የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Відкрити в Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Показати більше2 631
Підписники
+624 години
+267 днів
+4830 день
Архів дописів
22ቱ የእግዚአብሔር ኅቡዕ ስሞች(ሃያ ሁለቱ ዓሌፋት)
==================================
1. አሌፍ ፡ ብሂል አምላክ ፈጣሬ ኩሉ ዓለም
ዓለምን ከነጓዟ ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የፈጠረ እግዚአብሔር ማለት ነው።
2. ቤት፡ ብሂል ባዕል እግዚአብሔር
እግዚአብሔር ሁሉን መስጠት የሚችል ቸር ለጋስ ባለጸጋ ማለት ነው።
3. ጋሜል፡ ብሂል ግሩም እግዚአብሔር
እግዚአብሔር ሊመረመር የማይችል ግሩም ድንቅ ማለት ነው።
4. ዳሌጥ፡ ብሂል ህልው እግዚአብሔር
እግዚአብሔር በጌትነቱ ዙፋን ለዘለዓለም ይኖራል ማለት ነው።
5. ሄ፡ ብሂል ህልው እግዚአብሔር
እግዚአብሔር በአንድነቱ በሦስትነቱ ለዘለዓለም ይኖራል ማለት ነው።
6. ዋው፡ ብሂል ዋህድ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር በመንግሥት በሥልጣን በአገዛዝ በባህርይ አንድ አምላክ የሆነ ማለት ነው።
7. ዛይ፡ ብሂል ዝኩር እግዚአብሔር
እግዚአብሔር በሥራው ሁሉ እየታሰበ ሲመሰገን የሚኖር ፈጣሪ ማለት ነው።
8. ሔት፡ ብሂል ሕያው እግዚአብሔር
እግዚአብሔር በመንግሥቱ ሽረት በባሕርዩ ኅልፈት የሌለበት ለዘለዓለም ሕያው የሆነ ማለት ነው።
9. ጤት፡ ብሂል ጠቢብ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር ጥበብን የሚገልጽ ከጥበበኞች ይልቅ ጥበበኛ የሆነ አምላክ ማለት ነው።
10. ዮድ፡ ብሂል የማነ እግዚአብሔር
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና ጽኑዕ የሆነ ማለት ነው።
11. ካፍ፡ ብሂል ከሃሊ እግዚአብሔር
ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የሌለ ሁሉን ማድረግ የሚቻለው አምላክ ማለት ነው።
12. ላሜድ፡ ብሂል ልዑል እግዚአብሔር
እግዚአብሔር ልዑለ ባሕርይ የሆነ ማለት ነው።
13. ሜም፡ ብሂል ምዑዝ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር ንጹሕ ባሕርይ የሆነ አምላክ ማለት ነው።
14. ኖን፡ ብሂል ንጉስ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር የነገሥታት ንጉሥ የገዥዎች ገዥ የሆነ አምላክ ማለት ነው።
15. ሳምኬት፡ ብሂል ሰፋኒ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር ሁሉን የሚገዛ አምላክ ማለት ነው።
16. ዔ፡ ብሂል ዐብይ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር ታላቅና ገናና የሆነ አምላክ ማለት ነው።
17. ፌ፡ ብሂል ፍትው እግዚአብሔር
እግዚአብሔር ተወዳጅ የሆነ አምላክ ማለት ነው።
18. ጻዴ፡ ብሂል ጻድቅ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር ሐሰት የሌለበት እውነተኛ አምላክ ማለት ነው።
19. ቆፍ፡ ብሂል ቅዱስ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር ለልበ ቅኖችና ለየዋሃኖች ቅርብ የሆነ አምላክ ማለት ነው።
20. ሬስ፡ ብሂል ርዑስ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር ክብሩ ከእርሱ ለእርሱ የተገኘ የሁሉ ጌታ ማለት ነው።
21. ሳን፡ ብሂል ስቡህ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር በሥራው ሁሉ የተመሠገነ ማለት ነው።
22. ታው፡ ብሂል ትጉህ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር እንቅልፍ የሌለበት ትጉህ፤ ድካም የማይሰማው ጽኑዕ የሆነ ፈጣሪ ማለት ነው።
ምንጭ :- መዝሙረ ዳዊት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
https://youtu.be/5rLqRj0ho-g?si=nclQAFTxCM8mInb7
በሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት የተዘመሩ የመስቀል መዝሙራት በሊንኩ ገብተው ያዳምጡ።
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6
በዛሬው እለት መስከረም 12 /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋዮች ወንድማችን ወርቅነህ ባህሩ እና የትዝታ ወንድሙ የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!!!
