የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Відкрити в Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Показати більше2 636
Підписники
+124 години
+167 днів
+5630 день
Архів дописів
🔴#ስንክሳር ግንቦት_3
#ቅዱስ_ያሶን_ሐዋርያ
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ግንቦት ሦስት በዚች ቀን ጌታ ከመረጣቸው ከሰባ ሁለቱ አርድእት ውስጥ የሆነ ሐዋርያው ቅዱስ ያሶን አረፈ። ይህም ቅዱስ ከሐዋርያት ጋራ ወንጌልን በሰበከ ጊዜ ብዙ መከራዎችን በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተቀበለ ድንቆች ተአምራትንም አደረገ በሃምሳኛው ቀን ከሐዋርያት ጋራ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሏልና።
ትውልዱም ከጠርሴስ አገር ነው ከጠርሴስም ሰዎች አስቀድሞ አመነ ሐዋርያ ጳውሎስም ከተጠራና ከአመነ በኋላ በብዙ አገሮች ተከትሎ በወንጌል ትምህርት አገለገለው በተሰሎንቄ ከተማም ከጳውሎስ ጋራ ይዘው በመጐተት ከተሰሎንቄ ገዢ ዘንድ አቀረቡአቸው።
ከዚህም በኋላ በጠርሴስ አገር ቅዱስ ጳውሎስ ኤጲስቆጶስነት ሾመው የወልደ እግዚአብሔርንም ቤተ ክርስቲያን በመልካም አጠባበቅ በቅንነት ጠበቀ። ምእመናንን በቀናች ሃይማኖት ከአጸናቸውና በጎ ምግባርን ከአስተማራቸው በኋላ ከዚያ ወደ ምዕራብ አገር ሒዶ በውስጥዋ የከበረ ወንጌልን አስተማረ። ስሟ ኮራኮራስ ወደምትባል ደሴትም ደርሶ በውስጧ ወንጌልን ሰበከ እግዚአብሔርንም ወደማወቅ መለሳቸው በዲያቆናት አለቃ በሰማዕታትም መጀመሪያ በከበረ ሐዋርያ እስጢፋኖስ ስም በውስጧ ቤተ ክርስቲያን ሠራላቸው።
የዚያች አገር ገዥም በአወቀ ጊዜ ይዞ ከእሥር ቤት አስገባው በዚያም ሰባት ወንበዴዎችን አግኝቶ ሃይማኖትን አስተማራቸው በክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው። ከዚያም በኋላ በመኮንኑ ፊት ቁመው እኛ ክርስቲያን ነን በክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን ብለው ጮኹ። መኰንኑም ዝፍትና ዲን በተመላ ምጣድ ውስጥ አግብቶ አቃጠላቸው የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ።
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ያሶንን ከእሥር ቤት አውጥቶ ብዙ አሠቃየው ነገር ግን ምንም ምን ጉዳት አልደረሰበትም። የንጉሡም ልጅ ከቤቷ መስኮት ሁና አይታ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነች ልብሶቿንና ጌጦቿን አውጥታ ለድኆችና ለምስኪኖች ሰጠችና ከዚያም በሐዋርያው በያሶን አምላክ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ታመነች አባቷም ሰምቶ እንዲአሥሩዋት አዘዘ እንዳዘዛቸውም አደረጉ። በጢስም አፍነው አሠቃዩዋት ደግመውም አራቈቷትና አባቷ በፍላፃ ነደፋት ነፍሷንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠች።
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ያሶንን ወደ ደሴት ሰደደው በደሴትም ውስጥ ያሠቃየው ዘንድ መኰንኑ ከሠራዊቱ ጋራ አብሮ በመርከብ ተሳፈረ እግዚአብሔርም ከሠራዊቱ ጋራ በባሕር አሠጠመው።
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ያሶን ወንጌልን እያስተማረ ብዙ ዘመናት ኖረ። ሁለተኛም ሌላ መኰንን ተሾመ ቅዱስ ያሶንንም ይዞ በምጣድም ውስጥ ድኝና ዝፍት ሰም መልቶ ነበልባሉ ወደ ላይ እስቲወጣ ድረስ ከበታቹ አነደደ ቅዱስ ያሶንንም በውስጡ ጨመረው። የክብር ባለቤት ጌታችንም አዳነው ምንም ምን ጉዳት አልደረሰበትም መኰንኑም ይህን ድንቅ ሥራ አይቶ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቤተሰቡ ሁሉ ከሀገር ሰዎች ሁሉ ጋራ አመነ። ሁሉንም አጥምቆ የከበረ የወንጌልን ሕግና ትእዛዝ አስተማራቸው አብያተ ክርስቲያንም ሠራላቸው በውስጣቸውም ብዙ ድንቆች ተአምራትን አደረገ ብሩህ በሆነ ገድሉ ጌታችንን ደስ ካሰኘውና ካገለገለው በኋላ በበጎ ሽምግልና አረፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።https://t.me/finotebirhan12
የግንቦት ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ፲፰ የመወያያ ርእሶች አጽድቆ ውይይት መጀመሩን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ገለጹ።
የ፳፻፲፭ ዓ/ም ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የጀመረ ሲሆን ይህን አስመልክቶም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሊቀ ጳጳስ የጉባኤውን የቀን ውሎ አስመልክቶ ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) መረጃ ሰጥተዋል።
ብፁዕነታቸው እንኳን አደረሳችሁ የቤተ ክርስቲያናችን ጉባኤ በመሆኑ የሁላችም ጉባኤ ነው በማለት መረጃ መስጠቱን ጀምረዋል።
ብፁዕነታቸው ጉባኤው በቅዱስነታቸው ቃለበረከት እና ቡራኬ እንዲሁም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተኙበት መከፈቱን ተናግረዋል።
ቀጥለውም የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ሪፖርት ጽ/ቤቱ ዓመቱ ያከናወናቸውን ዝርዝር ሥራዎች ለጉባኤው መቅረቡንና በቤተ ክርስቲያናችን ጉዳይ ራሳቸውን መስዋእት አድርገው ላቀረቡ፣ ለታሰሩ ለተንገላቱ፣ ብዙ መከራ ለደረሰባቸው ወገኖች ቤተ ክርስቲያናዊ ምስጋና በጉባኤው ፊት መሰማቱንም ገልጸዋል።
ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ አክለውም በአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ የተለይተው የቀረቡትን አጀንዳዎች በጽሞና ከተመለከተና ከመረመረ በኋላ ፲፰ የመወያያ አጀንዳዎች ማጽደቁንም ገልጸዋል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ካጸደቃቸው አጀንዳዎች መካከል
፩. የሀገራችን ሰላም ጉዳይ
፪. ስለቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ችግሮች
፫. የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫን በተመለከተ
፬. ተጨማሪ መንፈሳዊ ኮሌጆች ማቋቋምን በተመለከተ
፭. የውጭ ሀገራት ላሉ አህጉረ ስብከት መተዳዳሪያ ደንብ በተመለከተ
፮. የ10 ዓመት መሪ ዕቅድን በተመለከተ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ከእነዚህም በዛሬው ዕለት የቅዱስነታቸው የመክፈቻ ቃለበረከትና የሰላም ጉዳይ ላይ ውይይት ማድረጉን አብራርተዋል።
በመጨረሻም ጉዳዩ የሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በመሆኑ ማኅበረ ካህናት ወምእመናን ጉባኤው እስኪጠናቀቅ በብርቱ ጸሎት ሊያግዙንና ሊያስቡን ይገባል በማለት አባታዊ ተማጽኗቸውን ገልጸዋል።
EOTC TV
🔴#ስንክሳር ግንቦት_3
#ቅዱስ_ያሶን_ሐዋርያ
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ግንቦት ሦስት በዚች ቀን ጌታ ከመረጣቸው ከሰባ ሁለቱ አርድእት ውስጥ የሆነ ሐዋርያው ቅዱስ ያሶን አረፈ። ይህም ቅዱስ ከሐዋርያት ጋራ ወንጌልን በሰበከ ጊዜ ብዙ መከራዎችን በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተቀበለ ድንቆች ተአምራትንም አደረገ በሃምሳኛው ቀን ከሐዋርያት ጋራ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሏልና።
ትውልዱም ከጠርሴስ አገር ነው ከጠርሴስም ሰዎች አስቀድሞ አመነ ሐዋርያ ጳውሎስም ከተጠራና ከአመነ በኋላ በብዙ አገሮች ተከትሎ በወንጌል ትምህርት አገለገለው በተሰሎንቄ ከተማም ከጳውሎስ ጋራ ይዘው በመጐተት ከተሰሎንቄ ገዢ ዘንድ አቀረቡአቸው።
ከዚህም በኋላ በጠርሴስ አገር ቅዱስ ጳውሎስ ኤጲስቆጶስነት ሾመው የወልደ እግዚአብሔርንም ቤተ ክርስቲያን በመልካም አጠባበቅ በቅንነት ጠበቀ። ምእመናንን በቀናች ሃይማኖት ከአጸናቸውና በጎ ምግባርን ከአስተማራቸው በኋላ ከዚያ ወደ ምዕራብ አገር ሒዶ በውስጥዋ የከበረ ወንጌልን አስተማረ። ስሟ ኮራኮራስ ወደምትባል ደሴትም ደርሶ በውስጧ ወንጌልን ሰበከ እግዚአብሔርንም ወደማወቅ መለሳቸው በዲያቆናት አለቃ በሰማዕታትም መጀመሪያ በከበረ ሐዋርያ እስጢፋኖስ ስም በውስጧ ቤተ ክርስቲያን ሠራላቸው።
የዚያች አገር ገዥም በአወቀ ጊዜ ይዞ ከእሥር ቤት አስገባው በዚያም ሰባት ወንበዴዎችን አግኝቶ ሃይማኖትን አስተማራቸው በክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው። ከዚያም በኋላ በመኮንኑ ፊት ቁመው እኛ ክርስቲያን ነን በክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን ብለው ጮኹ። መኰንኑም ዝፍትና ዲን በተመላ ምጣድ ውስጥ አግብቶ አቃጠላቸው የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ።
