። በዝግታ ወጣሁና ወደ እነርሱ ተጠጋሁ ከ ወገቤ ጎንበስ ብየ ሰላምታን አበረከትኩ በአጸፋው ጎንበስ ብለው ሰላምታየን መለሱ ፈጠን ብየ ሂጀ ጫፍና ጫፍ ለሁለት የተሸከሙትን የተቆረጠ የፓፓያ ግንድ ተቀበልኳቸው። እጂግ የደከሙ መነኮሳት፣ አይኖቻቸው የፈዘዙ፣ አካላቸውን እንኳ በቅጡ መሸከም የማይችል ተክለ ሰውነት፣ ገላቸውን ሙሉ መሸፈን ያልቻለ የተቀዳደደ ቀሚስ ፣እድፍ ያለች አስኬማ አድርገው ጎንበስ ቀና ይላሉ። ልቤን ሰበሩት የእውነት ያጡ የነጡ ድሄች ስለሆኑ ለሰወነታቸው ልብስ፣ ለእግራቸው ጫማ ፣ኑሮ የነፈገቻቸው መሰለኝ.... ሁኔታቸውን በትኩሮት ስመለከት ስለ እኛ እያሰብክ ነው ልጂ አሉኝ አንደኛው ጠየም ብለው ኑሮ ያጎበጣቸው መነኩሴ። ልቦናየን ያነበቡት እስኪመስለኝ ተርበተበትኩ። ልክ እኮ ነህ ያው... ታድያ ተየት መጣህ? የተለመደ የመነኮሳት ጥያቄ ነው ትንሽ ራቅ ይላል ብየ የመጣሁበትን አስረዳሁ....በያዙት የብረት አንካሴ ለ አጥር የሚሆን ገደል ሲቆፍሩ ከተቀመጥኩበት ፈንጠር ብየ በመነሳት ላግዝወት ላግዝወት አይ አይ እንግዳ ክቡር ነው አሉ እንደምንም ተቀብየ ቁፍሮ ስጀምር እስቸው እንዳሰቡት ስፋትና ጥልቀት መቆፈር ተሳነኝ ቆይ ልጂ ቆይ እንዲህ ነው ብለው ከዚያ ከደከመ ገላ የማይታመን በጎረምሳ ምት ቆፈሩት.... ደካማ ሲሏቸው ጠንካራ ሁነው ተገኙ። መኖር ባልችል እንኳ ስለ ቀደመ ኑሮወቻቸው መጠየቅ ፤ስላለፈ ታሪካቸው መስማት ፤ከኖሩት ኑሮ መካፈል፤ ከገጠመኖቻቸው ገጠመኖች ማድመጥ፤ ከሂወታቸው ሁሉ መማር፤ ከመነኮሳቱ ዘንድ ልምዴ ነውና ከባዕታቸው ቁጭ ብየ ለኑሮ ምግብ ፣ለሂወት ስንቅ፣ የሆነኝን ምክርና ተግሳጽ ተቀበልኩ። ይንንም ኑሮ ወደውት እና ፈልገወት እንጂ አጠተው እንዳልመረጡት ገባኝ። ስለ ሰማያዊው ልብስ ሲሉ ምድራዊ ልብሳቸውን ቀደዱ፤ ስለ ሰማያዊ መንግስቱ ሲሉ ምድራዊ ክብራቸውን አዋረዱ።... ከህይወታቸው ኑሮን ዘግኘ ክብር ሰላምታን ሰጥቸ ስወጣ ከኋላየ ገ/ሥላሴ አሉኝ ''በእርግጥ እኛ ገዳዮቻችን ይምጡልን እንላለን ነገር ግን ይህ ዘመን ለቀሪወች.... እግዚአብሔር ከእናነተ ጋራ ይሁን ሰላም ሁኖ ድጋሚ ከተመለስክ ዛዕቲ ይዕቲ መካንየ(ያች ነች ቦታየ)'' ብለው በያዟት እንጨት ወደ ለመለመች ተክል አመለከቱኝ... ። ጥያቄ ለማቅረብ ፋታ ሳይሰጡኝ ወጡ.. ምን ለማለት እንደፈለጉም ሳልረዳ እኔም ቀድሞ ሲያሳስብኝ ወደ ነበረው ጉዳየ ተመለስኩ። እየተዘዋወርኩ በዙሪያው ያሉ እጽዋቶችን ስመለከት ቆይቸ ከትልቅ ዋርካ ስር ካለው ባርጩሜ ቁጭ ብየ አይኖቸን በየ አቅጣቸው ስልክ አንድ ትኩረቴን የሳበኝ ነገር ተመለከትኩ። ከ አራት በአራት በሆነች የጭቃ ቤት የወጡ በነጭ ወረቀት ላይ ቁመዉ የሚሞነጫጭሩ ደንደን ያለ ተክለ ሰውነት ጠይም