እንኳን ደስ አላችሁ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6
በዛሬው እለት መስከረም 12 /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋዮች ዲ/ን ብሩክ ይብራ እና ቤተልሔም ፀጋዬ የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!!!
እንኳን ደስ አላችሁ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
ሰላም ለምቅዋምከ ዘልዑል ማዕረጋ ፤
እምተቅዋመ አዕላፍ እንግልጋ ፤
ሚካኤል መንፈስ ዘእንበለ ሥጋ፤
ታድኅን ዘተመንደቡ ለማዕከለ ባሕር እምፁጋ፤ ወለእለ በበድው ካዕበ ትባልህ በጸጋ።
በፈጣሪ ፊት ከአዕላፍ መላእክት መቆሚያ ይልቅ ከፍታ ለአላት መቆሚያህ ሰላም እላለሁ።
ተፈጥሮህም ከነፋስ የኾነ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ በክፋት ማዕበል እየተንገላቱ የሚጨነቁና በበረኃ የሚሠቃዩትን በፍጹም ረድኤትህ ደርሰህ የምታድናቸው አንተ ነህ።
የቅዱስ ሚካኤል ጸሎቱና በረከቱ አማላጅነቱም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ይኑር። አሜን
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
ጼዴንያ ማርያም
በዚህች ቀን ቅዱስ ሉቃስ የሳላትና ሥጋን የለበሰችው ከፊቷም ወዝ የሚወጣትና ድውያንን የምታድነው የድንግል ማርያም ስዕለ አድኅኖ ወደ ጼዴንያ ከወዳጇ ከብጽዕት ማርታ ዘንድ ገብታለች:: ቅድስት ማርታ ሃብት ንብረቷን በአብርሃማዊ ተግባር (በምጽዋትና እንግዳን በመቀበል) ላይ ያዋለች ክብርት ሴት ናት::
ለእመ ብርሃን ካላት ፍቅር የተነሳ እንቅልፍ አልነበራትም ተግታ ታገለግላትም ነበር ስዕሏን እንዲያመጣላት የላከችው ኢትዮዽያዊው መነኩሴ አባ ቴዎድሮስ የስዕሏን ተአምራት ባየ ጊዜ ለራሱ ለመውሰድ ሞክሮ ነበር::
ነገር ግን ከሁሉም በተሻለ የምትወዳት ቅድስት ማርታ ነበረችና በድንቅ ተአምር በዚህች ቀን ወደ ጼዴንያ ገብታለች:: ቅድስት ማርታም ያለ ዕረፍት ስታገለግላት ኑራ ዐርፋለች::
ተቀጸል ጽጌ / አጼ መስቀል
ከ1500 ዓመት በፊት አበባን ተቀዳጅ የሚል ትርጉም ያለው የ‹‹ተቀጸል ጽጌ›› ክብረ በዓል መከበር የተጀመረው በአፄ ገብረ መስቀል ዘመን ሲሆን፣ ዝማሬውን ያዘጋጀው ደግሞ ቅዱስ ያሬድ ነበር ክረምት በሚወጣበት መስከረም 25 ቀን የአበባው በዓል ሲከበር ቅዱስ ያሬድ ንጉሠ ነገሥቱን ‹‹ተቀጸል ጽጌ ገብረ መስቀል ሐፀጌ›› - አፄ ገብረ መስቀል ክረምቱ አልፎልሃልና አበባን ተቀዳጅ፣ አበባን ተላበስ እያለ ያወድሰው የነበረው በዓላዊ ትውፊት እየተቀባበለ እስከ 15ኛው መ/ክ/ዘ ደርሶ ነበር፡፡
በአፄ ዳዊት ዘመን የጌታችን ግማደ መስቀሉ መስከረም 10 ቀን ከግብፃውያን እጅ በመቀበላቸው ግማዱም በንጉሡ ምክንያት በመምጣቱ ‹‹አፄ መስቀል›› እየተባለ መከበር ሲጀምር፣ የ25ኛው ቀን የአበባው
በዓልም በ15 ቀን ወደኋላ በማፈግፈግ ከርሱ ጋር ባንድነት እንዲከበር በመወሰኑ እስካሁን በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ በቀድሞ ግዜ እስከ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመን (1923-1967) የ1966ቱ መስከረም 10 ድረስ በዓሉ በንጉሡ ፊት በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት፣ በኋላም በኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት ይከበር ነበር፡፡