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ያሶንን ከእሥር ቤት አውጥቶ ብዙ አሠቃየው ነገር ግን ምንም ምን ጉዳት አልደረሰበትም። የንጉሡም ልጅ ከቤቷ መስኮት ሁና አይታ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነች ልብሶቿንና ጌጦቿን አውጥታ ለድኆችና ለምስኪኖች ሰጠችና ከዚያም በሐዋርያው በያሶን አምላክ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ታመነች አባቷም ሰምቶ እንዲአሥሩዋት አዘዘ እንዳዘዛቸውም አደረጉ። በጢስም አፍነው አሠቃዩዋት ደግመውም አራቈቷትና አባቷ በፍላፃ ነደፋት ነፍሷንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠች።
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ያሶንን ወደ ደሴት ሰደደው በደሴትም ውስጥ ያሠቃየው ዘንድ መኰንኑ ከሠራዊቱ ጋራ አብሮ በመርከብ ተሳፈረ እግዚአብሔርም ከሠራዊቱ ጋራ በባሕር አሠጠመው።
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ያሶን ወንጌልን እያስተማረ ብዙ ዘመናት ኖረ። ሁለተኛም ሌላ መኰንን ተሾመ ቅዱስ ያሶንንም ይዞ በምጣድም ውስጥ ድኝና ዝፍት ሰም መልቶ ነበልባሉ ወደ ላይ እስቲወጣ ድረስ ከበታቹ አነደደ ቅዱስ ያሶንንም በውስጡ ጨመረው። የክብር ባለቤት ጌታችንም አዳነው ምንም ምን ጉዳት አልደረሰበትም መኰንኑም ይህን ድንቅ ሥራ አይቶ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቤተሰቡ ሁሉ ከሀገር ሰዎች ሁሉ ጋራ አመነ። ሁሉንም አጥምቆ የከበረ የወንጌልን ሕግና ትእዛዝ አስተማራቸው አብያተ ክርስቲያንም ሠራላቸው በውስጣቸውም ብዙ ድንቆች ተአምራትን አደረገ ብሩህ በሆነ ገድሉ ጌታችንን ደስ ካሰኘውና ካገለገለው በኋላ በበጎ ሽምግልና አረፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ግንቦት_2
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ግንቦት ሁለት በዚች ቀን #ጻድቅ_ኢዮብ አረፈ፣ የመንፈሳዊ ማኀበር አባት የአባ ጳኵሚስ ረድእ የከበረ #ቅዱስ_አባት_ቴዎድሮስ አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ጻድቁ_ኢዮብ
ግንቦት ሁለት በዚች ቀን ጻድቅ ኢዮብ አረፈ። ለዚህም ጻድቅ በዘመኑ እንደርሱ ያለ ዕውነተኛ ደግ ሰው እንደ ሌለ በቅዱሳት መጻሕፍትም ስለርሱ እንደተነገረ እግዚአብሔር መሰከረለት።
ሰይጣንም ቀንቶበት በገንዘቡና በልጆቹ ላይ ያሠለጥነው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነ። የጻድቅ ኢዮብን ትዕግሥት እግዚአብሔር ስለሚያውቅ አሠለጠነው ለመጪ ትውልድም አርአያና ምሳሌ እንዲሆን ፈቀደለት።
ስለርሱም ሐዋርያ ያዕቆብ በመልእክቱ እነሆ የጻድቅ ኢዮብን ትዕግሥቱን ሰምታችኋል አለ። ከዚህ በኋላም በአንዲት ቀን ገንዘቡ ሁሉ ጠፋ ሥጋውም በደዌ ሥጋ ከራሱ እስከ እግሩ ድረስ ተመታ። በዚህም በአስጨናቂ ደዌ ውስጥ ኖረ እግዚአብሔርንም አመሰገነው።
አንዲት ቃልን እንኳ በፈጠረው እግዚአብሔር ላይ አላጉረመረመም ነገር ግን የተወለደባትን ቀን ረገመ። እንስሶቹና ገንዘቡ ሁሉ በጠፋ ጊዜ እግዚአብሔር ሰጠ እግዚአብሔርም ነሣ የእግዚአብሔርም ስም የተመሰገነ ይሁን አለ።
በዚህ መከራ በነበረበት ዘመናት በተራራ ላይ ተጥሎ ሳለ የወዳጆቹና የሚስቱ ዘለፋ በዝቶበት ነበረ። እርስዋ እንዲህ ብላ መከረችው እስከ መቼ ድረስ በሞኝነት ትኖራለህ እንግዲህስ ስደበውና ሙት ዳግመኛ እግዚአብሔርን ደጅ እጠናዋለሁ መከራውንም እታገሣለሁ የቀድሞ ኑሮዬን ተስፋ አደርጋለሁ ትላለህን አለችው።
እንዲህስ እንዳትል ከዚህ ዓለም እነሆ ስም አጠራርህ ጠፋ ሴቶች ልጆቼና ወንዶች ልጆቼ ሞቱ እኔም ዘጠኝ ወር ሳረግዝ ሳምጥ ስወልድ ላይረቡኝ ላይጠቅሙኝ በከንቱ ደከምኩ ።
አንተም በመግል ተውጠህ በትል ተከበህ ትኖራለህ ሌሊቱን ሁሉ ስትዛብር ታድራለህ እኔም እየዞርኩ እቀላውጣለሁ ካንዱ አገር ወዳንዱ አገር ካንዱ ቤት ወዳንዱ ቤት እሔዳለሁ ከድካሜ በኔ ላይ ከመጣው ከችግሬም አርፍ ዘንድ ከጧት ጀምሮ ፀሐይ እስቲገባ ድረስ እጠብቃለሁ አሁን ግን እግዚአብሔርን የማይገባ ቃል ተናግረኸው ሙት አለችው።
ኢዮብም ሚስቱን እየተመለከተ ሰማት። ሥርዓት እንዳልተሠራባቸው ከአሕዛብ ሴቶች እንዳንዲቱ ተናገርሽን ከዚህ ቀድሞ በጎውን ነገር ከእግዚአብሔር እጅ ተቀበልን ከዚህ በኋላ መከራውን አንታገሥምን አላት። በዚህ ባገኘው መከራ ሁሉ ኢዮብ ጌታን የበደለው በደል የለም።
ኢዮብም ወርቅ በእሳት እንዲፈተን ፈጽሞ ተፈተነ። እግዚአብሔርም በደመና ውስጥ ተነጋገረው። ከተናገረውም በኋላ ከደዌው ፈወሰው ጥሪቱን ሁሉ ከቀድሞ እጥፍ አደረገለት ሌሎች ልጆችንም ሴቶችና ወንዶችን ሰጠው።
ኢዮብም ከደዌው ከተፈወሰ በኋላ መቶ ሰባ ዘመን ኖረ የኖረውም ዘመን ሁሉ ሁለት መቶ አርባ ስምንት ዓመት ነው። በበጎ ሽምግልናም እግዚአብሔርን አገልግሎ በሰላም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባት_ቴዎድሮስ
በዚችም ቀን የመንፈሳዊ ማኀበር አባት የአባ ጳኵሚስ ረድእ የከበረ አባት ቴዎድሮስ አረፈ።
ይህም አባት በገድል የተጠመደ ትሑት ቅን ታዛዥ በበጎ ሥራም ፍጹም ነበረ። ከአባ ጳኵሚስም ዘንድ ከታናሽነቱ ጀምሮ መነኰሰ ለፈጣሪውም እንደሚታዘዝ ይታዘዘው ነበረ።
ስለዚህም አባ ጳኵሚስ እጅግ ወደደው በላዩም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አድራበታለችና በአንድነት ለሚኖሩ መነኰሳት ሁሉ አጽናኝና አረጋጊ ሆነ። ጥበብና ዕውቀት ነበረውና በዕድሜው ሕፃን ሁኖ ሳለ አባ ጳኵሚስ ገሣጭና መካሪ አድርጎ ሾመው።
ከአባ ጳኵሚስም ዕረፍት በኋላ በአባቱ በአባ ጳኵሚስ ፈንታ አበ ምኔት ሆኖ ተሾመ። ይህም አባት ትሕትናው የበዛ ነው ከዚህ ከኃላፊው ዓለም ክብር ይሸሽ ነበር የአገልግሎቱንም በጎ ሥራ ፈጽሞ ወደወደደው እግዚአብሔር ሔደ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለሁላችን ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
የሚንቁትና የሚጠሉት ‹‹ይህ የነገሩትን ቀለም እንኳን አከናውኖ መናገር የማይችል ዛሬስ እንግዳ ድርሰት እደርሳለው ብሎ አገኝ አጣውን የቆጥ የባጡን ይቀባጥራል›› ብለው ተደነቁበት፡፡ የሚወዱትና የሚያከብሩት ግን ‹‹ከመንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እንዲህ ያለ ምሥጢር ከእሩቅ ብዕሲ ይገኛልን!›› ብለው አደነቁለት፡፡ ወዲያው የሚወዱት የሚያከብሩት ‹‹ጽፈን ደጉሰን አንይዘውምን!?›› አሉ፡፡ የሚንቁት የሚጠሉት ደግሞ ‹‹ማን ተናገረው ብለን እንይዘዋለን?›› አሉ፡፡ እንደ ልማዱ አድርገን አንይዘውም አሉ፡፡ ለሃገራቸው እንግዳ ድርሰት የተደረሰ እንደሆነ ጽፈው ደጉሰው ከእሳት ይጥሉታል፡፡ ከእሳት ደህና ሆኖ የወጣ እንደሆነ ከውሃ ይጥሉታል፡፡ ከውኃም ደህና ሆኖ የወጣ እንደሆነ ከድውይ ሰው ላይ ይጥሉታል፡፡ ከእሳት ገብቶ ባይቃጠል፣ ከውኃ ገብቶ ባይርስ በመጨረሻም ድውይ የፈወሰ እንደሆነ ‹‹ደገኛ ድርሰት ነው›› ብለው ይይዙታል፡፡ ይህንንም ቅዳሴ ማርያምን ጽፈው ደጉሰው ከእሳት ላይ ጣሉት፣ ከእሳት ደህና ወጣ፡፡ ከውኃ ላይ ጣሉት-ከውኃ ደህና ሆኖ ወጣ፡፡ ከደውያን ላይ ጣሉት-ድውይ ፈወሰ፡፡ ይልቁንም ሙት አስነሣ፡፡ ከዚህም በኋላ ‹‹ደገኛ ድርሰት ነው›› ብለው ጽፈው ደጉሰው ይዘውታል፡፡ በጥራዝም 14ኛ አድርገው ጠርዘውታል፡፡ ቅዳሴ ከዚያ በፊት 13 ነበርና አሁን ግን 14ኛ አድርገው ጽፈውታል፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ከ14ቱም ቅዳሴ ተአምራት ያልተደረገበት የለም፡፡
ይህም ቅዳሴ ማርያም ስለ እመቤታችን እጅግ በጠለቀ ሁኔታ የሚያመሰጥር በመሆኑ በሰሙነ ፍልሰታ ይተረጎማል፡፡ ዕለቱን የሚመለከቱ ምሥጢራትም በዕለቱ ይተረጎማሉ፡፡ ምሳሌ ነሐሴ ሦስት የበዓታና፣ ነሐሴ ሰባት የፅንሰታ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ የበዓታ ‹‹ድንግል ሆይ! አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ልጆች በጨዋታ ያደግሽ አይደለሽም፡፡ በቅድስና፣ በንጽሕና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ…›› የሚለውን ይመለከቷል፡፡ ነሐሴ ሰባትም ‹‹ድንግል ሆይ! ኃጢአት በሆነ ሩካቤ የተፀነስሽ አይደለሽም….›› የሚለውን ይመለከቷል፡፡
አባ ሕርያቆስ የእመቤታችንን ቅዳሴ እጅግ ድንቅ አድርጎ ለመጀመሪያ ጊዜ የቀደሰው በልደቷ ቀን ነው፡፡ ይኸውስ እንዴት ታወቀ ቢሉ አንድ ምግባር ሃይማኖቱ የቀና በትሩፋት የበለጸገ ደገኛ ባሕታዊ ነበርና ከተጋድሎውና ለእመቤታችን ካለው ፍቅር የተነሣሳ እመቤታችን ተገለጠችለት፡፡ እርሱም ‹‹ከ33ቱ በዓላት ማንን ትወጃለሽ?›› ብሎ ጠየቃት፡፡ እመቤታችንም ‹‹ኪዳነ ምሕረትን፣ ልደታን፣ አስተርአዮን፣ ፍልሰታን›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ከእነዚ ከ4ቱስ ማንን ትወጃለሽ?›› ቢላት እመቤታችን ‹‹ከጠባብ ወደ ሰፊ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን የወጣሁበት ነውና ልደቴን እወዳለው›› አለችው፡፡ ‹‹ቀድሞ እኔ ሳልወለድ እናትና አባቴን መባችሁን አንቀበልም ብለው አዝነው ተክዘው ነበር፡፡ የእነርሱ ሃዘን ሃዘኔ ነውና እኔን ከወለዱ በኋላ መባቸውን ተቀብለዋቸው ደስ ብሎዋቸዋል፡፡ የእነርሱ ደስታ ደስታዬ ነውና›› ብላዋለች፡፡
ይህንን ድንቅ የሆነውን የአባ ሕርያቆስን ቅዳሴ እመቤታችን ለሌላኛው ወዳጇ ለኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ገልጣለታለች፡፡ እመቤታችን ቅዱስ ኤፍሬምን ከሶርያ፣ አባ ሕርያቆስን ከብሕንሳ በደመና ጠቅሳ ቅዱስ ያሬድ ካለበት አድርሳ ‹‹አንተ ውዳሴዬን፣ አንተ ቅዳሴዬን ነግራችሁት በዜማ ያድርስ›› ብላቸው እነርሱም ለቅዱስ ያሬድ ነግረውት በዜማ አድርሶታል፡፡ ከዚሁም ጋር አያይዞ 13ቱንም ቅዳሴ በዜማ ደርሷል፡፡
በእመቤታችን በዓሏ ዕለት ጌታችን ተገልጦላቸው ቅዳሴዋን እንዲቀድሱ ነግሯቸው ለዚህም የሚሆን ከሰማይ ኅብስትና ጽዋ አውርዶላቸዋል፡፡ በዕለቱም ቅዳሴዋን ሲቀድሱ የከበሩ ሐዋርያት በቀኝ በግራ እየተራዷቸው ሲቀድሱ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ ኅብስቱንና ጽዋውን ጋርዶታል፡፡ በሌላ ጊዜም አቡነ ሳሙኤል ጊዜአቸው ደርሶ ከማረፉ በፊት ቅዱስ ሚካኤል ነሐሴ 16 ቀን ወደ ገነት ነጥቆ ወስዶ ከእመቤታችን ፊት አቁሞ አስባርኳቸዋል፡፡
ቅዱሳን አባቶቻችን የእመቤታችንን ቅዳሴዋን ሲቀድሱ ከምድር ከፍ ብለው ይታዩ ነበር፡፡ የዋልድባው አቡነ ሳሙኤል ቅዳሴ ማርያምን እየደገሙ ሲሄዱ ክንድ ከስንዝር ከመሬት ከፍ ይሉ ብለው ይሄዱ ነበር፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ዕለት ውኃውን ቢባርኩት ውኃው ኅብስት ሆኖላቸው ተመግበው ምእመናንንም መግበዋቸዋል፡፡ እመቤታችንም የፍቅር ምልክት ሁለት ንዋያት ከጠቻቸው በኋላ ‹‹ውዳሴዬን ከቅዳሴዬ ጋራ አንድ አድርጎ የሚደግመውን ሰው አንተ ከገባህበት ውሳጤ መንጦላዕት አገባዋለው›› ብላ ተስፋቸውን ነግራዋለች፡፡ ይህንንም መሠረት ነማድረግ ልጆቻው ዛሬ በዋልድባ ያጠና በቃሉ፣ ያላጠና በመጽሃፍ ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን ሳይደግም የሚውል የለም፡፡ ይህም ተስፋ ውዳሴዋን ከቅዳሴዋ ጋር አንድ አድርጎ ለሚደግም ሰው ሁሉ ነው እንጂ ለእነርሱ ብቻ አይደለም፡፡ ዳግመኛም ሃይማኖት ምግባሩ የቀና ያ ደገኛ ባሕታዊ እመቤታችንን ‹‹ከምስጋናሽ ሁሉ ማንን ትወጃለሽ?›› ብሎ ቢጠይቃት እርሷም ‹‹ልጄ ዳዊትን፣ አቡነ ዘበሰማያትን ቢደግሙለት እንዲወድ እኔም ውዳሴዬን ቅዳሴዬን ቢደግሙልኝ ወዳለሁ›› ብላዋለች፡፡
አባ ሕርያቆስ የብርሃን እናቱ እመቤታችን ድንቅ ምሥጢርን ከገለጠችለትና ከባረከችው በኋላ በዘመኑ ቁጥር አንድ ሊቅ ሆኖ እጅግ ብዙ ድርሳናትን ደርሷል፡፡ ቁጥራቸው እጅግ የበዙ ተግሣጻትን ጽፏል፡፡ አጠቃላይ ድርሰቶቹ ከ10 ሺህ በላይ ናቸው፡፡ በእንዲህ ያለ ንጽሕናና ቅድስና ሲያገለግል ኖሮ ጥቅምት 2 በሰላም ዐርፏል፡፡
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ: ፍቅሯ: ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን::https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ግንቦት_1
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
በግንቦት አንድ በዚህችም ቀን አምላክን የወለደች #እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ተወለደች፣ የከበረ #አባ_ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ የእመቤታችንን ቅዳሴ የደረሰበት ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ልደታ_ለማርያም
በግንቦት አንድ በዚህችም ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኀነት የሆነባት ናት። ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ። ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ በዚያ ወራት የመካኖችን መብዓ ካህናቱ አይቅበሉም ነበርና።
እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር። ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ኀሳባቸውን ተመለከተ።
ክቡር እያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኀነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው።
በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ ለተመሰገነች ሚስቱ ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት ቃሉ እውነት እንደሆነ እርሷም አመነች ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገኑት።
የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርገው ዘንድ ለእግዚአብሔር ስለትን ተሳለች። ከዚህም በኋላ ይቺን የከበረች ሕፃን ፀንሳ ወለደች ስሟንም ማርያም ብላ ሰየመቻት ትርጓሜውም እመቤት ነው ደግሞም ሀብትና ስጦታ ማለት ነው።
በእውነት የዓለሙ ሁሉ እመቤት ናት ሁላችን በእርሷ ሰማያዊ ሀብት ልጅነትን ያገኘንባት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የሥጋና የነፍስ መድኃኒት የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አቡነ_ሕርያቆስ_ዘብሕንሳ
በዚህች ቀን የከበረ አቡነ ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ የእመቤታችንን ቅዳሴ የደረሰበት ነው፡፡ ሕርያቆስ ማለት ‹‹ኅሩይ-የተመረጠ›› ማለት ነው፡፡ እንዲሁም ደግሞ ምሥጢረ ሥላሴን ከሁሉ ይልቅ አራቆ ይናገራልና አባቶቻን ሕርያቆስ ማለት ‹‹ረቂቅ›› ማለት ነው ይሉታል፡፡ ‹‹አብ ፀሐይ ወልድ ፀሐይ መንፈስ ቅዱስ ፀሐይ›› ብሎ አመስግኗልና አሁንም ሕርያቆስ ማለት ‹‹ፀሐይ›› ማለት ነው ይሉታል፡፡ ደግሞም የምእመናንን ልቡና በትምህርቱ ብሩህ አድርጓልና ሕርያቆስ ማለት ‹‹ብርሃን›› ማለት ነው፡፡ አንድም ደግሞ ሕርያቆስ ማለት ‹ንብ› ማለት ነው፡፡ ንብ የማትቀምሰው አበባ እንደሌለ ሁሉ ሕርያቆስም ያልቀሰመው ሰማያዊ ዕውቀት የለምና እርሱን የማይጠቅሰው ሊቅ የለም፡፡
አባ ሕርያቆስ ስለ ምሥጢረ ሥላሴ እና ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ የሚያመሰጥረውን እመቤታችንን በተለያዩ ምሳሌያት እየመሰለ የሚያመሰግንበትን ድንቅ የሆነውን ድርሰቱን ‹‹ቅዳሴ ማርያምን›› ሰማያዊ ምሥጢር ወለል ብሎ ተከፍቶለት ደርሶታል፡፡ የብሕንሳው ኤዺስቆዾስ ስላረፉ በእሳቸው ምትክ የሚሾሙትን ሲያፈላልጉ መንፈስ ቅዱስ አባ ሕርያቆስን መረጣቸው፡፡ የከበሩ ሐዋርያት ‹‹የተማረና ግብረ ገብ የሆነ ይሾም›› ብለው ሥርዓት ሠርተዋል፡፡ ደግሞም ‹‹ሁለቱን አስተባብሮ የያዘ ባይገኝ የተማረ ከሆነ ይሾም›› ብለዋል፡፡ ምክንያቱም በትምህርቱ መናፍቃንን ተከራክሮ ይመልሳልና ነው፡፡ ደግሞም ‹‹ግብረ ገብም ከሆነ ይሾም›› ብለዋል፡፡ ምክንያቱም በጸሎቱ ይጠብቃል በትሩፋቱ ያጸድቃልና ነው፡፡ በዚህም መሠረት አባ ሕርያቆስ ያልተማረ ነገር ግን ግብረ ገብ ነውና ‹‹ትምህርቱን ውሎ አድሮ ያደርገዋል›› ብለው ሾሙት፡፡ አባ ሕርያቆስም የተማረው ለጸሎት ለቅዳሴ ያህል ትንሽ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ይህ ቅዱስ አባት በብሕንሳ ገዳም በ10000 መነኮሳት እና በ10000 መነኮሳይያት ላይ ተሹሞ የገዳሙ አስተዳዳሪ ሆነ፡፡
አባ ሕርያቆስ እመቤታችንን እጅግ ከመውደዱ የተነሣ ስሟን እንኳን ሲጠራ በመስጦ ልቡናው ይሰወርበት ነበር፡፡ ዘወትር ፍቅሯ ከማሰብ በቀር ሌላም አያስብም ነበር፡፡ እርሱ የነበረበት ዘመን የሊቃውንት ዘመን ስለነበር ሁሉም ለትምህርት ሲተጉ አባ ሕርያቆስ ግን ለጸሎትና ለደግነት ብቻ ይተጋ ነበር፡፡ የአባ ሕርያቆስ የሌት ተቀን ሞኞቱ ‹‹እንደ ቅዱስ ኤፍሬም የእመቤታችን ምስጋና እንደ ባሕር አሸዋ እንደ ሰማይ ኮከብ በዝቶልኝ እንደልብስ ለብሼም እንደ ምግብ ተመግቤው›› የሚል ነበር፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮም እጅግ ስለሚወዳት እመቤታችንም ትጠብቀው ነበር፡፡ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባ ሕርያቆስ በበረኃ ብቻውን እየተጓዘ ሳለ የእመቤታችንን ፍቅር በልቡ ሲያመላልስ ስሟን እያነሣ ሲዘምር በተመሥጦ ውስጥ ሆኖ መንገድ ሳተና ከታላቅ ገደል ጫፍ ደርሶ ሳያስበው ወደቀ፡፡ ከገደሉም ጫፍ ደርሶ ከወደቀ በኋላ እጅግ ደንግጦ ራሱን ቢመለከት አካሉ ሳይጎድል ልብሱ ሳይቆሽሽ አገኘው፡፡ በዚህም ተገርሞ ያለበትን አካባቢውን ቢያማትር ራሱን ብርሃንን በተሞላ የልብስ ዘርፍ ላይ አገኘው፡፡ ያም ብርሃንን የተሞላ የልብስ ዘርፍ የእመቤታችን የቀሚሷ ዘርፍ ነው፡፡ በዚህም እጅግ ደንግጦ ‹‹እመ ብርሃን›› ብሎ ጮኸ፡፡ እመቤታችንም ከፊቱ ቁማ ተገለጠችለት፡፡ እርሱም የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክን በገሃድ በዐይኑ አጠገቡ ቆማ ቢያያት በደስታ ዘለለ፡፡ እመቤታችንም በቃሏ አነጋግራው ባርካው ተሰወረችው፡፡ እርሱም ፍቅሯ ጣዕሟ ቢመስጠው ከሰው ሳይገናኝ ምግብም ሳይበላ እዚያው እገደሉ ውስጥ አንድ ዓመት በምስጋና ብቻ በተመስጦ ኖሯል፡፡ በኋላም እመቤታችን ድጋሚ ተገልጣለት ከገደሉ አውጥታ ወደ ሀገሩ አድርሳዋለች፡፡
ከዚህም በኋላ አባ ሕርያቆስ እርሱ በተሾመባ በብሕንሳ ገዳም ሴትና ወንድ ያልተለየባት ገዳም ነበረችና በዚህች ገዳም የተሾመው አባ ሕርያቆስ ብዙም ትምህርት ስላልነበረው ይንቁት ነበር፡፡ ‹‹ከመጠምጠም መማር ይቅደም›› እንዲሉ ‹‹ከመሾም በፊት መማር አይቀድምም›› እያሉም ይዘብቱበት ነበር፡፡ እርሱ ግን እንደጠሉኝ ልጥላቸው ሳይል በፍቅር በትሕትና ይመክራቸው ነበር፡፡ እነርሱ ግን ‹‹በምን ምክንያት እንሻረው›› እያሉ ይመክሩ ነበር፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ‹‹ቀድሰህ አቁርበን እንበለውና አይሆንም ካለን በዚህ ምክንያት እንሻረው?›› ብለው መከሩ፡፡ እርሱም ሥርዓተ ቅዳሴውን ፈጽሞ ወደፍሬ ቅዳሴው ሲደርስ የትኛውን ከባድ ቅዳሴ ቀድስ እንበለው?›› እያሉ ይመካከሩ ጀመር፡፡ እርሱ ግን ከቅዳሴ ሐዋርያት በቀር የሚያውቀው አልነበረም፡፡ አባ ሕርያቆስ እያዘነ ወደ መንበሩ ዞሮ ‹‹እመቤቴ ሆይ! መናቄን መገፋቴን ተመልከች›› ሲል ወዲያው እመቤታችን ወርዳ ጠራችውና በዘርፋፋው ቀሚሷ ላይ ረቂቅ የሆነ ቅዳሴን አሳየችው፡፡ የለመኗትን የማትነሣ፣ የነገሯትን የማትረሣ የብርሃን እናቱ እመቤታችንም የልቡን መሻት ተመልክታ ‹‹ጎስዐ ልብየ ቃለ ሠናየ ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ›› በማለት ጀምሮ ‹‹ዛሬም አብን ወልድንና መንፈስ ቅዱስን እናመስግን›› እስከሚለው ድረስ ሰተት አድርጋ አስደርሳዋለች፡፡ እነርሱም ይህንን ግሩም የሆነውን ቅዳሴውን አደነቁ፡፡
🔴#ሚያዝያ_30
#ቅዱስ_ማርቆስ_ሐዋርያ
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ሠላሳ በዚች ቀን ለእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳት አለቃ የሆነ ወንጌልን የጻፈ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት አረፈ።
የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አርስጦቡሎስ ነው እርሱም ከአምስቱ አገሮች የሆነ የእናቱም ስም ማርያም ነው እርሷም በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ተጽፋለች እርሱም አስቀድሞ ስሙ ዮሐንስ ነው። በግብረ ሐዋርያት ማርቆስ በተባለ በዮሐንስ እናት ቤት ሐዋርያት ይጸልዩ ነበር ተብሎ እንደ ተጻፈ። እርሷም ባለጸጋ ነበረችና የዮናናውያንን የሮማይስጥን የዕብራይስጥን ትምህርት ለልጅዋ ለማርቆስ አስተማረችው።
በአደገም ጊዜ በርናባስ ወንጌልን ለመስበክ ከጳውሎስ ጋራ ሲሔድ ይዞት ሔደ በእነርሱም ላይ የሚደርስባቸውን መከራ አይቶ በጵንፍልያ ከተማ ሳሉ ትቷቸው ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።
ሐዋርያትም በተመለሱ ጊዜ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ማመን አሕዛብ እንደ ተመለሱ እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ላይ ድንቅ ተአምራትን እንዳደረገ ተናገሩ። ይህ ብላቴና ማርቆስም ከእርሳቸው ስለ መለየቱ አዘነ ተጸጸተ።
ከዚያም አብሮአቸው ሊሔድ ፈለገ አስቀድሞ ትቷቸው ስለተመለሰ ጳውሎስ ሊአስከትለው አልወደደም በርናባስ ግን ወሰደው አጎቱ ነውና። በርናባስም ከአረፈ በኋላ ወደ ሮሜ አገር ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ ሒዶ ለእርሱ ደቀ መዝሙሩ ሆነ በዚያም ቅዱስ ጴጥሮስ የተረጐመለትን ወንጌልን ጻፈ በሮሜ አገርም አስተማረበት። ከዚያም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዝና በሐዋርያትም ትእዛዝ ወደ እስክንድርያ አገር ሔደ። በውስጥዋም የከበረ ወንጌልን አስተማረ ደግሞም በአፍራቅያና በአምስቱ አገሮች በርቃ በሚባልም አገር ወደ እስክንድርያ ከተማ በገባ ጊዜ ጫማው ተቆረጠ።
በዚያም በከተማው መግቢያ ጫማ ሰፊ ነበረ። ቅዱስ ማርቆስም እንዲሰፋለት ለርሱ ሰጠው ሲሰፋም ጣቱን ወግቶ ሰነጠቀው ከእርሱም ደም ፈሰሰ በዮናኒም ቋንቋ ኢታስታዖስ አለ ትርጓሜውም አንድ እግዚአብሔር ማለት ነው። ቅዱስ ማርቆስም ስሙን የምትጠራው አውቀኸው ነውን አለው እንጠራዋለን እንጂ አናውቀውም አለ።
እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ከፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ አባታችን አዳም ትእዛዙን እንደተላለፈ የጥፋት ውኃም እንደ መጣ ሙሴንም እንደላከውና እስራኤልን ከግብጽ እንዳወጣቸው ሕግንም እንደ ሠራላቸው ናቡከደነጾርም ወደ ባቢሎን ማርኮ እንደወሰዳቸውና ከሰባ ዓመት በኋላ ወደ አገራቸው ኢየሩሳሌም እንደ ተመለሱ ክርስቶስ ሥጋ በመልበስ ወደ ዓለም ስለ መምጣቱ ነቢያት ትንቢት እንደ ተናገሩ ያስተምረው ዘንድ ጀመረ።
ከዚያም በኋላ ወደ ምድር ምራቁን ትፍ ብሎ ጭቃ አድርጎ ጣቱን ቀባው ወዲያው ዳነ በጌታችንም አመነ። ያም ሰፊ ስሙ አንያኖስ ነው። ቅዱስ ማርቆስንም ወደ ቤቱ ወስዶ ልጆቹን ዘመዶቹንም ወደ ርሱ አቀረበ እርሱም አስተምሮ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው።
በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያመኑ ሰዎች በበዙ ጊዜ የቅዱስ ማርቆስን ዜና ሰምተው የአገር ሰዎች ሊገድሉት ተሰበሰቡ እርሱም አንያኖስን ኤጲስቆጶስ አድርጎ ሹሞ ልጆቹን ቄሶችና ዲያቆኖች አድርጎ ከዚያም ወደ በርቃ ወደ አምስቱ አገሮችም ወጥቶ አስተማረ። በቀናች ሃይማኖትም አጸናቸው በእርሳቸውም ዘንድ ሁለት ዓመት ኖረ ኤጲስቆጶሳትን ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ሾመላቸው።
ከዚህም በኋላ ወደ እስክንድርያ ተመለሰ ምእመናንም ተጨምረው በዝተው በታወቁ ቦታዎች ሁሉ በባሕሩም ዳር በላሞች መካበቢያ በሚባለውም አብያተ ክርስቲያን ሠርተው አገኛቸው።
ከሀድያንም የከበረ ሐዋርያን ይገድሉት ዘንድ በብዙ ድካም ፈለጉት እርሱም አምስቱን አገሮች ሲጐበኝ በሥውር ወደ እስክንድርያ ከተማ ይገባ ይወጣ ነበር። በአንዲትም ዓመትም ከአምስቱ አገሮች ተመልሶ ሚያዝያ ዐሥራ ሰባት ቀን በመድኃኒታችን የትንሣኤ በዓል ወደ ቤተክርስቲያን ገባ ሕዝቡም ሁሉ በዙሪያው አሉ። ከሀድያንም ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብተው በአንገቱ ውስጥ ገመዶችን አድርገው በከተማው ሁሉ ጎተቱት። እነርሱም ገና እንደፍየል ሙክት እንጎትተዋለን እያሉ ይጮኹ ነበር። በላሞች መካበቢያና በሀገሪቱ አደባባይ በከተማውም ዙሪያ በየቀኑ ሲጎትቱት ኖሩ።
ሌሊትም በሆነ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሐዋርያት ጋራ በነበረበት አርአያ ሁኖ ተገለጠለት ሰላምታም ሰጥቶ አጽናናው ቃል ኪዳንም ሰጠው። እነሆ አንተ ከወንድሞችህ ሐዋርያት ጋር ተካከልህ አለው። እርሱም በልቡናው ፈጽሞ ደስ አለው። በማግሥቱም ሁለተኛ ገመዶችን በአንገቱ አድርገው በአገሮች ሁሉ ጎተቱት በቀኑም መጨረሻ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።
ከሀዲዎችም ታላቅ እሳትን አንድደው የቅዱስ ማርቆስን ሥጋ ከውስጡ ጨመሩ። በክብር ባለቤት ጌታችን ፈቃድም ንውጽውጽታ ጨለማ ቀዝቃዛ ነፋስ መብረቅና ነጐድጓድ ሆነ። ፀሐይም ጨለመ ከሀዲዎችም ሸሹ ምእመናንም መጥተው የሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስን ሥጋ ወሰዱ ምንም ጥፋት ሳይደርስበት ደኀና ሆኖ አገኙት በመልካም ልብስም ገንዘው በጥሩ ቦታ አኖሩት መታሰቢያውንም አደረጉ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ማርቆስ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን።https://t.me/finotebirhan12
ቲኬቱን ቀድመው በመግዛትና በጉባኤው ላይ በመገኘት ነፍስዎን ይመግቡ።
🔴#ስንክሳር ሚያዝያ_29
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ሃያ ዘጠኝ በዚህች ዕለት ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ #ሐዋርያ_አርስጦስ አረፈ፣ የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ #አባ_አካክዮስ አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ሐዋርያው_አርስጦስ
ሚያዝያ ሃያ ዘጠኝ በዚህች ዕለት ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ ሐዋርያ አርስጦስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከሐዋርያት ጋራ በጽርሐ ጽዮን የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ከተቀበለ በኋላ በሀገሩ ሁሉ ቋንቋ ተናገረ። ሐዋርያትንም እያገለገለ ከእሳቸው ጋራ ሲሰብክ ብዙ ጊዜ መከራ ተቀበለ።
ከዚያም በኋላ ሐዋርያት መርጠው ለኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ሾሙት። በዚችም አገልግሎት ጥቂት ቆይቶ ብናጥስ በሚባል አገር ላይ ሁለተኛ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት።
በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በውስጥዋ አስተምሮ አንድነትንና ሦስትነትን በማሳወቅ የሰዎቿን ልቡና ብሩህ አደረገ። የጣዖታትንም ቤቶች አፍርሶ አብያተ ክርስቲያንን ሠራ በክብር ባለቤት በጌታችንም ስም አጸናቸው።
ታላላቅ አስደናቂ ተአምራትን በማድረግ መራራ የሆኑ ውኃዎችን ለውጦ ጣፋጮች አደረጋቸው የደረቁ እንጨቶችንም እንዲያለመልሙና እንዲአፈሩ አደረጋቸው። በደዌ የተጨነቁ ብዙ በሽተኞችንም አዳነ ወደ በጎ እርጅና ደርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ። እነሆ ሐዋርያው ጳውሎስ በመልእክቱ አስታውሶታል፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_አካክዮስ
