uk
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Відкрити в Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Показати більше
2 639
Підписники
+124 години
+167 днів
+5630 день
Архів дописів
ክፍዎች ሰዎችም ቀንተውበት በጠላትነት ተነሡበት በክርስቶስ ከማያምኑ ጋራ ተሰባስበው ወደ ሸንጓቸውም አደረሱት ይህን ቅዱስ ባስሊዖስን ታላቅ ግርፋትን ገረፉት ነፍሱንም በጌታችን እጅ እስከሰጠ ድረስ እያሠቃዩ በዚያች አገር አዋሉት። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ቴዎቄጤኖስ በዚህች ቀን በንጉሥ መክስምያኖስ ዘመን ቅዱስ ቴዎቄጤኖስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህ ቅዱስ አስቀድሞ ወታደር ነበር ትጥቁን በንጉሡን ፊት ጥሎ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ ከርሱም ጋራ ብፅዕት እስክንድራ አለች። ንጉሡም ሰምቶ ተቆጣ ልብሱን አስወለቀው የሴቶች ልብስ አልብሰው ከሚፈትሉ ሴቶች ጋራ እንዲጨምሩት። ከዚያም የጋለ የብረት መንኰራኲር በላዩ አድርገው ዘቅዝቀው ቊልቊል እንዲሰቅሉት አዘዘ። ሁለተኛም እንዲህ ብሎ አዘዘ የፈላ ቅጥራን የተመላ ወጭት አምጥታችሁ ወደ ጆሮው እስቲደርስ በራሱ ላይ ድፉበት ደግሞ ከተሰቀለበት አውርደው ከእሥረኛዋ እስክንድራ ጋር በፊቱ እንዲአቆሙት አዘዘ። ከዚህም በኋላ ምላሱን እንዲቆርጡ አዘዘ በእሊህ ቅዱሳን በአንገቶቻቸው የሚካበዱ ደንጊያዎችን አሥረው በኤፍራጥስ ወንዝ ውስጥ እንዲጥሉአቸው አዘዘ። በዚያም ተጋድሎአቸውንና ምስክርነታቸውን ፈጸሙ ሥጋቸውንም ምእመናን አግኝተው በሥውር ቦታ ቀበሩት፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር መጋቢት_11 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ዐሥራ አንድ  በዚህች ዕለት ከተሰዓቱ ቅዱሳን አንዱ #አባ_አሌፍ አረፈ፣ ተጋዳይ የሆነ ኤጲስቆጶስ #አባ_ባስሊዖስ በማዕትነት አረፈ፣ በንጉሥ መክስምያኖስ ዘመን #ቅዱስ_ቴዎቄጤኖስ በሰማዕትነት አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አባ_አሌፍ መጋቢት ዐሥራ አንድ በዚህች ዕለት ከተሰዓቱ ቅዱሳን አንዱ አባ አሌፍ አረፈ፡፡ ተሰዓቱ ቅዱሳን በፈቃደ እግዚአብሔር ተሰባስበው በአንድ ላይ አገልግሎታቸውን ይፈጽሙ እንጂ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ ናቸው፡፡ እነርሱም የቁስጥንጥንያው አባ ሊቃኖስ፣ የሀገረ ቁስያው (ኢጣሊያ) አባ ይምአታ፣ የአንጾኪያው (ሶሪያ) አባ ጽሕማ፣ የቂልቅያው (ግሪክ) አባ ጉባ፣ የእስያው አባ አፍጼ፣ የሮምያው ጰንጠሌዎን፣ የቂሣርያው አባ አሌፍ ናቸው፡፡ ሁሉም የነገሥታት ልጆች ቢሆኑም ዓለምን ፍጹም ንቀው በአባ ጳኩሚስ እጅ ከመነኮሱ በኋላ ሮምን ወደ ቀናች ሃይማኖት መልሰዋት ነበር፡፡ በሮም ሣሉ በምድረ አዜብ ብሔረ ኢትዮጵያ ስለሚኖሩ ሰዎች ዝና ስለ ነገሥታቶቻቸውም ቅድስናና ሀገሪቱም የእመቤታችን አሥራት መሆኗን ከመጻሕፍት ተረዱ፡፡ አባ ዘሚካኤልም ከሁለቱ ደቀ መዛሙርቶቹ ጋር በሌሊት ወጥቶ ወደ ኢትዮጵያ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እየመራው መጥቶ አክሱም ደረሰ፡፡ በዚያም ጥቂት ጊዜ በመቀመጥ ተመልሶ ወደ ሮምያ ሄዶ ስለ ኢትዮጵያ ያየውንና የሰማውን በሙሉ ሁሉ ለሌሎቹ ቅዱሳን ሲነግራቸው እነርሱም ‹‹ይህችን ሄደን ማየት አለብን›› ተባበብለው ያላቸውን ሁሉ ይዘው ታቦቶቻቸውን፣ ካህናቶቻቸውን፣ ንዋየ ቅድሳቶቻቸውን፣ መጻሕፍቶቻቸውን ሁሉ ይዘው በዘሚካኤል መሪነት በመምጣት በ460 ዓ.ም ጳጳሱና ንጉሡ ካሉበት አክሱም ከተማ ገቡ፡፡ ተሰዓቱ ቅዱሳን ከአብርሃ ወአጽብሐ 6ኛ ንጉሥ በሚሆን በአልሜዳ ዘመነ መንግሥት ከአውሮፓና ከእስያ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው አክሱም ከተማ ካረፉ በኋላ ሀገረ ስብከታቸውን ተከፋፍለው ገዳም እየገደሙ፣ በዓት እያበጁ፣ ከሣቴ ብርሃን አባ ሰላማ የመሠረተውን የክርስትና ሃይማኖት በከፍተኛ ሁኔታ አስፋፍተዋል፡፡ ገዳማትን አስፋፍተው የወንጌልን ብርሃን በሀገራችን ላይ አብርተዋል፡፡ ተሰዓቱ ቅዱሳን የነገሥታት ወገን ስለሆኑ በሮም ነግሦ የሚገኘውን ወንድማቸውን ይስሐቅን ላኩበት፡፡ ንጉሡ ይስሐቅ ለአባ ዘሚካኤል የእኅት ልጅ ነው፡፡ እርሱም መልእክቱ እንደደረሰው 7 ዓመት በሮም ከነገሠ በኋላ መንግሥቱን ትቶ በሌሊት ተነሥቶ በመውጣት ወደ ሀገራችን በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል መሪነት መጣና ከወንድሞቹ ጋር ተቀላቀለ፡፡ እነርሱም አመነኮሱትና ስሙን ገሪማ አሉት፡፡ ሁሉም በአንዲት የጸሎት ቤት በምንም ሳይለያዩ በአንድነት እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ እንደ አንድ ልብ መካሪ ሆነው ለጸሎት ቆመው ውለው ያድሩ ነበር፡፡ እነዚህም እጅግ የከበሩ ቅዱሳን ድውያንን እየፈወሱና ሙታንን እያስነሱ እጅግ በጣም አስገራሚ የሆኑ ድንቅ ድንቅ ብዙ ተአምራትን ያደርጉ ነበር፡፡ ከሰንበት በቀር እህል የሚባል ነገር የማይቀምሱት እነዚህ ቅዱሳን ኢትዮጵያን በኪደተ እግራቸው ባርከዋታል፣ ጌጦቿ ሆነውላታል፣ በትምህርታቸው የእምነቷን መሠረት አጽንተውታል፣ የልዕልናዋንም ታሪክ ለዓለም መስክረውላታል፡፡ ለ12 ዓመታትም በፍጹም አንድነት አብረው ከተቀመጡ በኋላ ‹‹እርስ በራሳችን እየተያየን ብንኖር ተድላ ደስታ ይሆንብናልና ተለያይተን እንቀመጥ›› ብለው ተማከረው በተለያየ በዓት አባ ሊቃኖስ በደብረ ቁናጽል፣ አባ ጰንጠሌዎንም በእርሱ ትይዩ በሆነ ቦታ፣ አባ ገሪማ በደብረ መደራ፣ አባ ጽሕማ በደብረ ጸድያ፣ አባ ይምአታ በደብረ ገረዓልታ፣ አባ አፍጼ በደብረ ይሐ፣ አባ አሌፍ በደብረ አኅድአ፣ አባ አረጋዊ በደብረ ዳሞ መኖር ጀመሩ፡፡ በዋሻና በፍርኩታ ውስጥ በተራራም ላይ መኖር ጀመሩ፡፡ እናንተ የከበራችሁ ቅዱሳን ሆይ! የነገሥታት ልጆች ስትሆኑ ላባችሁን እያንጠፈጠፋችሁ በዱር በገደል መንከራተታችሁ፣ በቀበሮም ጉድጓድ መቀመጣችሁ፣ የምትለብሱት ሳታጡ በበርድ በቁር መራቆታችሁ ምንኛ ድንቅ ነው!? የምትበሉት የምትጠጡት ሳታጡ የነገሥታት ልጆች ስትሆኑ መራብ መጠማታችሁስ እንደምን ያለ ነው!? አቡነ አሌፍ ኤርትራ ጠረፍ አካባቢ ወደሚገኘው በዓታቸው ወደ ደብረ አኅድአ በሄዱ ጊዜ በቦታው ላይ ታላቅ ዘንዶ ሰፍሮ ይኖር ነበር፡፡ ይህንንም ታላቅ ዘንዶ ቦታውን አስለቅቀው በዋሻ ውስጥ ገብተው ብዙ ተጋድሎ አድርገዋል፡፡ ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ሕዝቡንም የከበረች ወንጌልን እያስተማሩ በተአምራት ከደዌ እየፈወሱ በጸሎታቸውም አጋንንትን እያስወጡ፣ ድውያንን እየፈወሱ፣ ዕውራንን እያበሩ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ሐዋርያዊ አገልግሎት ፈጽመዋል፡፡ መላእክትም ዘወትር ባለመለየት አባ አሌፍን ይጎበኙዋቸው ነበር፡፡ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዘወትር እየተገለጠላቸው ይባርካቸውና ቃልኪዳን ይሰጣቸው ነበር፡፡ የአቡነ አሌፍ ገዳማቸው ከአዱዋ በስተሰሜን አቅጣጫ ወደ ኤርትራ ጠረፍ አቅራቢ ልዩ ስሙ ብህዛ በሚባለው ተራራማ ቦታ ላይ ይገኛል፡፡  የአባታችን በዓለ ዕረፍታቸው መጋቢት 11 ነው፡፡ ነገር ግን ቀደምት ቅዱሳን አባቶቻችን በደነገጉት መሠረት ይህ ወቅት ዐቢይ ጾም ላይ ስለሚውል በዚህ ወቅትም ምንም ዓይነት በዓል ማክበር ሥርዓት ስላልሆነ በጻድቁ ገዳም ውስጥ የአባታችን በዓላቸው በስፋት የሚከበረው ታህሳስ 11 ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አባ_ባስሊዖስ በዚህችም ዕለት ደግሞ ተጋዳይ የሆነ ኤጲስቆጶስ አባ ባስሊዖስ በማዕትነት አረፈ። ይህንንም ቅዱስ የኢየሩሳሌሙ ሊቀ ጳጳሳት አባ አርሞን ከሌሎች ኤጲስቆጶሳት ጋራ ሾመው። በታወቀና በተወሰነ ቦታ ላይ አይደለም። እምነት በሌላቸው በአረማውያን አገር ይሰብክ ዘንድ ላከው እንጂ። ይህም ቅዱስ ወደ ከሀድያን አገር ገብቶ የከበረ ወንጌልን ሰበከ። እነርሱም እየደበደቡ በአገራቸው ሁሉ አዞሩት። ደግሞ ወደ ሠርዑና አገሮች ገብቶ የከበረ የወንጌል ትምህርትን ስተማረ። እኩሌቶቹ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ያላመኑት እኩሌቶቹ ከሀድያን ግን አሳደዱት ከከተማው ውጭ ወጥቶ በዋሻ ውስጥ ተቀመጠ። የዚያች አገር ሰዎች እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ ይመለሱ ዘንድ በአንድ ልጁም ያምኑ ዘንድ ስለዚያች አገር ሰዎች አዘውትሮ እግዚአብሔርን ማለደ። በዚያንም ሰሞን ለእርሱ ለአባቱ አንድ ብቻውን የሆነ የመኰንኑ ልጅ ሞተ። አባቱም ታላቅ ኀዘንን አዘነ መኰንኑ አባቱም በሕልሙ ልጁን አየው። እርሱም በፊቱ ቁሞ አባቴ ሆይ እነሆ እኔ በታላቅ ጨለማ ውስጥ ነኝና ወደ ክርስቶስ ስለ እኔ ይጸልይ ዘንድ ኤጲስቆጶሱ አባ ባስሊዖስን ጠርተህ ለምነው ሲለው ነበር። ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ደንግጦ ተነሣ ከእርሱም ጋራ የአገር ታላላቆችን ይዞ ወደ ቅዱስ ባስሊዖስ በዓት ሔደ። ከእርሱ ጋራም ወደ ከተማ ገብቶ ስለ ልጁ እንዲጸልይ ለመነው። እርሱም ልመናውን ተቀብሎ ወደ ከተማ ገባ በመኰንኑ ልጅ መቃብር ላይም ጸለየ ያንጊዜም የመኰንኑ ልጅ ድኖ በሕዝብ ሁሉ ፊት ተነሣ መኰንኑ ሕዝቡም ሁሉ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ከአገርም ሰዎች ብዙዎች አምነው የክርስትና ጥምቀትን በቅዱስ ባስሊዖስ እጅ ተጠመቁ በዚያቺም አገር ታላቅ የክርስቲያኖች ጉባኤ ሆነ።

ደብረ_ዘይት   የዐቢይ ጾም 5ኛ ሳምንት   ደብረ ዘይት ማለት የወይራ ተራራ ማለት ነው፡፡ ይህም ቦታ ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ ካለው ከቄድሮስ ሸለቆ ራቅ ብሎ የሚገኝ፣ ርዝመቱ ፪ ኪሎ ሜትር፥ ከፍታው ደግሞ ከኢየሩሳሌም ከተማ በላይ 62 ሜትር ያህል ከፍታ ያለው ነው፤ቢታንያና ቤተ ፋጌ ከደብረ ዘይት ተራራ ሥር የሚገኙ ቦታዎች ናቸው፡፡ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ የተፈጸሙ  ድርጊቶች -  በደብረ ዘይት ተራራ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ ጊዜ የሚያድርበት፣ የሚያስተምርበት፣ ውሎ የሚያርፍበት ሥፍራ ነበር። - የጌታችን በዳግም ምጽአት እንደሚመጣ አስተምሮበታል /ማቴ.24፥1-36/ ⊚ 33 ዓመት ከ3 ወር በዚህ ምድር ተመላልሶ ሞቶ ከተነሳ በኋላ ያረገበት ተራራ ነው፤ ‹‹ሁለት ሰዎች ነጫጭ ልብስ ለብሰው በአጠገባቸው ቆመው ታዩአቸው ‹እናንተ የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እያያችሁት ለምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ ያረገው ኢየሱስ፥ ከእናንተ ወደ ሰማይ ሲያርግ እንዳያችሁት እንዲሁ ዳግመኛ ይመጣል› አሏቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ደብረ ዘይት ከሚባለው ተራራ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፤›› ሐዋ.1፥11-12፣ ሉቃ.24፥51-52/፡፡ - ዳዊት ከልጁ ከአቤሴሎም በሸሸ ጊዜ ወደ ደብረ ዘይት አቀበት ወጥቶ ነበር /2ኛ ሳሙ.15፥30/፣ - ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ሆሳዕና ከደብረ ዘይት ወደ ኢየሩሳሌም ሔዷል /ማር.11፥1/ - ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ግርጌ በምትገኘው ለምለም ስፍራ በጌቴ ሴማኒ በአይሁድ ጭፍሮች ተያዘ፡፡ ማር.26፥30-36፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተቀበረችበት ቦታም በጌቴሴማኒ ነበር፡፡ - በደብረ ዘይት ተራራ ወገብ ላይ በሰፊው ተንጣሎ የሚታይ የአይሁድ መቃብር አለ። ይህን ስፍራ ለመቃብርነት የመረጡበት ምክንያት ወደፊት መሢሑ መጥቶ እስራኤልን ነፃ አውጥቶ ወደ አባቱ ያርጋልና ኋላ ለፍርድ ሲመጣ በመጀመሪያ የሚፈርድበት ስፍራና ሙታንም የሚነሱበትና የሚሰበሰቡበት ስፍራ ይህ በመሆኑ እኛ መሢሐችንን ለማግኘትና ከሙታንም ለመነሳት የመጀመሪያዎቹ እንሆናለን ብለው በማመናቸው ነው። አይሁድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መሢሕ እርሱ ነው ብለው አያምኑም። በመሆኑም እስራኤል ወደፊት አንድ ታላቅ መሢሕ እግዚአብሔር እንደሚልክላቸው ባላቸው ተስፋ መሠረት ገና አሁንም ድረስ መሢሐችንን እንጠብቃለን ይላሉ፤ ነገር ግን አይሁድ በዚህ በትልቁ ነገር ላይ ወደኋላ ቀርተው ተበድለዋል። ቀመረ አዝማናትን ቀንሰዋል፥ ቈነጻጸለዋል፤ የኦሪት መጽሐፋቸው ኦሪተ ብጡል ተብላለች፤ ይመጣል ያሉበትም ዘመን ሳይመጣ ዓለም ከተፈጠረ፥ ዘመን ከተቈጠረ 8ኛ ሺህ ላይ ደርሰናል፡፡ ይሁንና እግዚአብሔር እስራኤልን ብቻ ሳይሆን ዓለሙን ሁሉ እንዲያድን  አንድ  ልጁን  ጌታችን  መድኃኒታችን  ኢየሱስ  ክርስቶስን ልኮልን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶልን በእርሱ ቁስል እኛ ተፈውሰናል፣ በእርሱ ሞት እኛ ሕይወትን አግኝተናል /ኢሳ.፶፫፥፬-፮/። ከዚህ በኋላ ሌላ መሢሕ ሌላ አዳኝ ፈጽሞ የለም፡፡ ※ ከዳግም_ምጽአት በፊት የሚከሰቱት ድርጊቶች /ማቴ. ፳፬፥ ፫-፴፮/ እንደተገለጸው፡- - ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና ብዙዎችንም ያስታሉ - ጦርነትን የጦርነትንም ወሬ ትሰማላችሁ - ሕዝብ በሕዝብ ላይ፣ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣሉ - በየሀገሩም ረኃብ፣ ቸነፈርም፣ የምድር መናወጥም በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል - በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጧችኋል፤ ይገድሏችሁማል፤ ስለ ስሜም በሕዝብ ሁሉ ዘንድ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ - በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ እርስ በእርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ፣ እርስ በእርሳቸውም ይጣላሉ - ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ፤ ብዙዎችንም ያስታሉ - ከዐመፅም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች -  የጥፋት ርኩሰት በተቀደሰችው ሥፍራ ቆሞ ታያላችሁ

የዐቢይ ጾም አምስተኛ ሳምንት እግዚአብሔርሰ ገሀደ ይመጽእ ወአምላክነሂ እያረምም እሳት ይነድድ ቅድሜሁ። ትርጉም :-እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝም አይልም እሳት እሳት በፊቱ
የዐቢይ ጾም አምስተኛ ሳምንት እግዚአብሔርሰ ገሀደ ይመጽእ ወአምላክነሂ እያረምም እሳት ይነድድ ቅድሜሁ።        ትርጉም :-እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝም አይልም እሳት እሳት በፊቱ ይነዳል።

🔴#ስንክሳር መጋቢት_10 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት አስር በዚች እለት የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት #ቅዱስ_ስመስቀል የተገለጠበትና የተገኘበት ነው፣ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ታላቁን ዲማ ጊዮርጊስን የመሠረቱ #የአቡነ_ተከስተ_ብርሃን የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ዕፀመስቀል መጋቢት አስር በዚች እለት የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የተገለጠበትና የተገኘበት ነው። የዚህም የከበረ ዕፀ መስቀል መገለጡና መገኘቱ ሁለት ጊዜ ሆኗል።መጀመሪያ የፃድቁ ንጉስ የቆስጠንጢኖስ እናት በሆነች በንግስት እሌኒ እጅ ነው። «እርሷ ለእግዚአብሔር ተስላ ነበርና ልጇ ቆስጠንጢኖስ ወደ ክርስቲያን ሀይማኖት ቢገባ ወደ ኢየሩሳሌም ሄዳ መስቀሉን እስከ አገኘችው ድረስ ልትፈልግው በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ልታንፃቸው ነው። ከዚህ በኋላ ልጇ አምኖ የክርስትና ጥምቀትን በተጠበቀ ጊዜ እሌኒ ቅድስት ወደ ኢየሩሳሌም ሄደች ከእረሷ ጋርም ብዙ ሰራዊት ነበር ደርሳም ስለ ከበረ መስቀል መረመረች የሚያስረዳት አላገኘችም የአይሁድ ወገን የሆነ አንድ ሽማግሌ ሰው አስራ በርሀብና በጥማት አስጨነቀችው። በተጨነቀም ጊዜ ለንግስት እሌኒ የጉልጎታን ኮረብታ አስጠርጊ ብሎ ነገራት እርሷም ይጠርጉ ዘንድ አይሁድን አዘዘቻቸው። ቤቱን የሚጠርግ ሰው ሁሉ ጥራጊውን በውስጡ የከበረ መስቀል በአለበት በጌታችን መቃብር ላይ እንዲጥል አይሁድ አስቀድመው አዝዘው ነበርና ንግስት እሌኒ እስከ ደረሰችበት ጊዜ ከሁለት መቶ አመት በላይ ጥራጊያቸውን ሲጥሉበት ኖሩ ኮረብታም ሆነ። አይሁድም በጠረጉ ጊዜ ሶስት መስቀሎች ተገለጡ የክብር ባለቤት ክርስቶስ የተሰቀለበት የትኛው እንደሆነ አላወቁም። የሞተ ሰውም አግኝተው አመጡ። አንዱንም መስቀል አምጥተው በሞተው ሰው ላይ አኖሩት አልተነሳም ደግሞ ሌላውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ አኖሩ አሁንም አልተነሳም ከዚህም በኃላ ሶስተኛውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ አደረጉት ያንጊዜ የሞተው ሰው ተነሳ እሌኒም የክርስቶስ መስቀል እንደሆነ አውቃ ሰገደችለት የክርስቲያንም ወገኖች ሁሉ ሰገዱለት። ለልጅዋ የላከችው ይህ መስቀል ነው የሚል በሌላ መፅሀፍ ይገኛል የቀረው ግን ግንዱ በውስጡ ተተክሎበት የነበረው ከእርሱም እኩሌታውን ከቅንዋቱ ጋራ ወደ ልጅዋ የላከችው ነው። ከዚህም በኃላ ስራአታቸውና የህንፃቸው ነገር በመስከረም ወር በአስራ ሰባት ተፅፎ የሚገኝ አብያተ ክርስቲያናትንና የከበሩ ቦታዎችን አነፀች። ሁለተኛው በሮሙ ንጉስ በህርቃል ዘመን የሆነው ሲሆን የፋርስ ሰዎች በግብፅ አገር ሳሉ ወደ አገራቸው ሊመለሱ ወደዱ። ከሹማምንቶቻቸው አንዱ የጦር መኰንን ተነጥሎ ወደ ኢየሩሳሌም አልፎ ደረሰ ወደ ከበረ መስቀል ቤተ ክርስቲያንም ገባ። መስቀሉም በላዮ በተተከለበት ግንድ ፊት ታላቅ ብርሀን ሲበራ አይቶ ሊያነሳው እጁን ዘረጋ። እሳትም ወጥታ እጁን አቃጠለችው። ከክርስቲያን በቀር ማንም ሊነካው እንደማይችል የመስቀልን የክብሩን ነገር ሰዎች ነገሩት። ሁለት ዲያቆናትንም ይዞ የከበረ መስቀልን እንዲሸከሙ አዘዛቸው ከኢየሩሳሌም ብዙ ሰዎችን ማርኮ ወደ አገሩ ተመለሰ። የፋርስ ሰዎች ኢየሩሳሌምን እንዳጠፏት ብዙዎች ሰዎችንም እነድ ማረኩና የከበረ የክርስቶስንም መስቀሉን እንደ ወስዱ የሮም ንጉስ ህርቃል በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ። ስለርሱም እንዲፆሙ ምእመናንን አዝዞ ወደፋርስ ዘምቶ ወጋቸው ብዙዎችንም ገደላቸው የከበረ እፀ መስቀልንም እየፈለገ በሀገራቸው ሁሉ ዞረ ግን አላገኘውም። ያ ዲያቆናቱና መስቀሉን የወሰደ መኰንን ከቦታዎች በቤቱ አነፃር ባለ በአንድ ቦታ ላይ ወስዷቸው ጥልቅ ጉድጓድ እንዲቆፍሩ አዝዞ በዚያ የከበረ መስቀልን አስቀበረ እነዚያንም ዲያቆናት ገደላቸው። ነገር ግን ያ መኰንን የማረካት የካህናት ወገን የሆነች በእርሱ ቤት የምትኖር አንዲት ብላቴና ነበረች። እርሷም የከበረ መስቀልን ሲያስቀብርና ሁለቱን ዲያቆናት ሲገድላቸው በቤቱ ውስጥ ሁና በመስኮት ትመለከት ነበር ወደ ንጉስ ሀርቃልም ሂዳ መኰንኑ ያደረገውን ሁሉ ነገረችው። ይህንንም ንጉስ ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ያቺ ብላቴናም መራችው ከእርሱም ጋራ ብዙ ሰራዊት ሆኖ ኤጲስቆጶሳትና ካህናትም ነበሩ። ወደ ቦታውም እስከምታደርሳቸው ያቺን ልጅ ተከተሏት ቅፍረውም የከበረ እፀ መስቀልን አገኙት ከአዘቅቱም አወጡት ንጉሱና ሰራዊቱም ሰገዱለት። በልብሰ መንግስቱም አጐናፀፈው ታላቀወ ክብርንም አከበረው እጅግም ደስ አለው ከሰራዊቱ ጋር። የዚህም መስቀል ሁለተኛ የተገለጠበትና የተገኘበት በዚች ቀን በመጋቢት አስር ነው፡፡ ከዚህ በኃላ ንጉሱ የከበረ እፀ መስቀልን ተሸክሞ ወደ ቁስጥንጥንያ ከተማ ወሰደው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_ተከስተ_ብርሃን በዚህች ቀን ለኢትዮጵያ ጻድቅ ታላቁን ዲማ ጊዮርጊስን የመሠረቱ አቡነ ተከስተ ብርሃን ዘደብረ ድማኅ የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ጻድቁ አባታቸው መልከ ጼድቅ እና እናታቸው ድል በኢየሱስ ይባላሉ፡፡ አባ ተከስተ ብርሃን ከዲማ ዋሻ በመነሳት እየተዘዋወሩ ወንጌልን አስተምረዋል። ከዕለታት አንድ ቀን ከጎጃም አውራጃ ይኸውም እነብሴ በሚገኘው ነድ አጹራ ማርያም በሚባለው ቦታ ያሉ ሰዎች የእጃቸውን ተዓምራት የቃላቸውን ትምህርት ሰምተው ከማመናቸው የተነሳ በአንድ ቀን ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ ህዝብ በማጥመቃቸውና ቀኑ መሽቶ ስለነበረ ብርሃን ስለወረደላቸው አባ ተከስተ ብርሃን የሚል ስም ሰጥቷቸዋል፤ የቀድሞ ስማቸው አባ በኪሞስ ነበርና። አባ ተከስተ ብርሃን እንዲህ ባለ መንፈሳዊ አግልግሎት ደብረ ድማኅንና እግዚአብሔርን ሲያገለግሉ ኖረዉ በበአታቸው በዲማ በመቀመጥ ለ15 ዓመታት ለገዳሙ መምህር በመሆን ገዳሙን አጠናክረዋል። አባታችንም የሴትና የወንድ ገዳም አቋቁመው ሴቶችን በምሥራቅ ወንዶችን በምዕራብ መኖሪያቸው አድርገው በአንድ በር እየገቡ በአንድ አዳራሽ እየተሰበሰቡ እንደማዕረጋቸው በቆብና በአስኬማ እየተቀመጡ ሰርከ ህብስታቸው እንዲመገቡ አድርገው ከቆዩ በኋላ መጋቢት 10 ቀን ዐርፈው በዋሻው ውስጥ ተቀብረዋል። በስማቸው በፈለቀ ጠበል በሽተኞች በተለይ በመውለድ የሚሰቃዩት ይፈወሳሉ። ከአቡነ ተከስተ ብርሃን ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። የመድኃኒታችን የመስቀሉ በረከት ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር መጋቢት_9 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ዘጠኝ በዚህች ቀን ተጋዳይ የሆነ ጽኑዕ አባት #ቅዱስ_ኩትን አረፈ፣ የከበረ #ቅዱስ_እንድርያኖስና_ሚስቱ_አውሳብዮስና_አርማ በሰማዕትነት አረፉ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ኩትን_ሐዋርያ መጋቢት ዘጠኝ በዚህች ቀን ተጋዳይ የሆነ ጽኑዕ አባት ኩትን አረፈ። እርሱም በሶርያ አገር ስሟ በንጣንዮስ ከምትባል ቦታ የሚኖር ነው። አባቶቹም ከዋክብትን ያመልኩ ነበር የአባቱ ስም ንስጣር የእናቱም ስም ቴዎድራ ይባላል። በአደገ ጊዜም ወላጆች ሊአጋቡት ፈለጉ እርሱ ግን አልወደደም ግድ ብለው ያለውዴታው ሚስትን አጋቡት ሊገናኛትም አልፈለገም ስለ ሥጋ ድካም ወይም ስለ ጽድቅ ሳይሆን የሥጋ ፍትወትን ስለሚጠላት ነው እንጂ። ደናግልም እንደሆኑ ሁለቱ ሁሉ ከሚስቱ ጋራ በአንድነት ኖረ። አምላክ ሆይ ወደ ዕውቀትህ ምራኝ በማለት ጸሎትና ምልጃን ያዘወትር ነበር። ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ ለቆርኔሌዎስ እንደተገለጠ ተገልጦ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ማመንን አስተማረው ከሐዋርያትም ወደ አንዱ ሔዶ የክርስትና ጥምቀትን እንዲጠመቅ አዘዘው። የሐዋርያት የስብከታቸው ወራት ነበረና ሒዶ ተጠመቀ የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት ሁሉ ሕጉን ሥርዓቱንም ሁሉ ተማረ መለኮታዊ ምሥጢርንም ተቀበለ። በየቀኑ ሁሉ የሐዋርያ ጳውሎስን ትምህርት ይሰማ ነበር የጽድቅን ሥራ መሥራትና ንጽሕና ለበጎ ሥራ መጠመድ ትጋት ቅንነት የዋህነት ጾም ጸሎት ሰጊድ በላዩ ተጨመረ። በእነዚህ ሁሉ የሚተጋ ሆነ እግዚአብሔርም አስደናቂ ተአምራቶችን እንዲአደርግ በርኲሳን አጋንንት ላይ ሥልጣንን ሰጠው። በሚያደርገው ተአምራትም ወላጆቹን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደማመን ስቦ አስገባቸው ደግሞ ሚስቱንና ወላጆቿን አስገባቸው። ከከሀድያን አንዱ ለሰይጣን ሊሠዋ ወደ ጣዖቱ ቤት በገባ ጊዜ ቅዱስ ኩትን አውቆ በሰይጣን ላይ ጮኸ እርሱ ሰይጣን እንጂ አምላክ እንዳልሆነ በሰው ፊት ያምን ዘንድ አዘዘው። ሰይጣንም እንዳዘዘው ራሱን ገለጠ በዚያ የነበሩ ሁሉም የቅዱስ ኩትን አምላክ አንድ እርሱ ብቻ ነው እያሉ ጮኹ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቁ። ከዚህ በኋላ ከቀላውዴዎስ ቄሣር የተላከ መኰንን የቅዱስ ኩትንን ዜናውን በሰማ ጊዜ ወታደር ልኮ አስቀረበው ስለ ሥራውም ጠየቀው እርሱም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ መኰንኑም ጽኑ ግርፋት ገርፈው እንዲአሥሩት አዘዘ ይህንንም አደረጉበት። የአገር ሰዎችም ቅዱስ ኩትንን አሠቃይተው እንዳሠሩት በሰሙ ጊዜ ሁሉም ወደርሱ ተራወጡ መኰንኑንም ሊገሉት ወደዱ መኰንኑም ሸሸ። ቅዱስ ኩትንንም ከማሠሪያው ፈትተው ከደሙም አጥበው ተሸክመው ወደቤቱ ወሰዱት ከዚያም በኋላ ብዙ ዘመናት ኑሮ የወደደውን እግዚአብሔርን አገልግሎ ደስ አሰኝቶ በፍቅር አንድነት አረፈ። ከዕረፍቱም በኋላ ቤቱን ቤተ ክርስቲያን አድርገው ሥጋውን በውስጥዋ አኖሩ ጌታችንም ከሥጋው ብዙዎች ታላላቅ ተአምራቶችን አሳየ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_እንድርያኖስ በዚህች ቀን የከበረ እንድርያኖስና ሚስቱ አውሳብዮስና አርማ ሌሎች አርባ ሰዎችም በሰማዕትነት አረፉ። እሊህንም ምርጦች ለረከሰ ከወርቅና ከብር ለተሠራ ጣዖት ማምለክን እምቢ ስላሉ የክብር ባለቤት ለሆነ ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለስሙ ዐላውያን ጽኑ የሆነ ሥቃይን አሰቃዩአቸው። ከዚህም በኋላ ራሶቻቸውን በሰይፍ ቆረጡ የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

¤¤¤ጉባኤ ጽዮን¤¤¤ ፨፨፨ዘመነ ሰማዕታት በክርስቲያን ህይወት፨፨፨ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ሞ ከሞሽቱ 11፡30 ጀሞሮ
¤¤¤ጉባኤ ጽዮን¤¤¤ ፨፨፨ዘመነ ሰማዕታት በክርስቲያን ህይወት፨፨፨ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ሞ ከሞሽቱ 11፡30 ጀሞሮ

🛑የዕለቱ ወንጌል እና ምስባክ መጋቢት_8 #ዘቅዳሴ #ሮሜ_2:1-17፡ዕጓለ እመሕያው በምንትኑ ዘትትዋሥኦ #ይሁዳ_1:17-ፍጻሜ፡ወአንትሙሰ አኃዊነ ተዘከሩ ቃለ ዘነገሩክሙ #የሐዋ_ሥራ_1:15-ፍጻሜ፡
🛑የዕለቱ ወንጌል እና ምስባክ መጋቢት_8 #ዘቅዳሴ #ሮሜ_2:1-17፡ዕጓለ እመሕያው በምንትኑ ዘትትዋሥኦ #ይሁዳ_1:17-ፍጻሜ፡ወአንትሙሰ አኃዊነ ተዘከሩ ቃለ ዘነገሩክሙ #የሐዋ_ሥራ_1:15-ፍጻሜ፡ ወውእተ አሚረ ተንሥአ ጴጥሮስ #ምስባክ አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ፡፡ #ትርጉም ነገር የለም መናገርም የለም ድምጣቸውም አይሰማም ድምጣቸው ወደ ምድር ሁሉ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ፡፡ #መዝ_18:3-4 #ወንጌል #ማቴዎስ_10:1-17፡ወጸውዖሙ ለ፲ወ፪ አርዳኢሁ #ቅዳሴ፡ዘሐዋርያት፡፡(ዘበደኃሪ)

🔴#ስንክሳር መጋቢት_8 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ስምንት በዚህች ከአስራ ሁለቱ ሀዋርያት የአንዱ #የሐዋርያ_ቅዱስ_ማትያስ የእረፍቱ መታሰቢያ ሆነ፣ የእንዴናው መኰንን #ቅዱስ_አርያኖስ በሰማእትነት አረፈ፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_አባት_አባ_ዮልዮስ አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ማትያስ_ሐዋርያ መጋቢት ስምንት በዚህች እለት በአስቆሮቱ ይሁዳ ፈንታ የተሾመ ከአስራ ሁለቱ ሀዋርያት የአንዱ ሀዋርያ የማትያስ የእረፍቱ መታሰቢያ ሆነ። ይህም ሰውን ወደሚበሉ ሰዎች አገር ወንጌልን ይሰብክላቸው ዘንድ በሄደ ጊዜ ወዲያውኑ ይዘው አይኖቹን አውልቀው አሰሩት ምግባቸው የመፃተኛ ሰው በድን ስለሆነ ልማዳቸውም እንዲህ ነው። መፃተኛ ሰው ሲይዙ አይኖቹን አውልቀው በእስር ቤት ያኖሩታል።የያዙበትንም ቀን ይፅፋሉ ሰላሳ ቀንም እስቲፈፀም ሳር ያበሉታል ከዚያ በኃላም አውጥተው አርደው ይበሉታል። ሀዋርያ ማትያስም ታስሮ ሳለ ሰላሳው ቀን ሳይፈፀም በጌታችን ትእዛዝ ሀዋርያው እንድርያስ ወደርሱ ደረሰ የአገሩ ሰዎች የሚሰሩትን ክፉ ስራ አይቶ አደነቀ እጅግም አዘነ እስረኞችንም ሁሉ አውጥቶ የአገር ሰዎች ወደማያገኙአቸው ቦታ አኖራቸው።