በዘመነ ደርግ ተቋርጦ የነበረው የአበባው በዓል ተቀጸል ጽጌ ከ1980ዎቹ አጋማሽ ጀምሮ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አማካይነት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዐውደ ምሕረት በመንፈሳዊ ሥነ ሥርዓትና ለምእመኑ አበባ እየታደለ መከበር ጀምሮ እንደቀጠለ ነው፡፡ ‹‹የክረምቱ ወራት አልፎ መጸዉ ብሎም በጋው ሲተካ፣ ምድር በልምላሜ ፀጋ ተውባ አረንጓዴ ልብስ ተጎናጽፋ፣ በዕፅዋት አበባ ደምቃ፣ የመንፈስ ደስታ የምታድልበት፣ ሰማይ በከዋክብት አጊጦና አሸብርቆ የሚታይበት በመሆኑ የአበባ በዓል ስም ከግብር የተስማማለት ነው፡፡
ቅዱስ እግዚአብሔር በዕለቱ ከሚታሰቡ ቅዱሳን በረከት ያድለን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
🌻ተቀጸል ጽጌ 🌻
በዐፄ ዳዊት ዘመን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ግማደ መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ የገባበትና የ “ተቀጸል ጽጌ”(አበባን ተቀዳጅ) በዓል ዛሬ መስከረም ፲ ቀን ይከበራል፡፡
+3
እናስተዋውቅዎ
""""""""""""""""""""
ጥንታዊው እና ታሪካዊው የርዕሰ አድባራት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን በ1872 ዓ.ም በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ተመሰረተ። የኪነ ሕንፃ ግንባታው አምስት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን ከ1872 እስከ 1877 ዓ.ም ተሰርቶ ሲጠናቀቅ በግብጻዊው ጳጳስ አቡነ ማቴዎስ ተባርኮ ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የተከበራችሁ የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላት ከዚህ ቀደም ለበዓለ ደመራ ክብረ በዓል ከትርኢት አቅራቢዎች ውጪ ያሉ አገልጋዮች ከደብራችን በዕለቱ ልብሰ ስብሐት በመልበስ ወደ መስቀል አደባባይ እናመራ የነበረ ሲሆን አሁን ግን ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተሰጠን አቅጣጫ መሰረት በዕለቱ የሚወጡ ዘማርያንም ቢሆኑ በአንድነት በደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ የመዝሙር ጥናት ቅዳሜና እሑድ ከ ቀኑ 10:00-12:00 ስለሚከናወን ተገኝታችሁ ካላጠናችሁ ስለተከለከለ በዕለቱ የማትሳተፉ መሆኑን አጥብቀን እናሳውቃለን።
የሰ/ት/ቤታችን አባላት ጉዳይ ክፍል
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የሐዘን መግለጫ
የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን ዳንኤል ተስፋዬ አባት ስላረፉ ስርዓተ ቀብራቸው ነገ ዛሬ መስከረም 09/2017 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ላይ በደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቤ/ክ ስለሚፈጸም የምትችሉ አባላት ቀብሩ ላይ እንድንገኝ ይሁን እንዲሁም መኖሪያ ቤታቸው በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን። የአባታችንንነፍስ ይማርልን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የኦርየንታል ኦርቶዶክስ እና የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስቲያናት የነገረ መለኮት ውይይት ከ34 ዓመታት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ በካይሮ መካሄድ ጀመረ !