ገጽታ ያላቸው መንኩሴ በግራ እጃቸው ወረቀት በቀኝ ደግሞ አስክርቢቶ እንደያዘ ቁልቁል ወረዱ..... አዲስ ነገር ፈላጊነቴ ከተቀመጥኩበት አርጩሜ እምር ብየ በመነሳት ከእርምጃ በፈጠነ ከሩጫ ዝግ ባለ አጓጓዝ ደረስኩ። ገረበብ ባለችው በር አጮልቄ ስመለከት ከጫፍ እስከ ጫፍ የተዘረጋ ጥቁር ሰሌዳ በጂኦሜትሪ ስእሎች ሞልቶ ተመለከትኩ..። ጠይሙ መነኩሴ ምን ሊሰሩ እንዳሰቡ ባልረዳውም ግን በሳይንስ ዘንድ ብቁ የሆኑ ሰው እንደሆኑ ተረዳሁ። ወደ ወረዱበት ቁልቁል መንገድ ተከትየ ወረድኩ ፤ከሲሚንቶ ኮንክሪት የተሰራ የሚመስል እጂግ ማራኪ የሆነ ተራውን የተደረደሩት ከኖራ አፈር የተገነቡ ቤቶችን ተመለከትኩ። ሰላምታየን ስሰጥ በፈገግታ ተቀበሉኝ..እጂግ የሚያምሩ የሲሚኒቶ ቤቶችን የሚያስንቁ ስራወች ናቸው ስል በፈገግታ ''ስራቸን ከአፈር መሆኑን አሳበቅክ'' አሉኝ ምሁሩ መነኩሴ። ''አለም እንዴተ ሰንበታለች? ምን አዲስ ክስተት አለ? አሉ በእጃቸውን ህንጻውን እየነካኩ''...አለም አሰልች ነች... በምንኖርባት ምድር ሁሉም ነገር እየተለወጠ ነው ለውጡ ለበጎ ቢሆን ጥሩ ነበር ነገር ግን ሰው ሁሉ ሰባእዊ ባህሪው ና ጠባዩ እየተለወጠ ነው ይህ ደግሞ አደጋ ነው ህዝቡ በፍርሃት ቆፍን ውስጥ ወድቋል...አልኳየው። ወደ ቤታቸው እያመራን ፈገግ የሚያስብሉ ነገሮችን እያወጉኝ በጂኦሜትሪ የተመላችውን ቤት በስተቀኝ ትተን ወደ ባዕታቸው ተጓዝን። ከሁሉም ባዕቶች ራቅ ብላ ለብቻ የተሰራች ውብ በኖራ የተቀለሰች ቤት የእሳቸው የእጂ ስራ መሆኗን አይቸ ተረዳሁ....። በሃርግ አጥር የተከለለው ቤታቸው በጀርባ በኩል ታላቅ ጋራ ታክኮ በግራና ቀኝ ደግሞ ሚያማምሩ እጽዋቶች ተውቧል። በቦታ አመራረጣቸው ተገርሜ በሃርግ አጥር የተከበበችውን ጎጆ ስዞር ከጋራው ጫፍ እስከ ጫፍ የተወጠረ አቦጀዴ የሚያማምሩ ስነ ስእላትን በአግርሞት ተመለከትኩ። የእያንዳንዱ ስእል ላይ የውይን ሃረግ ፍሬ የመሰሉ ስአላት በተሰጣቸው የቁጥር ውክልና ተቀምጠው አየሁ ስእላቱ ላይ ያየሁት ፍሬ የአባ ገ /ሂወት ከትራሴ ላይ ጥለዋት የሄዱ አይነት ስትሆን የለመለመች የእጽዋት ቀጥሏም '' ዛእቲ ይእቲ መካንየ'' ያች ነች ቦታየ ብለው መነኩሴው የተቆሙኝ ነች.....የነገሮቹ መገጣጠም ወደ አንዳች ጫፍ ይወስደኝ ይሆን..... ስነ ስእላቱ ስመለከት የቤተክርስቲያን ስእላት ሁሌም ከሚያስተላልፉት መልእከት ለየት ባለ የአሳሳል ስነ ዘዴ የተዋበ ነው። ይምጡ እንጂ የሚል ድምጽ ከጎጆዋ ጣራ ስር ወጥቶ ከተመስጦየ አባነነኝ። በገዳማት የሚኖሩ መነኮሳት ማንኛውንም አይነት ሰው አንቱ ብሎ የመጥራት ልምዳ አላቸው። ያየሁትን እያምሰ ለሰልኩ ወደ ቤቷ አመራሁ .... ጋራውን ታካ በኖራ የተገነባችው ውብ ጎጆ ቤት ከውጭ በኩል