በዚህችም ቀን ንጹሕ ደግ ቅን የሆነ የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ አባ አካክዮስ አረፈ። ይህንንም ቅዱስ ከሀድያን ብዙ ቀኖች አሠቃዩት እግዚአብሔርም በእጆቹ ብዙ ተአምራትን አደረገ ከዚህም በኋላ በፍቅር አንድነት አረፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን ።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ሚያዝያ_28
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ሃያ ስምንት በዚች ቀን በኮራሳት ተራራ በገድል ተጠምዶ የሚኖር #ቅዱስ_ሜልዮስ በሰማዕትነት አረፈ፣ መቅሱር ከሚባል አገር #ቅዱስ_ብስጣውሮስ በሰማዕትነት አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ሜልዮስ_ዘደብረ_ኮራሳን
ሚያዝያ ሃያ ስምንት በዚች ቀን በኮራሳት ተራራ በገድል ተጠምዶ የሚኖር ቅዱስ ሜልዮስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም አባት ኮራሳት በሚባል አገር በተራራ ባሉ ዋሻዎች ከሁለት አርድእቱ ጋራ ይኖር ነበር።
የኮራሳት ንጉሥ ሁለቱ ልጆቹ ወደዚያ ወጡ ከእርሳቸውም ጋራ አገልጋዮች አሉ አራዊትን አጥምደው በፍላፃዎች ይገሉ ዘንድ መረባቸውን ተክለው አርባ ምዕራፍ ያህል ሔዱ። መረቡን በጠቀለሉት ጊዜ ይህን ቅዱስ አባት ማቅ ለብሶ ጠጉሩም የረዘመ ሁኖ አገኙት።
የንጉሥ ልጆችም በአዩት ጊዜ ፈሩ አንተ ሰው ነህን ወይም መንፈስ ብለው ጠየቁት እርሱም በዚህ ተራራ ውስጥ የምኖር ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የምሰግድ ሰው ነኝ ብሎ መለሰላቸው።
እነርሱም ከእሳትና ከፀሐይ በቀር አምላክ የለም እንዳንገድልህ ሠዋላቸው አሉት። እርሱም እሳትና ፀሐይ የተፈጠሩ ናቸው እናንተም ተሳስታችኋል ፍጥረቶችን በፈጠረ በዕውነተኛ አምላክ ታምኑ ዘንድ እኔ እለምናችኋለሁ ብሎ መለሰላቸው።
በዚያን ጊዜ ይህን አባት ሁለቱን አርድእትም ይዘው ጽኑ ሥቃይ አሠቃዩአቸው በዚህ ወር በዐሥራ ሦስት የሁለቱን አርድእት ራሳቸውን ቆረጡአቸው የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ።
አረጋዊ ቅዱስ ሜልዮስን ግን ዐሥራ አምስት ቀን ያህል ሲአሠቃዩት ኖሩ ከዚህ በኋላ በመካከላቸው አቆሙት አንዱ በፊት አንዱ በኋላ ሁነው በፍላፃ ይነድፉት ጀመር። እርሱም በእናንተ ላይ ክፉ ያልሠራውን ለመግደል ሁለታችሁ ስለተስማማችሁ እንዲሁ እንደሥራችሁ በፍላፃችሁ ነገ ትሞታላችሁ አላቸው። ሰምተውም አልፈሩም ነፍሱን እስከሚአሳልፍና ምስክርም ሆኖ የሰማዕትነት አክሊልን እስከሚቀበል ነደፉት እንጂ።
በማግሥቱም እንደልማዳቸው ለአደን ወጡ የዱር አህያም አገኙ ተከትለውም ቀስታቸውን አስፈነጠሩ እግዚአብሔርም ፍላፃቸውን ወደልባቸው መለስ ቅዱስ ሜልዮስም እንደተናገረባቸው ሞቱ።
በዚህ ቅዱስም እጅ ጌታችን ተአምራትን ገለጠ በአንዲት ዕለትም አልፎ ሲሔድ በመንገድ ላይ የሞተ ሰው አገኘ የአገር ሰዎች ግን አንዱን መነኰስ አንተ ነህ የገደልከው ብለው ያዙት። ቅዱስ ሜልዮስም ጸለየ የሞተውንም በውኑ የገደለህ ይህ መነኵሴ ነውን አለው ያን ጊዜ የሞተው ተነሥቶ እርሱስ አልገደለኝም ነገር ግን ብዙ ገንዘቤን ከአንድ ቄስ ዘንድ አደራ አስጠበቅሁ ስለዚህ ገደለኝ ከዚህም ጣለኝ አለ ደግሞ እንዲህ ብሎ ለመነው ዕገሌ ወደሚባል ወደዚያ ቄስ ሒደህ ገንዘቤን ከርሱ ተቀብለህ ለልጆቼ ስጥ ቅዱስ ሜልዮስም እስከ ትንሣኤ ቀን በሰላም አርፈህ ተኛ እኔ ገንዘብ አከፋፋይ ዳኛ አይደለሁም አለው ያንጊዜም ተኛ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ብስጣውሮስ
በዚህችም ቀን መቅሱር ከሚባል አገር ቅዱስ ብስጣውሮስ በሰማዕትነት አረፈ። የዚህም ቅዱስ አባቱ ጻድቅ ሰው ነው እናቱን ግን ሰይጣን አስቷት ወደ እስልምና ገባች እርሱም ፈሪሀ እግዚአብሔርን እየተማረ እስከሚጐለምስ አደገ አካለ መጠንም አድርሶ ሚስት አገባ ከርሷም ልጆችን ወለደ።
ብዙ ዘመናትም በአለፉ ጊዜ አንገተ ደንዳና በቀለኛ ሰው በእርሱ ላይ ተነሥቶበት ወደ እስላሞች መኳንንት ሒዶ ሰው ወደ እኛ ሕግ ቢገባ ልጆቹም ሃይማኖቱን ይከተላሉ ይህ ብስጣውሮስ ግን ከሕጋችን የተለየ ነው ብሎ ነገር ሠራበት።
የእስላሞች ዳኞችም በሰሙ ጊዜ መልዕክተኞች ልከው ወደርሳቸው ወደ ሸንጎ አቀረቡት ስለ ሃይማኖቱም ጠየቁት ክርስቲያን እንደሆነ ያለ ፍርሀት ክርስቲያን ነኝ ብሎ ታመነ።
ዳኛው ግን ይሸነግለው ዘንድ በፍቅር ይናገረው ጀመረ ከከበረችና ከቀናች ሃይማኖቱ ይመልሰው ዘንድ ብዙ ስጦታዎችን እንደሚሰጠው ቃል ገባለት ቅዱሱ ግን ከቶ አልተመለሰም ወደ ስጦታውም ከቶ ልቡ አላዘነበለም።
ከዚህ በኋላ ወደ ግዞት ቤት ወስደው በእግረሙቅ እንዲአሥሩት በአንገቱም የተበሳ ታላቅ ግንድ አሥረው በግንባሩ ደፍተው በኲስ ላይ እንዲጥሉት መኰንኑ አዘዘ። እንዲሁም አደረጉበት እስከ ሦስት ቀን በእሥር ቤትም ሳለ ፀዐዳ ርግብ መጥቶ ጋረደው ስለዚህም የእሥር ቤቱ ጠባቂ ምስክር ሆነ።
ከዚህም በኋላ ዳኞች ወደ ሸንጎ አስቀርበው ከእንግዲህ አንታገሥህም ወደ ሃይማኖታችን ከምትገባና ወይም በእሳት ከምናቃጥልህ ምረጥ አሉት። እርሱም እኔ ከእናንተ ጋራ ለዘላለሙ ዕድል ፈንታ የለኝምና የወደዳችሁትን አድርጉ ብሎ መለሰላቸው።
በዚያን ጊዜም እጅግ ተቆጡ ያለ ርኀራኄ ይደበድቡት ዘንድ አዘዙ ያገር ሰዎችም በጫማቸው መቱት አንዲት ሴትም መጥታ በጫማዋ መታችው ወዲያውኑ እጆቿ ደረቁ።
ከዚህም በኋላ ባለ ሰይፍ ከመኰንኑ ታዝዞ ወጣ ሰይፉንም መዝዞ ሳያቋርጥ መላልሶ አንገቱን መታው። ምቱም ወደ ጐን ሒዶ ጆሮውን ቆረጠው አመታቱ ክፉ ስለ ሆነ ከሥሮቿ ብዙ ደም ፈሰሰ።
ከዚህም ደግሞ ተዉት ወደ እምነታቸው ሊአስገቡት እምቢ በአላቸውም ጊዜ ሁለተኛ ሰይፉን መዝዞ ሰያፊው የከበረች አንገቱን ቆረጠው በመንግሥተ ሰማያትም የምስክርነት አክሊልን ተቀበለ። ሥጋውንም ከእሳት ጨመሩ ግን አልተቃጠለም። ዘመዶቹም መጥተው በድኑን ወደአገሩ ወሰዱ። በቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ ጐን ቀበሩት። የክብር ባለቤት ጌታችንም ብዙ ድንቆች ተአምራትን ከሥጋው ገለጠ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም ቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ሚያዝያ_27
#ቅዱስ_ፊቅጦር_ሰማዕት
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ሃያ ሰባት በዚች ቀን የከበረ ቅዱስ ፊቅጦር በሰማዕትነት አረፈ። ለዚህ ቅዱስ የአባቱ ስም ኀርማኖስ ነው እርሱም ለዲዮቅልጥያኖስ የአማካሪዎቹና የሰራዊቱ አለቃ ነው ስለ አምልኮ ጣዖት ሥራ ምክሩና ንግግሩ ሁሉ ከእርሱ ጋራ ነበር የእናቱም ስም ማርታ ይባላል በክርስትናዋ የጸናች ብፅዕት ናት።
ቅዱስ ፊቅጦርም በአደገ ጊዜ አባቱ ወደ ንጉሥ አቀረበው ንጉሡም በመንግሥቱ ውስጥ ሦስተኛ ማዕርግ አድርጎ ሾመው በዚያን ጊዜ ዕድሜው ሃያ ዓመት ነበረ። እርሱም የዚህን ዓለም ክብር ናቀ ሥጋ አይበላም ወይን አይጠጣም ዘወትርም ይጾማል ጸሎትንም ባለማቋረጥ በቀንና በሌሊት ይጸልያል።
በክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም የታሠሩትን ይጐበኛቸዋል ለድኆችና ለምስኪኖችም ይመጸውታል። የቅዱሳን ቆዝሞስና ድምያኖስ እናት ቅድስት ቴዎዳዳን በገደሉዋት ጊዜ ንጉሡን ስለ መፍራት ሊቀብራት ማንም አልደፈረም። ይህ ቅዱስ ፊቅጦርም መጥቶ ሥጋዋን ወሰደ ከንጉሥ ስለሚመጣው ቅጣት ሳይፈራ ቀበራት። ጣዖት ስለ ማምለኩ አባቱን ዘወትር የሚገሥጸውና ብዙ ጊዜም የሚመክረው ሆነ አባቱም ወደ ንጉሥ ከሰሰው እንጂ አልሰማውም።
ተከሶም ወደ ንጉሥ በአቀረቡት ጊዜ አማልክት ያልሆኑ ርኲሳን ጣዖታትን ለሚያመልክ ሰነፍ ዝንጉ ልብ የለሽ ለሆነ ንጉሥ አላገለግልም። ከዛሬ ጀምሮ ለሕያው ንጉሥ ክርስቶስ እገዛለሁ የሰጠኸኝንም ገንዘብህን ንሣ ብሎ ከፊቱ ትጥቁን ፈትቶ ጣለላት።
አባቱ ኀርማኖስም ወደ እስክንድርያ እንዲልከውና በኄርሜኔዎስ መኰንን ዘንድ በዚያ ፊቅጦር እንዲቀጣ ንጉሡን መከረው። በዚያን ጊዜም ከአደባባይ አወጡት እናቱም በብዙ ልቅሶ ልትሸኘው መጣች።
እርሱም ሲመግባቸው ስለ ነበሩ የታሠሩ ምእመናን ስለ ድኆችና ምስኪኖች ስለ ሙት ልጆችና ስለ ባልቴቶች የሚሹትን በመስጠት እንድትጐበኛቸው አዘዛት ከዚያም አፉን ለጉመው ወሰዱት።
በእስክንድርያ አገር ወደ መኰንኑ ኄርሜኔዎስ ዘንድ በደረሰ ጊዜ ታላቅ ሥቃይን አሠቃዩት የእግዚአብሔርም መልአክ ወደ ሰማያት አውጥቶ ስለ ክብራቸው ለመናገር የሚያስጨንቁ የብርሃን ማደሪያዎችን አሳይቶ ወደ መኖሪያው መለሰው።
መኰንኑም በእሳት በአፈሉት በዝፍት በዲን ደግሞ አሠቃየው ከዚያም በብረት አልጋ ላይ አስተኝተው ከበታቹ እሳትን አነደዱ። ደግመው ከውሽባ ማንደጃ ውስጥ ጨመሩት በየአይነቱ በሆነ ሥቃይም አሠቃዩት የክብር ባለቤት ጌታችንም ያጸናውና ከሥቃዩ ያስታግሠው መልአኩንም ልኮ ከቁስሉ ይፈውሰው ነበር።
ከዚህም በኋላ ወደ እንዴናው ከተማ ላከው በዚያም ታላቅ ሥቃይን አሠቃዩት ምላሱን ቆረጡ። በእሳት ያጋሉዋቸውን ችንካሮች በጐኖቹ ውስጥ ጨመሩ እግዚአብሔር ግን አጽንቶ አስታግሦ ያለ ጉዳት በደኀና ያነሣዋል።
ከዚህም በኋላ በዚያ በረኃብ እንዲሞት ከዱር ባለ ግምብ ውስጥ አሠሩት። እርሱ ግን መጥረብ የሚያውቅ ስለሆነ ላይዳዎችን በመጥረብና በመሸጥ በየጥቂቱ እየተመገበ የቀረውን ለድኆች እየሰጠ ኖረ።