መስከረም 7 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
+++
ጉባኤው “የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናል” (2ኛ ቆሮንቶስ 5፡14) በሚል መሪ ቃል በእምነት እና እና በአገልግሎት እና በማኅበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሂደዋል፤ ጉባኤው ትናንትና እና ዛሬ በግብጽ ቅዱስ ቢሾይ ገዳም “ሎጎስ” የስብሰባ ማዕከል መካሄድ የጀመረ ሲሆን በኦሪየንታል ኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስቲያናት እና በምሥራቅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መካከል ይፋዊ የነገረ መለኮት ውይይት በዚህ ስብሰባ ተካሂዷል።
ዓላማው ከ30 ዓመታት በላይ የተቋረጠውን ይፋዊ የሥነ-መለኮት ንግግር እንደገና ለመቀጠል እና እንደገና ለመገምገም መሆኑን የግብጽ ቤተ ክርስቲያን አስታውቃለች።
ጉባኤው የተከፈተው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እና በፓትርያርክ አቡነ በርተሎሜዎስ ቀዳማዊ፣ መልእክት ነው።
በስብሰባው ላይ በሁለቱ አቢያተ ክርስቲያናት ቤተሰቦች ላይ የሚነሱ ልዩ ልዩ የአስተምህሮ ጉዳዮች ወደ አንድ ወጥ አቋም ለመድረስ በማለም በዚሁ ልክ ውይይት መደረጉ ነው የተገለጸው።
የምሥራቃውያን ኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስቲያናት ልዑካንን ጨምሮ በጉባኤው የአሌክሳንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ (አስተናጋጅ ቤተ ክርስቲያን)፣ የአንጾኪያ እና የመላው ምሥራቅ ፓትርያርክ (ሶርያ )፣ የአርመን ኦርቶዶክስ፣ የኦርቶዶክስ የኢትዮጵያ የኤርትራ አቢያተ ክርስቲያናት መወከላቸውን የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ገልጻለች።
©ተ.ሚ.ማ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
አስቸኳይ የስራ ማስታወቂያ
.....................................
የስራ መደብ:- ኤዲተር
የት/ደ:- ኤዲቲንግ ፎቶሾፕ የተማረ/ች
የስራ ልምድ :- በማተሚያ ቤት የሰራ/ች
ብዛት :- 1(አንድ)
ቦታ:- ተክለሃይማኖት
ስልክ:-0931144444
ደሞዝ:- በስምምነት
ማሳሰቢያ:- የሰንበት ት/ትቤታችን አባላት የሆናችሁና የስራ ዕድል ሲመጣልን እንድናገናኝዎ የምትፈልጉ ወይም ይህ መረጃ የሚያደርሳቸውና የሚያስፈልጋቸውን አባላት የምታውቁ ከታች በተቀመጡ ስልኮች በመደወል እንዲያስመዘግቡ በትህትና እንጠይቃለን።
0966-25-87-38 ዮሐንስ ትዳሩ
0912-41-97-72 ዮናስ እርዳው
የበጎ አድራት ክፍል
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
+1
ሰንበት ት/ት ቤታችን በዛሬው እለት አስተምሮ ካስመረቃቸው ተማሪዎቹ መካከል የደብራችን ምግባረ ሰናይ ክፍል ኃላፊ የሆኑት እማሆይ ሲ/ር ገነት ይገኙበታል እና ለሌሎቻችንንም አርአያ መሆን የሚችሉ እናታችን ናቸው እማሆይ እድሜና ጤና ጸጋና በረከትን ያድሎት።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