እነርሱ ግን ሁለቱ ሀዋርያት እንድርያስና ማትያስ ተገለጡላቸው የአገሩም ሰዎች ያዙአቸው በዘንገታቸውም ገመድ አስገብተው እስከሶስት ቀን በአገሩ ጥጋጥግ ጎተቱአቸው ሀዋርያት ስለዚያች አገር ሰዎች ስለድኅነታቸው ወደ እግዚአብሄር ፀለዩ ያንጊዜ ከወህኒ ቤቱ ምሰሶ ስር ውኃን አፈለቁ ውኃውም ከፍ ከፍ ብሎ በሀገር ውስጥ እሰከሚአጥለቀልቅና ወደ ሰዎች አንገት እስከ ደረሰ እየበዛ ሄደ። በተጨነቁና የህይወታቸውን ተስፋ በቆረጡ ጊዜ ወደ ሀዋርያት መጡ በፊታቸውም ኃጢአታቸውን እየተናዘዙ አለቀሱ ሀዋርያትም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመኑ እናንተም ትድናላችሁ አሉአቸው እሊያ ሁሉም በክብር ባለቤት በጌታችን አመኑ። ሀዋርያትም አስተማሩአቸው ገሰፁአቸውም የአንድነትን የሶስትነትን የመድኃኒታችን ሰው የመሆኑን ምስጢር ገለጡላቸው ደግሞም ይህን የአራዊት ጠባይ ጌታችን ከእነርሱ ያርቅ ዘንድ ፀለዩላቸው ከዚህ በኃላ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቋቸው ያ የአውሬ ጠባይ ከእርሳቸው ርቆ ሰው የሚመገበውን የሚመገቡ የዋሆች ቅኖች ሆኑ። ኤጲስቆጶሳትን ቀሳውስትንና ዲያቆናትንም ሾሙላቸው በቀናች ሀይማኖትም እያፀኑአቸውና እያስተማሩአቸው ሰላሳ ቀኖች ያህል ከእሳቸው ጋራ ኖሩ ከዚያም ወጥተው ሄዱ የአገር ሰዎች ግን በሌላ ጊዜ ወደ እነርሱ እንዲመለሱላቸው ሀዋርያትን ለመኑአቸው። ሀዋርያ ማትያስ ግን ወደ ደማስቆ ከተማ ገብቶ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰበከ።የአገርም ሰዎች ይዘው በብረት አልጋ ላይ አስተኝተው በበታቹ ስድስት ቀን ስድስት ሌሊት እሳት አነደዱ ሊአዩትም ወደርሱ በመጡ ጊዜ ፊቱ እንደ ፀሀይ ሲበራ አገኙት ስጋውንም ሆነ የራስ ጠጉሩን ወይም ልብሶቹን ምንም ምን እሳት አልነካውም እጅግም አደነቁ።አሁንም ዳግመኛ ሀያ አራት ቀን እስኪፈፀም ድረስ ሀዋርያ ቅዱስ ማትያስ በተኛበት በዚያ የብረት አልጋ በታች እሳትን አነደዱ። ከዚህ በኃላም ከእሳቱ ባወጡት ጊዜ ያለ ምንም ጉዳት ጤነኛ ሆኖ አገኙት እጅግም አደነቁ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ።እርሱም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃቸው ካህናትንም ሾመላቸው በቀናች ሀይማኖትም እያፀናቸው ከእርሳቸው ጋራ ኖረ። ከዚያም ተነስቶ ስሟ ፊላዎን ወደሚባል ከአይሁድ አገሮች ወደ አንዲቱ ሄደ በዚያም በጎ እረፍትን አረፈ ስጋውንም በመልካም ቦታ አኖሩ ከስጋውም በሽተኞችን በመፈወስ ታላላቅ የሚያስደንቁ ተአምራት ተገለጡ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_አርያኖስ_ሰማዕት በዚህች እለት የእንዴናው መኰንን ቅዱስ አርያኖስ በሰማእትነት አረፈ። ይህም እንዲህ ነው የከበሩ ፊልሞንና አብለንዮስ በእርሱ እጅ በሰማእትነት ከሞቱ በኃላ እርሱም በስቃይ ውስጥ ሳለ ከአማንያን አንዱ ከቅዱሳን ከደማቸው ወስደህ አይንህን ብትቀባ በዳንክ ነበር አለው ያን ጊዜም ከደማቸው ወስዶ አይኑን ቀባ ወዲያው ድኖ ፈጥኖ አየ። ከዚያም በኃላ በቅዱሳን ላይ በአደረገው ክፉ ስራ ሁሉ በድንቁርናውም ምህረት የሌለው ስቃይ ስለአሰቃያቸው ታላቅ ፀፀት ተፀፅቶ አዘነ ተነስቶም ጣኦታቱን ሰበረ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምኖ ምእመናንን ማሰቃየቱንም ተወ። ዲዮቅልጥያኖስም ወሬውን በሰማ ጊዜ ጭፍሮቹን ልኮ ወደርሱ አስመጣው በምን ምክንያት አማልክትን ማምለክ እንደ ተው ጠየቀው።እርሱም በቅዱሳን ሰማእታት እጅ እግዚአብሄር የሚሰራቸውን አስደናቂዎች ተአምራት ሊነግረው ጀመረ ህዋሳታቸውን እንዴት እንደሚቆራርጡአቸው በየአይነቱ በሆነ ስቃይም ሲያሰቃዩአቸው ያለምንም ጉዳት ጤነኞች ሆነው ተመልሰው እንደሚነሱ። ዲያቅልጥያኖስም የተአምራትን ነገር ስለ ነገረው ተቆጣ ፅኑ የሆነ ስቃይም እንዲአሰቃዩት አዘዘ። ሁለተኛም ከጉድጓድ እንዲጨምሩትና እስኪሞትም የጉድጓዱን አፍ እንዲዘጉ አዘዘ እንዲሁም አደረጉ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መልአኩን ልኮ ከጉድጓዱ አውጥቶ በንጉስ ዲዮቅልጥያኖስ መኝታ ላይ አቆመው።ንጉሱም በነቃ ጊዜ አይቶ ደነገጠ ፈራ ማነህ አንተ አለው። እርሱም እኔ የእንዴናው ገዥ አርያኖስ ነኝ ብሎ መለሰለት ንጉሱም ደንግጦ እየተንቀጠቀጠ በማቅጠቅልለቅ ከባህር እንዲአሰጥሙት አዘዘ በባህሩም ውስጥ ነፍሱን በጌታችን እጅ ሰጠ። እንዲህም ሆነ ቅዱስ አርያኖስ ዘመዶቹንና አገልጋዮቹን ሲሰናበታቸው እንዲህ ብሎ ነገራቸው ለስጋዬ እርሱ እንደሚአስብና ወደአገሬ ወደእንዴናው እንደሚመልሰው በሌሊት ራእይ እግዚአብሄር አስረድቶኛልና እናንተም በእስክንድርያ ወደብ ስጋዬን ጠብቁ አላቸው። በአሰጠሙትም ጊዜ ጌታችን አሳ አንበሪን አዘዘ አንበሪውም ተሸክሞ ወስዶ በእስክንድርያ ወደብ አውጥቶ በየብስ ላይ አኖረው።አሽከሮቹ ከዚያ እየጠበቁት ነበር ወደ አገሩ ወደ እንዴናው አድርሰው ከቅዱሳን ሰማእታት ከፊልሞንና ከአብላንዮስ ከስጋቸው ጋራ በአንድነት አኖሩት። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ዮልዮስ_ሊቀ_ዻዻሳት በዚችም ቀን ደግሞ በእስክንድርያ ለተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አስራ አንደኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አባት አባ ዮልዮስ አረፈ። ይህም አባት አስቀድሞ በእስክንድርያ ቄስ ሆኖ ነበር እርሱም በአለበት ዘመን በግብፅ አገር እንደርሱ ያለ የሌለ አዋቂ ብልህ የሆነ ምሁር ነበር። የክብር ባለቤት በሆነ በእግዚአብሄርም ፈቃድ በእስክንድርያ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ ብዙዎች ድርሳናትንና ተግሳፃትን ደረሰ። የሹመቱም ዘመን ሰላም የሰፈነበት ነበር በቀናች ሀይማኖትም ይፀኑ ዘንድ ህግና ስርአትንም ሁሉ እንዲጠብቁ ህዝቡን ሁልጊዜ ይመክራቸውና ያስተምራቸዋል። በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር አስር አመት ከኖረ በኃላ በሰላም በፍቅር አረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