አንድ መኰንንም መጥቶ በዚያ ግምብ አቅራቢያ አደረ ስለ ቅዱስ ፊቅጦርም እርሱ የንጉሥ የሠራዊት አለቃ የሆነ የኀርማኖስ ልጅ እንደሆነ ነገሩት።
መኰንኑም ወደርሱ አቅርቦ ብዙ ሸነገለው ባልሰማውም ጊዜ ያሠቃዩት ዘንድ አዘዘ ጅማቶቹን መዘዙ አፉን መቱት ቊልቊል ሰቅለው በእጆቹ ላይ ከባድ ደንጊያ አንጠለጠሉ። ከዚያም ከሚነድ እሳት ውስጥ ጨመሩት ሙጫ አደሮ ማርና ዘይትን አፍልተው በላዮ ደፉበት በማበራያም አበራዩት አፉንም በአሞትና በእሬት አመረሩት ዐይኖቹንም አወለቁት ደግመውም ዘቅዝቀው ሰቀሉት። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ተገልጾለት አጸናው አረጋጋው። ሥሮቹንና ሕዋሳቶቹን በቦታቸው መለሰለትና አዳነው።
አንዲት ዓሥራ አምስት ዓመት የሆናት ብላቴና ነበረች ቅዱስ ፊቅጦርን ሲአሠቃዩት በቤቷ መስኮት ታየው ነበር። መላእክትንም በእጆቻቸው አክሊሎችን ይዘው እነርሱም በቅዱስ ፊቅጦር ራስ ላይ ሲያኖሩአቸው አይታ እንዴት እንዳየች ለአሕዛብ ነገረቻቸው እጅግም አደነቁ። ከእርሳቸውም ብዙዎች በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በሰማዕትነት አረፉ፡፡፡ ያቺም ብላቴና በጌታችን አመነች መኰንኑም ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ። የሕይወት አክሊልንም ተቀበለች ሁለተኛም የአመኑትን ሁሉ ራሳቸውን እንዲቆርጡአቸው አዘዘ የሕይወትንም አክሊል ተቀበሉ።
ከዚህም በኋላ የከበረች የቅዱስ ፊቅጦርን ራስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ተጋድሎውንም ፈጽሞ የሕይወትና የድል አክሊልን ተቀበለ።
ምእመናን ሰዎችም ሥጋውን ወስደው በከበሩ ልብሶች በድርብ በፍታ ገነዙት። እናቱ ማርታም ከአንጾኪያ እስክትመጣ በንጹህ ቦታ አኖሩት በመጣችም ጊዜ ከዚያ ወሰደችው። ውብ ቤተ ክርስቲያንም ሠርታ ሥጋውን በውስጥዋ አኖረች ከእርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ሚያዝያ_26
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ሃያ ስድስት በዚህች ቀን የሱሲ ልጅ #ቅዱስ_ሱስንዮስ በሰማዕትነት አረፈ፣የጠራቢ ልጅ #ቅዱስ_ዮሐንስ በሰማዕትነት አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ሱስንዮስ
ሚያዝያ ሃያ ስድስት በዚህች ቀን የሱሲ ልጅ ሱስንዮስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም የከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ወዳጅ ነበረ። የእግዚአብሔር መልአክም ተገለጠለትና ሰማዕት እንደሚሆን ነገረው ይህም ነገር በልቡ አደረ።
ከዚህም በኋላ አምልኮ ጣዖትን እንዲአስፋፉና እንዲአድሱ ከሹመት ደብዳቤ ጋራ ንጉሡ ወደ ኒቆምድያ ላከው። ቅዱሱም አይቶ እጅግ አዘነ ከዚያም ወደርሱ አንድ ቄስ አምጥቶ የክርስትናን ትምህርት ተምሮ ተጠመቀ።
ከዚህ በኋላም ወደ አንጾኪያ ተመለሰ ፍጥረቱ ልዩ የሆነ ልጅን ወልዳ እኀቱን አገኛት። ከዚህ በፊት ሴት ልጅ ወልዳ ገድላ ደሟን ጠጥታለች ሰይጣን አድሮባታልና በወፍና በከይሲ አምሳልም ይገለጣል በአገር ውስጥም ልጅ በሚወለድ ጊዜ ወደርሱ ወርዳ በሥራይም ገድላ ደሙን ትጠጣለች።
ቅዱስ ሱስንዮስም ይህን በአየ ጊዜ ጦሩን አንሥቶ ከልጅዋ ጋራ እኀቱን ገደላት ልጅዋ የሰይጣን ልጅ ነውና ሁለተኛም ሥራየኞች ስለሆኑ ባሏንና የባሏን አባቱን ገደላቸው እነርሱ በሥራያቸው ሰውን እያሳመሙ ይገድላሉና።
ከዚህም በኋለ ወደኒቆምድያ ተመልሶ ወደዚያ ወደ አጠመቀው ቄስ ደርሶ ያደረገውን ሁሉ ነገረው። ወደ አገሩ አንጾኪያም በተመለሰ ጊዜ ከእርሱ የሆነውን አባቱ ሱሲ አወቀ መገደሉንም ወዶ ከንጉሥ ዘንድ ነገር ሠራበት። ያን ጊዜም ቅዱስ ሱስንዮስ ወደ ጣዖታት ቤት ሒዶ ወደ ሲኦል ይወርዱ ዘንድ በጌታችን ኢየሱስ ስም አዘዛቸው ያን ጊዜም ምድር አፍዋን ከፍታ ዋጠቻቸው ጣዖታቱንም እንዳጠፋቸው ወሬው ተሰማ።
አባቱም ዳግመኛ በንጉሥ ዘንድ ከሰሰው ታላቅ ሥቃይም ያሠቃዩት ዘንድ ንጉሥ አዘዘ በብረት ዘንጎችም ደበደቡት በመንኰራኲርም አበራዩት በመዶሻም ቀጥቅጠው ሁለተኛ ደግመው እህል በሚአበራዩበት መሣሪያ አበራዩት። ከዚያም በከተማው ውስጥ ጐተቱት።
የክብር ባለቤት ጌታችንም ያጸናውና በሥቃዩም ውሰጥ ያስታግሠዋል ከቁስሉ የሚፈውሰውን መልአኩንም ልኮ ያለ ምንም ጉዳት አነሣው። ብዙ ሰዎችም አይተው በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በርሱ ምክንያት ሰማዕታት ሆኑ።
ንጉሥም ከማሠቃየቱ በደከመ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ። በሥቃዩም ወራት በሰማዕትነት የሞቱት ቍጥራቸው አንድ ሺህ አንድ መቶ ዘጠኝ ሆነ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ዮሐንስ_ሰማዕት
በዚህችም ቀን የጠራቢ ልጅ ቅዱስ ዮሐንስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ ከነነዌ አገር ነው አባቱ ጣዖትን የሚጠርብና የሚያመልክ ነው። እናቱ ግን ክርስቲያናዊት ናት ልጅ በአጣችም ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ለመነች ጌታም ልመናዋን ተቀብሎ ይህን የተባረከ ልጅ ሰጣት ስሙንም በሥውር ዮሐንስ ብላ ጠራችው።
ስምንት ዓመትም በሆነው ጊዜ የጠረበውን ጣዖት እየሸጠለት ኣባቱን ያገለግል ነበር። በአንዲት ዕለትም ጣዖቱን ሊሸጥ ሲሔድ የእግዚአብሔር መልአክ ተገናኘውና ጣዖት የሰይጣን ማደሪያ እንደሆነ ነገረው ጣዖቱንም ከእጁ እንዲጥለው አዘዘው በክብር ባለቤት በክርስቶስ ማመንን አስተማረው።
ወደ አባቱም በተመለሰ ጊዜ ሰማይና ምድርን በውስጣቸውም ያለውን ሁሉ ከፈጠረ ከክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም እኔ ለሰው እጅ ሥራ አልሰግድም አለው። አባቱም ሰምቶ በእሥር ቤት አሠረው እናቱም መጥታ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም ደሙን ያፈስ ዘንድ አጸናችው።
ከዚህም በኋላ በነገራቸው ሊሸነግሉት የአገር ሰዎች መጥተው የአባትህን አምላኮች ለምን ተውክ አሉት። እርሱም እኔ የሰው እጅ ለሠራቸው ጣዖቶች አልሰግድም አነርሱ የርኲሳን አጋንንት ማደሪያዎች ናቸውና አላቸው አባቱም ይህን በሰማ ጊዜ ምሳር አንሥቶ አንገቱን ቆረጠው በድኑም አልወደቀም በደሙ እስከተጠመቀ ድረስ በእግሮቹ ቆመ እንጂ።
እናቱም በደሙ ተጠምቃ አቤቱ የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የአቤልን መሥዋዕት በምድረበዳ የተቀበልክ ይህንን መሥዋዕት ከእኔ ተቀበል አለች። በዚያን ጊዜ በአባቱ ሰይጣን አደረበትና አበደ። ሚስቱም ወደ ልጅዋ መቃብር ወስዳው ስለርሱ ጸለየች ቅዱስ ዮሐንስም በሌሊት ወደርሱ መጥቶ አባቱን በጦር ወጋው ሰይጣኑም ከእርሱ ወጣ። ከዚህ በኋላም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነና በስሙ ተጠመቀ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ሰማዕታት ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ሚያዝያ_25
#ቅድስት_ሣራ
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ሃያ አምስት በዚች ቀን ቅድስት ሣራ ከሁለቱ ልጆቿ ጋራ በሰማዕትነት አረፈች፡፡ ይቺም ቅድስት ከአንጾኪያ አገር ናት እርስዋም ከዲዮቅልጥያኖስ መኳንንት ለአንዱ ስሙ ስቅራጥስ ለሚባል ሚስቱ ናት እርሱም በፊት ክርስቲያን ነበረ በኋላ ንጉሡን በመፍራት ካደ እርስዋ ግን በክርስትናዋ ጸንታ ኖረች።
ባልዋ ስቅራጥስም እኔ የክርስቲያንን ሃይማኖት እወዳለሁ የንጉሡን ሥቃይ ከመፍራት በቀር ክርስቶስን በልቤ አልካድኩትም ይላት ነበር። እንደዚህም ስትኖር ሁለት ልጆችንም ወለደች በአንጾኪያም አገር የክርስትና ጥምቀትን ልታስጠምቃቸው አልተቻላትም። አብያተ ክርስቲያናት ተዘግተዋልና ጠፍተዋልምና ሰውን ወዳድ ክርስቶስን ብዙ ስለመውደዷ ልጆቿን ታስጠምቃቸው ዘንድ ታላቅ ተጋድሎ አደረገች ወደ እስክንድርያ ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጴጥሮስ ልትሔድ ወዳ አሽከሮቿን አስከትላ ሁለቱን ልጆቿን ይዛ በመርከብ ተሳፈረች።
የክብር ባለቤት ጌታችንም የሃይማኖቷን ልዕልና ለመጪው ትውልድ ሊገልጥ ወዶ ያቺ መርከብ ለመሥጠም እስከምትደርስ በባሕር መካከል ጥቅል ነፋስን አስነሣ። ይቺ ቅድስትም ልጆቿ ሳይጠመቁ እንዳይሞቱ ፈራች ተነሥታም ጸለየች ከዚያም ምላጭ አንሥታ ጡቷን የቀኙን በጣች ከደሟም ወስዳ ፊታቸውን በመስቀል ምልክት ቀባች በደረታቸውና በጀርባቸውም ላይ እንዲሁ አደረገች በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በባሕሩ ውስጥ አጠመቀቻቸው ያን ጊዜም ታላቅ ጸጥታ ሆነ።
ወደ እስክንድርያ አገርም በደረሰች ጊዜ ከሀገር ልጆች ጋራ ያጠምቃቸው ዘንድ ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጴጥሮስ ልጆቿን አቀረበች በዚያን ጊዜም ከሀገር ልጆች አጠመቀ። ወደልጆቿም ደርሶ ሊአጠምቃቸው ወሰዳቸው ያን ጊዜ ውኃው ረጋ እነርሱን ትቶ ከአገር ልጆች አጠመቀ ውኃውም ተፈትቶ ወረደ ደግሞ ሊአጠምቃቸው ወደ ልጆቿ ተመለሰ አሁንም እንደቀድሞው ውኃው ረጋ እንዲሁም ሦስት ጊዜ አደረገ ውኃውም ይረጋል አደነቀ። እናታቸውንም አቅርቦ ጠየቃት እርሷም ፈርታ ተንቀጠቀጠች ከእርሷም የሆነውን በባሕር መካከል ዐውሎ ነፋስ እንደተነሣባት ጡቷን በጥታ ደሟን እንደ ቀባቻቸውና በባሕር ውስጥ እንዳጠመቀቻቸው ነገረችው ስለ አደረገችውም ድፍረት በፊቱ ሰግዳ ይቅር ይላት ዘንድ ለመነችው።
