uk
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Відкрити в Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Показати більше
2 756
Підписники
+124 години
+97 днів
+4330 день
Архів дописів
‹‹… መስቀል ኃይልነ መስቀል ጽንዕነ መስቀል ቤዛነ መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ አይሁድ ክህዱ ንሕነሰ አመነ ወእለ አመነ በኃይለ መስቀሉ ድኅነ፤ … መስቀል ኀይላችን፣ ጽንዓችን፣ ቤዛችን፣ የነፍሳችን መ
‹‹… መስቀል ኃይልነ መስቀል ጽንዕነ መስቀል ቤዛነ መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ አይሁድ ክህዱ ንሕነሰ አመነ ወእለ አመነ በኃይለ መስቀሉ ድኅነ፤ … መስቀል ኀይላችን፣ ጽንዓችን፣ ቤዛችን፣ የነፍሳችን መዳኛ ነው፡፡ አይሁድ ይክዱታል፤ እኛ ግን እናምንበታለን፡፡ ያመነውም እኛ በመስቀሉ ኀይል እንድናለን፤ ድነናልም›› እንኳን ለበዓለ መስቀል በሰላም አደረሳችሁ

እጸ መስቀል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ከዲያብሎስ ባርነት ነጻ ሊያወጣ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ በቀራንዮ አደባባይ በመካነ ጎልጎታ በፈቃዱ ተሰቀለ። ሞተ ጥልንም በመስቀሉ ገደለ። ከፍተኛ ወንጀል የሠሩ ሰዎች ብቻ ይሰቀሉበት የነበረው መስቀል ከጌታችን ስቅለት በኋላ የድኅነት ምልክት ሆነ:: ጌታ የተሰቀለበት መስቀል ተአምር በማድረጉ የተመቀኙ  አይሁድ መስቀሉን ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት መስቀሉ የተቀበረበትን ስፍራ የቆሻሻ መጣያ አደረጉት። ንግሥት እሌኒ ልጇ ቆስጠንጢኖስ ክርስቲያን ከሆነላት ወደ ኢየሩሳሌም ሔዳ መስቀሉን ለመፈለግ እንዲሁም በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ለማሳነፅ ለእግዚአብሔር ተሳለች፡፡ ከዚህ በኋላ ልጇ ቆስጠንጢኖስ አምኖ በ337 ዓ.ም ተጠመቀ፡፡ ንግስት እሌኒም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች የጌታችንን መስቀል መፈለግ ብትጀምርም ያለበት ስፍራ የሚነግራት ሰው ልታገኝ አልቻለችም፡፡ አይሁድ የተቀበረበትን ቦታ ለማሳየት ፍላጎት ባይኖራቸውም  አንድ ኪራኮስ የሚባል አረጋዊ ሰው አስጨንቃ ስለያዘችው መስቀሉ የሚገኝበትን ስፍራ ጠቆማት ነገር ግን ለዘመናት ቆሻሻ ሲጣልበት የነበረ ስፍራ በመሆኑ ተራራ ሰርቷል በቦታው ከነበሩት ከሦስቱ ተራሮች ውስጥ መስቀሉ የሚገኝበት የትኛው እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ ንግሥት እሌኒ ከሦስቱ ተራሮች የቱ እንደሆነ ለመለየት በእግዚአብሔር ረዳትነት ደመራ አስደምራ ብዙ እጣንም በመጨመርና በማቃጠል ጸሎት ተያዘ፡፡ የእጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ በመውጣት በቀጥታ ተመልሶ መስቀሉ ወዳለበት ተራራ ላይ በማረፍ መስቀሉ ያለበትን ትክክለኛ ስፍራ አመለከታት፡፡ መስከረም አስራ ስድስት ቀን ቁፋሮው ተጀምሮ መጋቢት አስር ቀን ሦስት መስቀሎች  ተገኙ፡፡ ነገር ግን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል  የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ተቸገሩ፡: መስቀሎቹን ወስደው ሙት ላይ ቢያስቀምጡ ጌታችን  በዕለተ አርብ የተሰቀለበት መስቀል የሞተውን ሰው አስነሳው ሌሎቹ ሁለቱ መስቀሎች ግን ሙትን ማስነሳት  ባለመቻላቸው የጌታችንን መስቀል ለይቶ ማወቅ ተችሏል።  ንግስት እሌኒና ክርስቲያኖች ሁሉ ለመስቀሉ ሰገዱለት የመስቀሉ በረከት በሁላችንም ላይ ይደርብን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ለመስቀል ዘማርያን በሙሉ እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ነገ ለምናከብረው የመስቀል ደመራ በዓል ለዝማሬ አገልግሎት ስንመጣ * ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ አላስፈላጊ
ለመስቀል ዘማርያን በሙሉ እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ነገ ለምናከብረው የመስቀል ደመራ በዓል ለዝማሬ አገልግሎት ስንመጣ * ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ አላስፈላጊ ጌጣጌጦችን( ትውዝፍት ፣ምንዝር ጌጥ ) እንዳትጠቀሙ ከወዲሁ ልናሳስብ እንወዳለን።  ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን  አክብረን ማስከበር ያለብን እኛው ራሳችን በመሆኑ ስለዚህ የተከለከሉ ጌጣጌጦች          1.የከንፈር ቀለም (ሊፕ እስቲክ)     2.ቅንድብመቀንደብ                          3.የጥፍር ቀለም ና የጥፍር ተከላ እንዲሁም 4.አላስፈላጊ ሜካፕ ..... 5.ወንዶች አግባብነት የሌለው ጸጉር ቁርጥ በማስወገድ እንዲሁም ሌሎችም ተገቢ ያልሆኑ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጪ ያሉ ተግባራትን አትጠቀሙ።                     * መገኛሰዓት:- የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል አጥኚዎች ከቀኑ 6:00 ጎላ ጊቢ እንድትገኙ ይሁን።                                       መልካም የመስቀል ደመራ በዓል እንዲሆንልን እንመኛለን።