🛑የዕለቱ ወንጌል እና ምስባክ #መጋቢት_7 ፊልሞን ወአብላንዮስ ወቅዱስ ቴዎድሮስ፡፡ #ዘቅዳሴ #ሮሜ_8:31-ፍጻሜ፡ምንተ እንከ ንብል እንበይነዝ #1ኛ_ዮሐንስ_1:14-20፡ጸሐፍኩ ለክሙ ወራዙት #የ
🛑የዕለቱ ወንጌል እና ምስባክ #መጋቢት_7 ፊልሞን ወአብላንዮስ ወቅዱስ ቴዎድሮስ፡፡             #ዘቅዳሴ #ሮሜ_8:31-ፍጻሜ፡ምንተ እንከ ንብል እንበይነዝ #1ኛ_ዮሐንስ_1:14-20፡ጸሐፍኩ ለክሙ ወራዙት #የሐዋ_ሥራ_5:17-34፡ወተንሥኡ ሊቃነ ካህናት             #ምስባክ ቀዳሚሃ ለጥበብ ፈሪሃ እግዚአብሔር ምክር ሠናይት ለኵሉ ዘይገብራ ወስብሐቲሁኒ ይነብር ለዓለም፡፡              #ትርጉም የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ለሚያደርጓትም ሁሉ ደህና ማስተዋል አላቸው ምስጋናውም ለዘላለም ይኖራል፡፡   #መዝ_110:10 #ማቴዎስ_10:28-ፍጻሜ፡ ኢትፍርህዎሙኬ እንከ ለእለ ይቀትሉ ሥጋክሙ #ቅዳሴ፡ዘወልደ ነጎድጓድ(ኀቤከ)

🛑የዕለቱ ወንጌል እና ምስባክ #መጋቢት_7 ፊልሞን ወአብላንዮስ ወቅዱስ ቴዎድሮስ፡፡             #ዘቅዳሴ #ሮሜ_8:31-ፍጻሜ፡ምንተ እንከ ንብል እንበይነዝ #1ኛ_ዮሐንስ_1:14-20፡ጸሐፍኩ ለክሙ ወራዙት #የሐዋ_ሥራ_5:17-34፡ወተንሥኡ ሊቃነ ካህናት             #ምስባክ ቀዳሚሃ ለጥበብ ፈሪሃ እግዚአብሔር ምክር ሠናይት ለኵሉ ዘይገብራ ወስብሐቲሁኒ ይነብር ለዓለም፡፡              #ትርጉም የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ለሚያደርጓትም ሁሉ ደህና ማስተዋል አላቸው ምስጋናውም ለዘላለም ይኖራል፡፡   #መዝ_110:10 #ማቴዎስ_10:28-ፍጻሜ፡ ኢትፍርህዎሙኬ እንከ ለእለ ይቀትሉ ሥጋክሙ #ቅዳሴ፡ዘወልደ ነጎድጓድ(ኀቤከ)

🔴#ስንክሳር መጋቢት_7 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ሰባት በዚህች ቀን የከበሩ #ቅዱሳን_ፊልሞንና_አብላንዮስ በሰማዕትነት አረፉ፣ #ቅዱስ_ቴዎዶጦስ በሰማዐትነት ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱሳን_ፊልሞንና_አብላንዮስ መጋቢት ሰባት በዚህች ቀን የከበሩ ፊልሞንና አብላንዮስ በሰማዕትነት አረፉ። ይህ ፊልሞንም የእንዴናው ገዥ በሆነ በአርያኖስ ፊት በአዝማሪነት ይጫወት ነበር ከአዝማሪው አብላንዮስም ጋራ እርስ በርሳቸው ወዳጆች ሆኑ ለክብር ባለቤት ክርስቶስም ስለ ስሙ ምስክሮች ሊሆኑ ተስማሙ። አዝማሪው ፊልሞንም ልብሱን ወስዶ ለአብላንዮስ ሰጠው እርሱም የአብላንዮስን ልብስ ለብሶ ወደ መኰንኑ ወደ አርያኖስ ገብቶ በፊቱ ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ። መኰንኑም ተመልክቶ አዝማሪው አብላንዮስ እንደሆነ አሰበ በፍላጻም እንዲነድፉት አዘዘ ያንጊዜም አዝማሪው ፊልሞን መሆኑን አውቆ እጅግ ተቆጣ። ደግሞ አብላንዮስን እንዲነድፉት አዘዘ ሁለቱንም ነደፉአቸው አንዲት ፍላጻም ወደ መኰንኑ ተመልሳ ዐይኑን አወጣቻት እጅግም አሠቃየችው። የከበሩ ፊልሞንና አብላንዮስ ግን ገድላቸውን ፈጽመው የሕይወት አክሊልን ተቀበሉ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስቴ_ቴዎዶጦስ በዚህችም ዕለት ደግሞ ቅዱስ ቴዎዶጦስ በሰማዕትነት አረፈ። እርሱም ከገላትያ አገር የሆነ በምክርና በተግሣጽ አምልኮተ እግዚአብሔርንም በማጽናት ያደገ ነው። ወደ ከሀዲ መኰንንም ሒደው የክርስቲያን ወገን እንደሆነ ነገር ሠሩበት መኰንኑም አሥረው እንዲአመጡት አዘዘ። ቅዱሱም ይህን በሰማ ጊዜ ሳይዙት ወደ መኰንኑ ሔዶ መኰንኑንና የረከሱ ጣዖቶቹን ረገመ ዘለፋቸውም መኰንኑ እሱን በማስፈራት ሁኖ የሥቃይ መሣሪያዎችን ሁሉ አሳየው ለጣዖት እንዲሠዋ በመሸንገል አስገደደው ቅዱሱም ስለ ድንቁርናው ረገመው ዘለፈውም። ከዚህ በኋላም የውስጥ ዕቃው እስከሚታይ ሰቀለው ጐኖቹን ይሠነጣጥቁ ዘንድ መኰንኑ አዘዘ። ከዚያም ወደ ወህኒ ቤት ይጨምሩት ዘንድ ደግሞ አውጥተው በዕንጨት እንዲሰቅሉት ቊስሎቹንም እንዲአድሱ ጐኖቹንም እንዲሠነጣጥቁ አዘዘ። እርሱ ግን መኰንኑ የሚያመጣውን ሥቃይ እንደ ኢምንት አደረገው በክብር ባለቤት በጌታችን ክርስቶስ በፍቅሩ ፍላጻነት ልቡ ተነድፏልና ዐይኖቹም ወደላይ ይመለከቱ ነበር። መኰንኑም ብርታቱን በአየ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ። ቅዱስ ቴዎዶጦስም የራሱን መቆረጥ ሰምቶ እጅግ ደስ እያለው ወጣ። ወደ እግዚአብሔርም ሲጸልይና ሲማልድ እንዲህ አለ። የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አመሰግንሃለሁ ከተከታተለኝ ክፉ ነገር ሁሉ አድነኸኛልና በጠላትነት የተነሡብኝንም ወደ ገሃነም አውረድካቸው እኔንም ከሞት በር ከፍ ከፍ አድረግኸኝ። ይህንንም ብሎ በሰገደ ጊዜ ወታደሩም የቅዱሱን ዐይን ይሸፍን ዘንድ መሸፈኛ አመጣ። ቅዱሱም ይህ ሞትን ለሚፈሩ ነው እኔ ግን በክብር ባለቤት በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሞትን አልፈራም አለ። ወታደሩም ሰይፉን መዝዞ የከበረች ራሱን ቆረጠ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር መጋቢት_6 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ስድስት በዚች ቀን #ቅዱስ_ዲዮስቆሮስ በሰማዕትነት አረፈ፣ ታማኝ የሆነ ኤጲስቆጶስ #የቅዱስ_ቴዎዶስዮስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፣ #የአቡነ_አርከሌድስ እረፍታቸው ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ሰማዕት_ዲዮስቆሮስ መጋቢት ስድስት በዚች ቀን በእስ*ላሞች ዘመነ መንግሥት ዲዮስቆሮስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ ከእስክንድርያ ሰዎች ወገን ነው