አባ ጴጥሮስም ሴትዮ አትፍሪ ሃይማኖትሽ ፍጹም ነው አንቺ በባሕር ውስጥ በአጠመቅሻቸው ጊዜ በመለኮታዊት እጁ ያጠመቃቸው ባለቤቱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና አይዞሽ አላት።ማጥመቁንም በፈጸመ ጊዜ ሥጋውን ደሙን አቀበላቸው ይቺም ቅድስት ወደ አንጾኪያ ቤቷ ተመለሰች።
ባሏም በአያት ጊዜ ይህን በማድረጓ ተቆጥቶ ወደ ንጉሡ ሒዶ ከሰሳት ያደረገችውንም ነገረው። ንጉሡም ወደርሱ ያቀርቧት ዘንድ አዘዘ ስትቀርብም ወደ እስክንድርያ ለምን ሔድሽ ከክርስቲያን ወገኖች ጋራ ልታመነዝሪ ነውን አላት። እርሷም እንዲህ ብላ መለሰችለት ክርስቲያኖች አያመነዝሩም እንደናንተ የረከሰ ጣዖትን አያመልኩም ከእንግዲህ ደግሞ ከእኔ ቃልን አትሰማም የወደድከውን አድርግ ሁለተኛም በእስክንድርያ ካንቺ የሆነውን ንገሪኝ ብሎ ጠየቃት ምንም ምን አልመለሰችለትም ።
ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም እጆቿን የኋሊት አሥረው ሁለቱንም ልጆቿን በሆድዋ ላይ አድርገው ሦስቱንም በእሳት ያቃጥሉአቸው ዘንድ አዘዘ። ፊቷንም ወደ ምሥራቅ መልሳ ወደ ክብር ባለቤት ጌታችን ጸለየች ከዚያም ከልጆቿ ጋራ አቃጠሉዋት የድልና የሕይወት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቷ ለዘላለም ይማረን አሜን። https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ሚያዝያ_24
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ሃያ አራት በዚህች ቀን የቅዱስ ኤስድሮስ ባልንጀራ #ቅዱስ_ፃና በሰማዕትነት አረፈ፣ ጳጳሳት ስልሳ አምስተኛ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #አባ_ስንትዩ አረፈ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ፃና
ሚያዝያ ሃያ አራት በዚህች ቀን በመጋቢት ዐሥራ ስምንት ቀን የተጻፈ የቅዱስ ኤስድሮስ ባልንጀራ ቅዱስ ፃና በሰማዕትነት አረፈ፡፡
ይህም እንዲህ ነው ባልንጀራው ከኤስድሮስ ጋራ ከአሠቃዩት በኋላ ባልጀራው ኤስድሮስ በሰማዕትነት ሞተ። ቅዱስ ፃናም በእሥር ቤት ቀረ ከአገረ ፈርማ መኰንንም ታሠረ በእርሱም ፈንታ ሌላ መኰንን ተሾመ።
ያንን መኰንንም የክብር ባለቤት የሆነ የኢየሱስ ክርስቶስ ስም የሚጠራ ክርስቲያንን ሁሉ እንዳያስቀር ከሀዲው ንጉሥ አዘዘው። ስለ ቅዱስ ፃናም እርሱ ከጭፍሮች ውስጥ እንደሆነ ጽኑዕ ሥቃይም እንዳሠቃዩትና ከአላማውም እንዳልተመለሰ በነገሩ ጊዜ የከበረች ራሱን ይቆርጡት ዘንድ አዘዘና ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ።
የቅዱስ ፃና እናቱም ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት በሆነ ጊዜ አስቀድማ እንዳየች አሁንም ብርሃናውያን መላእክትን የቅዱስ ፃናን ነፍስ ሲያሳርጓት አይታ ለሰው ነገረች። ምዕመናንም ሥጋውን ወስደው ገንዘው ሰምኑድ በሚባል አገር ከባልንጀራው ከኤስድሮስ ሥጋ ጋር አኖሩት። በውስጥዋም እስከ ዛሬ በዓል ይደረግላቸዋል። ወደ እርሳቸው በእምነት ለሚመጣም ታላላቅ ድንቆች ተአምራቶች ይታያል።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ስንትዩ_ሊቀ_ጳጳሳት
በዚህችም ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ስልሳ አምስተኛ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ስንትዩ አረፈ፡፡ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ መንፈሳዊ ነው። በአስቄጥስም ገዳም በአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን በበጎ ሥራ በገድል ተጠምዶ አድጎ በዚያው ገዳም አበምኔት ሁኖ ተሾመ። ከዚህም በኋላም ሕዝቡና ኤጲስቆጶሳቱ መርጠውት በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት። ነገር ግን በዘመኑ ሁሉ ከእስላሞች ነገሥታት ታላቅ ችግርና ኀዘን ደረሰበት። ይኸውም በእርሱ ዘንድ ምንም ምን ያልኖረውን ሊሰጣቸው የሌለውን ብዙ ገንዘብ ይሰጣቸው ዘንድ ፈልገው ይዘውታልና። እግዚአብሔር በእጆቹ ብዙ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ ብዙዎችን ጭንቅ ከሆነ ደዌያቸው አድኖቸዋልና ከሰዎችም ላይ ሰይጣናትና አስወጥቷልና በአገረ መርዩጥ ላይ በጸሎቱ ዝናምን አዝንሞአልና። እርሱም ዝናምን ከማጣት የተነሣ ወንዞቻቸው ጉድጓዶቻቸው ሁሉ ደርቀው ከረኃብና ከውኃ ጥም የተነሣ ለሞት ተቃርበው በታላቅ ረኃብ ሦስት ዓመት ኑረዋልና።
በሰማዕት ቅዱስ ሚናስ ቤተ ክርስቲያን በዓልን ሊያከብር ወደርሳቸው በደረሰ ጊዜ የዚያች አገር ሰዎች ወደ ርሱ ተሰብስበው ውኃ በማጣት እንደ ተቸገሩ ነገሩት እርሱሙ ፈጽሞ አጽናናቸው። የቅዳሴውንም ሥርዓት ከፈጸመ በኋላ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ወዲያውኑ ታላቅ ነጐድጓዶችና ኩሬዎች ሁሉ ሞሉ የተክል ቦታዎች ሁሉ ረኩ። ረኃብ በሆነባቸው በእነዚህ ሦስት ዓመት እንደመላ ኖረ።
አራተኛውም በአስቄጥስ አረቦች በተሰበሰቡ ጊዜ በዚያ የሚኖሩትን መነኰሳት ይገድሉአቸው ዘንድ ከበቡአቸው ይህም አባት መስቀሉን ይዞ ወደእርሳቸው ወጣ መስቀሉንም በአዩ ጊዜ ወደኋላቸው ተመልሰው ሸሹ በማንም ላይ ከቶ ጉዳት አላደረሱም። ደግሞ በትምርቱ ከአገሩና ከመንጋው ውስጥ ክህደትንና ኑፋቄን አስወገደ በዚያን ጊዜ ስለእኛ መከራ የተቀበለው ትብስእት ብቻውን ነው አምላክ አይደለም የሚሉ ነበሩና።
ይህም አባት ስንትዩ በከበረ በታላቁ ጾም ወራት መልክትን ጽፎ ለአገሩ ሁሉ ላከ በውስጥዋም እንዲህ የሚል እያስተማረ "ስለእኛ መከራ የተቀበለ እግዚአብሔር ቃል በሥጋ ነው ከተዋሕዶ በፊት ሁለት የነበሩ በተዋሕዶ አንድ ባሕርይ ስለሆነ አንዲት ሰዓት ወይም የዐይን ጥቅሻ ያህል ከቶ አልተለያዩም በመከራ ጊዜ ወይም በሞት ከመለኮቱ ያልተለየ እርሱ አካላዊ ቃል በሥጋው ስለ እኛ መከራን ተቀበለ"። ይቺም መልእክት በአገሩ ሁሉ በአነበቡአት ጊዜ የክርስቲያን ወገኖች ታላቅ ደስታ ደስ አላቸው እሊያ የሳቱትም ተመልሰው ንስሓ ገቡ። ሁለኛም ደግሞ ምላሳቸውን መቆረጥ የሚገባቸው የተሳሳቱ የመለኮት ባሕርይ ሞተች የሚሉ ሰዎች ተገለጡ እሊህም የብልንያ አገር ሰዎችና ኤጲስቆጶሳቸውም ነው።
ይህም አባት ይህን የእብደትና የስንፍና ነገር በሰማ ጊዜ እጅግ አዝኖ መልእክትን በውስጡ እንዲህ ጻፈ "እግዚአብሔር ባሕርዩ አትመረመርም የማትዳሠሥ የማትታመም ናት እግዚአብሔር ቃል ከእኛ ነሥቶ ያለ መለያየትና ያለ መቀላቀል ከመለኮቱ አዋሐደው ከሰውነቱ ባህርይ በቀር ሕማምን አታስገባም" ሁለተኛም በውስጥዋ እንዲህ አለ "እኛ መከራ ከሚቀበል ከሥጋው እግዚአብሔር ቃልን አንለየውም በመከራውም በሥራው ሁሉ አንድ እንደሆነ እናምናለን እንጂ ሁለተኛም መለኮቱ በባሕርዩ የማይታመም የማይሞት እንደሆነ ከመለኮት ሳይለይ ስለእኛ መከራ ተቀብሎ ሞተ እንጂ"። የመልእክቱም ደብዳቤዎች ወደእነዚህ ሰዎች ደርሰው በአነበቡአቸው ጊዜ ከስሕተታቸው ተመልሰው በእውተኛዪቱ በቀናች ሃይኖት አመኑ። ኤጲስቆጶሳቸውም ጋራ ወደዚህ አባት ወደ ሊቀ ጳጳሳት ስንትዩ ፊት ቀርበው የቀናውን እምነት ተቀብለው አመኑ ታላቅ ስሕተታቸውንና በደላቸውንም ይተውላቸው ዘንድ ለመኑት እርሱም ስሕተታቸውን እያመኑ በኤጲስቆጶሳቱ ሁሉ በካህናቱ በሕዝቡም ፊት እንዲሰግዱ አዘዛቸው እንዳዘዛቸው አደረጉ በደላቸውንም ተወላቸው።
ይህም አባት አብያተ ክርስቲያናትን ስለማነፅ የስደተኞችንም ቦታዎች ስለማዘጋጀት ብዙ የሚአስብ ነው ከዚህ የሚተርፈውንም ለድኆችና ለምስኪኖች ይሰጣል። መልካም ጉዞንም በመጓዝ እግዚአብሔርን አገለገለው ሚያዝያ24 በሰላምም ዐረፈ። የሹመቱም ዘመን ዐሥራ አምስት ዓመት ሆነ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የቅዱሳኑ በረከት ረድኤት በሁላችን የክርስቲያን ወገኖችን ከሥጋና ከነፍስ መከራ ይጠብቀን ለዘላለሙ አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12
ያን ጊዜም የክቡር ጊዮርጊስን ራስ በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ድል አድራጊ ጊዮርጊስም እጅግ ደስ አለው እሳት ከሰማይ አውርዶ ሰባውን ነገሥት ያቃጥላቸው ዘንድ መከራውም ከክርስቲያን ወገን ጸጥ ይል ዘንድ ጌታችንን ለመነው፡፡ ወዲያው እሳት ወርዶ ከሠራዊታቸው ጋር ሰባውን ነገሥታት አቃጠላቸው፡፡
ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተገልጾ ብዙ ቃል ኪዳን ሰጠው፡፡ በምድር መታሰቢያህን ለሚያደርግ ሁሉ እኔ ኃጢአቱን ሁሉ እደመስሳለሁ በመከራም ውስጥ ሁኖ በባሕርም ሆነ በየብስ ወይም በደዌ በስምህ የሚለምነኝን እኔ ፈጥኜ ከመከራው አድነዋለሁ ይህንንም ጌታችን ተናግሮ በክብር ወደ ሰማይ ወጣ፡፡
ከዚህ በኋላ ራሱን ዘንበል አድርጎ በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያት አክሊላትን ተቀበለ፡፡ ከአገልጋዮቹም የቀሩት ሥጋውን ወስደው በልብስ ጠቀለሉት ወደ ሀገሩ ልዳም ወሰዱት፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው በውስጥዋ አኖሩት ከእርሱም ቍጥር የሌላቸው ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ሮቆ
በዚህችም ቀን ተአምራትን እስከ አሳየ ድረስ የተጋደለ ቅዱስ ሮቆ አረፈ። በአንዲት ዕለትም ለጸሎት ቁሞ ሳለ የንዳድ ትንኝ ነደፈው ቀስሉን እያሳየ በብዙ ልቅሶ ወደ ጌታችን ለመነ።
ያን ጊዜም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደመና ላይ ተገለጠለት። በአንጻሩም ቁሞ ወዳጄ ሮቆ አትፍራ ላድንህ ወደ አንተ መጥቻለሁና ።
ደግሞም የሮቆ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ከንዳድ በሽታ አድነኝ ብሎ በስምህ ለሚለምነኝ የንዳድ በሽታ በላዩ ላላመጣበት ከአንተ ጋራ ቃል ኪዳንን ላጸና መጣሁ አለው።
ይህንንም ብሎ በታላቅ ክብር ወደ ሰማያት ዐረገ። ቅዱስ ሮቆም በብዙ ገድል ተጠምዶ ኑሮ በሰላም አረፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የቅዱሳኑ በረከት ረድኤት ሁላችን የክርስቲያን ወገኖችን ከሥጋና ከነፍስ መከራ ይጠብቀን ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ሚያዝያ_23
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ሃያ ሦስት በዚህች ቀን ታላቅና ክቡር የሆነ #የሰማዕቱ_የቅዱስ_ጊዮርጊስ የምስክርነት ፍጻሜ ሆነ፣ ተአምራትን እስከ አሳየ ድረስ የተጋደለ #ቅዱስ_ሮቆ አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሊቀ_ሰማዕት
ሚያዝያ ሃያ ሦስት በዚህች ቀን ፀሐይና የአጥቢያ ኮከብ የተባለ ታላቅና ክቡር የሆነ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ የምስክርነት ፍጻሜ ሆነ። የዚህም ቅዱስ አባቱ መስፍን ነው ስሙም አንስጣስዮስ ይባላል ከቀጰዶቅያ አገር ነው የእናቱም ስም ቴዎብስታ ይባላል ከፍልስጥዔም አገር ናት ታናሽ ሆኖ ሳለ አባቱ አረፈ።
ሃያ ዓመትም በሆነው ጊዜ የአባቱን ሹመት ሊቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ዘንድ ሔደ፡፡ ንጉሡም ጣዖት አቁሞ ጣዖትን እንዲአመልኩ ሰዎችን ሁሉ ሲያስገድዳቸው አገኘው። ይህንንም አይቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ እጅግ አዘነ በእርሱ ዘንድ ያለውን ገንዘቡን ሁሉ ለድኆች ለምስኪኖች ሰጠ ባሮቹንም ነፃ አወጣቸው።
ከዚህ በኋላ በንጉሥ ፊት ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ። ንጉሡም አባበለው ብዙ ቃልኪዳንም ገባለት እርሱ ግን አልተቀበለውም። ለመስማት እንኳ የሚያስጨንቅ ሥቃይን አሠቃየው ጌታችን ግን ያጸናዋል ቍስሉንም ያድነዋል ሦስት ጊዜም እንደ ሚሞት እርሱም እንደሚአሰነሣው በአራተኛውም የምስክርነት አክሊልን እንደሚቀበል ነገረው። ቃል ኪዳንም ሰጠው ስሙ በዓለሙ ሁሉ የተገለጠ ይሆን ዘንድ በተጋድሎና መከራ በመቀበልም ጽኑዕ በሆነ ሥቃይም ሰባት ዓመት እንደሚኖር መላእክትም እንደሚአገለግሉት ነገረው።
ንጉሡም ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለመታዘዙና ባለመመለሱ እጅግ አዘነ ስለዚህም አትናስዮስ የሚባል ታላቅ ሥራየኛ አመጣ እርሱም መርዝን ቀምሞ በጽዋ መልቶ አስማት ደግሞ እንዲጠጣ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰጠው። ወዲያውኑ የሚሞት መስሎት ነበር። ቅዱሱም ያንን ጽዋ ጠጣው ምንም ጉዳት አልደረሰበትም።
ያ መሠርይም በክብር ባለቤት በጌታ ኢየሱስ አምኖ በሰማዕትነት ሞተ። ከእርሱም ጋራ ሌሎች ብዙዎች ሰዎች በሰማዕትነት ሙተው የሕይወት አክሊል ተቀበሉ ቍጥራቸውም ሠላሳ ሺህ ሰባት መቶ ነፍስ ነው።
ቅዱስ ጊዮርጊስም በዱድያኖስና በሰባ ነገሥታት ፊት በቆመ ጊዜ በዚያም የተቀመጡባቸው የዕንጨት ወንበሮች ነበሩ። ቅዱሱንም እሊህን የተቀመጥንባቸውን ወንበሮች እንዲበቅሉ እንዲአብቡና እንዲአፈሩ ታደርጋቸው ዘንድ ከአንተ እንሻለን አሉት። በዚያን ጊዜ ጸለየ እንዳሉትም አደረጋቸው ይህንንም ድንቅ ሥራ አይተው ቍጥር የሌላቸው ብዙ አሕዛብ በጌታችን አመኑ።
ከዚህም በኋላ ቅዱሱን ወስደው በጐድጓዳ ብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት። አቃጥለው አሳርረውም ሥጋውንና አጥንቱን ፈጭተው አመድ አድርገው ከረጅም ተራራ ላይ በተኑት። ጌታችንም ነፍሱን ወደ ሥጋው መልሷት ደግሞ አስነሣው። ወደ ነገሥታቱም ተመልሶ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ስም ሰበከ ቁጥር የሌላቸው አሕዛብ አይተው አደነቁ በጌታችንም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ።
ነገሥታቱም ደግመው ሙታኖችን ብታሥነሣ አምላክህ እውነተኛ አምላክ እንደሆነ እናውቃለን በእርሱም እናምናለን አሉት። ቅዱሱም ጸለየ ከጉድጓድም ውስጥ ወንዶችና ሴቶች ጎልማሶችንም አስነሣላቸው እነዚያም በክብር ባለቤት በጌታችን ስም አስተማሩ የገሀነምንም ወሬ ተናገሩ ጥምቀትንም ተቀብለው ተመልሰው አረፉ።
ከሀድያን ነገሥታት ግን ሙታንን ያስነሣህ አይደለም የረቀቁ ሰይጣናትን አሳየህ እንጂ ብለው ተከራከሩ። ከዚያም ከጭንቀታቸው ብዛት የተነሣ ከአንዲት ድኃ ሴት ዘንድ አስጠበቁት እርሷም እንጀራ ልትለምንለት ወጣች የእግዚአብሔርም መልአክ በላዩ ከበጎ ነገር ሁሉ የተመላ ማዕድን አቀረበላት። የዚያች መበለትም የቤቷ ምሰሶ ቅርንጫፍን አበቀለ ታላቅ ዛፍም ሆነ። ያቺም መበለት በተመለሰች ጊዜ የቤቷ ምሰሶ ቅርንጫፍ አብቅሎ ታላቅ ዛፍ እንደሆነ ስለ ማዕዱም ይህን ታላቅ ምልክት አይታ የክርስቲያኖች አምላክ ሰው ተመስሎ ወደእኔ መጣ አለች።
ቅዱሱም እኔ አምላክ አይደለሁም የአምላክ ባሪያ ነኝ እንጂ አላት። እርሷም እንዲህ ብላ ለመነችው የአምላክ አገልጋይ ከሆንክ ቸርነትህ እንድትደርሰኝ አለምንሃለሁ። ዕውር ደንቆሮ ዲዳ ጐባጣ የሆነ ልጅ አለኝና ታድንልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ። ስለ ጌታችን እምነትም አስተማራትና በመስቀል ምልክት አማተበው ያንጊዜም አየ። ቅዱሱም በሌላ ጊዜ እንዲሰማ እንዲናገርና እንዲሔድ እንዲአገለግለኝም እኔ እሻለሁ አላት።
በዚያን ጊዜ ንጉሡ በአገሩ ሜዳ ውስጥ ሲዘዋወር ያቺን ዛፍ አይቶ አደነቀ ስለ እርሷም ጠየቀ ቅዱስ ጊዮርጊስ በእርሷ ዘንድ የተቀመጠባት የዚያች መበለት የቤቷ ምሰሶ እንደሆነ ነገሩት። ንጉሡም ተቆጣ ቅዱሱንም ከዚያ ወስዶ አሰገረፈው በመንኰራኩርም አበራዩት ሙቶም ከከተማ ውጭ ጣሉት ጌታም ከሞት አስነሣው ወደ ነገሥታቱም ተመለሰ ንጉሡም አይቶ ደነገጠ ስለ ሕይወቱም አደነቀ።
ከዚህም በኋላ ይሸነግለው ዘንድ ጀመረ በመንግሥቱ ላይም ሁለተኛ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊስም እየዘበተበት ነገ በጥዋት ለአማልክቶችህ መሥዋዕትን አቀርባለሁ አንተም ሕዝቡ እንዲሰበሰቡ እዘዝ እኔ ስሠዋ እንዲአዩ አለው፡፡ ንጉሡም ዕውነት የሚሠዋ መስሎት ደስ አለው ወደ ቤተ መንግሥቱም እልፍኝ አስገብቶ አሳደረው፡፡
ለጸሎትም ተነሣ የዳዊትንም መዝሙር አነበበ የዱድያኖስ ሚስቱ እለስክንድርያ ንግሥት ሰምታ ቃሉ ደስ አሰኛት የሚያነበውንም ይተረጒምላት ዘንድ ለመነችው እርሱም እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ሰው እስከሆነበት ጊዜ የሆነውን ሁሉ ሊያስረዳትና ሊያስገነዝባት ጀመረ ትምህርቱም በልቡዋ ተቀርጾ በክብር ባለቤት በጌታችን አመነች፡፡
በማግሥቱም ቅዱስ ጊዮርጊስ ለአማልክት ሲሠዋ ለማየት ሰው ሁሉ እንዲሰበሰብ ዐዋጅ ነጋሪ ዞረ የቤቷን ምሰሶ ያበቀለላት ያቺ መበለት ሰምታ ዕውነት መስሏት እጅግ እያዘነች ልጅዋን ተሸክማ እያለቀሰችም ወጣች፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስም በአያት ጊዜ ፈገግ አለ ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው አላት ከዚያም ልጅዋን ጠርቶ ወደ አጵሎን ሒድ ወደእኔም ይመጣ ዘንድ በክብር ባለቤት በጌታዬ ኢየሱስ ስም እዘዘው አለው፡፡ ያን ጊዜ ያ ልጅ ድኖ ቅዱስ ጊዮርጊስ እንዳዘዘው ወደ ጣዖቱ ቦታ ሒዶ አዘዘው፡፡ በጣዖቱ ያደረ ያ ርኵስ መንፈስም ከማደሪያው ወጥቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አለበት መጥቶ እኔ ሰውን ሁሉ የማስት እንጂ አምላክ አይደለሁም ብሎ በሕዝቡ ሁሉ ፊት አመነ፡፡ ቅዱሱም ትውጠው ዘንድ ምድርን አዘዛትና ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖታቱንም ከአገልጋዮቻቸው ጋራ አጠፋቸው ንጉሡም ከወገኖቹ ጋር አፈረ፡፡
ብስጭትና ቁጣንም እንደተመላ ወደ ንግሥት ሚስቱ ዘንድ ገባ፡፡ እርሷም አምላካቸው ጽኑዕና ኃያል ነውና ክርስቲያኖችን አትጣላቸው አላልኩህምን አለችው፡፡ ይህንንም ከእርስዋ ሰምቶ በእርሷ ላይ እጅግ ተቆጣ ወደ ክብር ባለቤት ክርስቶስ እምነት የከበረ ጊዮርጊስ እንደአስገባት አወቀ፡፡
ከዚህም በኋላ ከከተማ ውጭ እንዲጐትቷትና በመጋዝም እንዲሰነጥቋት አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች፡፡ በዚያም ጊዜ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሥራ ነገሥታቱ ሁሉም ደነገጡ ኀፍረት ደግሞ እንዳይጨምርባቸው ከእርሱም እንዲአርፍ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ እንዲጽፍ ንጉሥ ዱድያኖስን መከሩት፡፡
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