በማግባባት በመገፋፋት ከክርስቲያን አውጥተው ወደ እስ*ልምና አስገቡት በእምነታቸውም ጥቂት ጊዜ ኖረ። ፍዮም በሚባል አገር ለአንድ ክርስቲያን ሰው የተዳረች አንዲት እኀት ነበረችው ወንድሟ የክብር ባለቤት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት እንደ ተወ በሰማች ጊዜ ታላቅ ኀዘንን አዘነች። ከዚህም በኋላ እንዲህ ብላ ወደርሱ መልእክትን ላከች የክብር ባለቤት ክርስቶስን አንተ እንደ ካድከው ከምሰማ በክርስትናህ ሳለህ የሞትህ መርዶ ቢመጣልኝ እወድ ነበር። ከዚያም ከቅዱሳት መጻሕፍት ጠቅሳ ጻፈችለት በደብዳቤዋ ፍጻሜም እንዲህ ብላ ጻፈች። "ከዛሬ ጀምሮ ወደ ክርስትናህ ካልተመለስክ ይህቺ ደብዳቤ በእኔና በአንተ መካከል የፍቅር ፍጻሜ እንደሆነች ዕወቅ ከቶ ፊትህንም እንዳታሳየኝ መልእክትም ቢሆን አትላክልኝ። የእኅቱንም የመልእክት ደብዳቤ በአነበበ ጊዜ መሪር ዕንባን አለቀሰ ተጸጸተ ፊቱን ጸፋ ጽሕሙንም ነጨ ተነሥቶም ወገቡን ታጠቀ ረጅም ጸሎትንም በመጸለይ ማለደ ፊቱንም አዳኝ በሆነ መስቀል ምልክት አማተበ ከቤቱም ወጥቶ በእስክንድርያ ከተማ ውስጥ ተመላለሰ። እስ*ላሞችም በአዩት ጊዜ ይዘው ወደ መኰንኑ አቀረቡት መኰንኑም ከእርሱ ስለሆነው ነገር ጠየቀው እርሱም ክርስቲያን ነኝ ሌላ ምንም ምን አላውቅም ብሎ መለሰ። መኰንኑም ደግሞ የክርስቲያንን ሃይማኖት ትተህ ወደእኛ እምነት ገብተህ አልነበረምን ብሎ መለሰለት። ቅዱስ ዲዮስቆሮስም መልሶ እንዲህ አለ በወልድ የማያምን ሕይወትን አያያትም የእግዚአብሔር የቁጣው መቅሠፍት በላዩ ይወርዳል እንጂ የሚል በከበረ ወንጌል ተጽፏል። ስለዚህ እኔ በክብር ባለቤት በሕያው እግዚአብሔር ልጅ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ እኔም ትውልዴ ከክርስቲያን ነው አሁንም በክርስትናዬ እሞታለሁ። መኰንኑም እጅግ ተቆጥቶ ከዚህ ምክርህ ካልተመለስክ እኔ የጸና ቅጣት እቀጣሃለሁ አለው። ቅጣቱንም ፈርቶ ከመልካም ምክሩ አልተመለሰም። ከዚያም በኋላ ታላቅ ግርፋት ገርፎ አሠረው በእሥር ጥቂት ቀናት ቆየ ከእሥር ቤትም አውጥቶ ከምክሩ ከሐሳቡ ቢመለስ ብዙ ገንዘብ ሊሰጠው ቃል ገባለት። ይህ ካልሆነ ግን በእሳት እንደሚአቃጥለው ነገረው። ቅዱሱም ሕያው በምታደርግ ከክርስቲያን ሃይማኖት በቀር በሌላ አልሞትም ብሎ መለሰለት። መኰንኑም በእሳት እንዲአቃጥሉት አዘዘ ከከተማም ውጪ ታላቅ ጉድጓድ ቆፈሩለት። ዕንጨትም መልተው አነደዱት ነበልባሉም እጅግ ከፍ ከፍ አለ ያን ጊዜም ብዙ ገርፈው ሥጋውን በሰይፍ ሰነጣጠቁ ። ወደ እሳትም ጨመሩት ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጥቶ በመንግሥተ ሰማያት የሰማዕትነትን አክሊል ተቀበለ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ቴዎዶስዮስ በዚችም ዕለት ታማኝ የሆነ ኤጲስቆጶስ የቅዱስ ቴዎዶስዮስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። የዚህንም ቅዱስ ዜና ከዲዮቅልጥያኖስ የተሾመ የቆጵሮስ ገዥ ዮልዮስ ሰማ። ወደርሱም አስቀርቦ የክብር ባለቤት ክርስቶስን ክዶ ለረከሱ ጣዖቶች ዕጣን እንዲአጥን መሥዋዕትም እንዲአቀርብ ፈለገ፡፡ ቅዱስ ቴዎዶስዮስም እኔስ በሕያው እግዚአብሔር ልጅ በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ ለእርሱም ዕሠዋለሁ በሎ መለሰ። ትእዛዙንም ባልሰማ ጊዜ ጽኑዕ ግርፋትን ከላም ቆዳ በተሠራ ጅራፍ ገረፈው። ከዚያም ሰቅሎ ሥጋውን ሁሉ ሰነጠቀ አውርዶም በእሳት በአጋሉት በብረት አልጋ ላይ አስተኛው ጌታችንም ከዚህ ሥቃይ ጠብቆ አዳነው። ከዚህ በኋላ እጆቹንና እግሮቹን በረጃጅም ችንካሮች ቸንክረው እስከ ወህኒ ቤት ጐትተው በዚያ ጣሉት። እግዚአብሔርም ከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስን አጥፍቶ ጻድቁ ቈስጠንጢኖስ እስከ ነገሠ ድረስ በወህኒ ቤት ኖረ። ቈስጠንጢኖስም የመንግሥት ሥልጣን በያዘ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን የታሠሩትን ሁሉ እንዲፈቷቸው አዘዘ። ከዚያም በኋላ ወደ አገሩ ተመልሶ በጵጵስናው ሹመት ላይ ሁኖ ምእመናንን በበጎ አመራር እየመራ ኖረ። ዕድሜውንም ፈጽሞ በሰላም አረፈ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_አርከሌድስ ዳግመኛም በዚህች እለት አቡነ አርከሌድስ እረፍታቸው ነው፡፡ አቡነ አርከሌድስ አገራቸው ግብፅ ሲሆን ከተሰዓቱ ቅዱሳ ቀጥሎ ነው ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ የመጡት፡፡ የነበሩበትም ጊዜ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በነበሩበት ጊዜ ነበር፡፡ወደ አገራችን ከመጡ በኋላ ወሎ ውስጥ ያለችውን እጅግ ጥንታዊቷን ቸር ተከል ማርያምን ቆረቆሯት፡፡ ጻድቁ የሚታወቁበት ትልቁ ገድላቸውም ሳይንት ውስጥ በቸር ተከል ማርያም ገዳም ውስጥ ለ21 ዓመታት ሳያርፉ ሳይቀመጡ በመቆም ጸሎት ያደረጉ ታላቅ አባት መሆናቸው ናቸው፡፡ አቡነ አርከሌድስ እጃቸውን ሲያጨበጭቡ 500 ርግቦች በአንድ ጊዜ ይሰበሰቡላቸው ነበር፡፡ እነርሱንም ወደፈለጉት ቅዱሳን መልእክት ይልኳቸው ነበር፡፡ በዚህ አስደናቂ ሥራቸውም በቅዱሳን ዘንድ ትልቅ ክብር ነበራቸው፡፡ለቅዱሳን የተለያየ ታሪክ አላቸው፣ ለአንዱ አንበሳ፣ ለአንዱ ጅብና አጋዘን፣ ለአንዱ ንብ፣ ለአንዱ ነብር፣ ለአንዱ አጋንንት ይታዘዙላቸው ነበር፡፡ ጻዲቁ በመጨረሻ ወደ ምረድ ግብፅ ተመልሰው ከሰማዕታት ጋር ተሰይፈው በሰማዕትነት ያረፉ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

#በዚህ_ሳምንት መጋቢት ዘጠኝ 12:00 ስዓት ሰዓት ስለምታከብሩ በእግዚአብሔር ስም እናመሰግናለን።
#በዚህ_ሳምንት መጋቢት ዘጠኝ 12:00 ስዓት ሰዓት ስለምታከብሩ በእግዚአብሔር ስም እናመሰግናለን።