ለመስቀል ዘማርያን በሙሉ እንኳን ሐመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ነገ ለምናከብረው የመስቀል ደመራ በዓል ለዝማሬ አገልግሎት ስንመጣ * ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ አላስፈላጊ
ለመስቀል ዘማርያን በሙሉ እንኳን ሐመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ነገ ለምናከብረው የመስቀል ደመራ በዓል ለዝማሬ አገልግሎት ስንመጣ * ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ አላስፈላጊ ጌጣጌጦችን( ትውዝፍት ፣ምንዝር ጌጥ ) እንዳትጠቀሙ ከወዲሁ ልናሳስብ እንወዳለን።  ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን  አክብረን ማስከበር ያለብን እኛው ራሳችን በመሆኑ ስለዚህ የተከለከሉ ጌጣጌጦች          1.የከንፈር ቀለም (ሊፕ እስቲክ)     2.ቅንድብመቀንደብ                          3.የጥፍር ቀለም ና የጥፍር ተከላ እንዲሁም 4.አላስፈላጊ ሜካፕ ..... 5.ወንዶች አግባብነት የሌለው ጸጉር ቁርጥ በማስወገድ እንዲሁም ሌሎችም ተገቢ ያልሆኑ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጪ ያሉ ተግባራትን አትጠቀሙ።       * መገኛሰዓት:- የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል አጥኚዎች ከቀኑ 6:00 ጎላ ጊቢ እንድትገኙ ይሁን።                                       መልካም የመስቀል ደመራ በዓል እንዲሆንልን እንመኛለን።

ሰላም ለምቅዋምከ ዘልዑል ማዕረጋ ፤ እምተቅዋመ አዕላፍ እንግልጋ ፤ ሚካኤል መንፈስ ዘእንበለ ሥጋ፤ ታድኅን ዘተመንደቡ ለማዕከለ ባሕር እምፁጋ፤ ወለእለ በበድው ካዕበ ትባልህ በጸጋ። በፈጣሪ ፊት ከአ
ሰላም ለምቅዋምከ ዘልዑል ማዕረጋ ፤ እምተቅዋመ አዕላፍ እንግልጋ ፤ ሚካኤል መንፈስ ዘእንበለ ሥጋ፤ ታድኅን ዘተመንደቡ ለማዕከለ ባሕር እምፁጋ፤      ወለእለ በበድው ካዕበ ትባልህ በጸጋ። በፈጣሪ ፊት ከአዕላፍ መላእክት መቆሚያ ይልቅ ከፍታ ለአላት መቆሚያህ ሰላም እላለሁ። ተፈጥሮህም ከነፋስ የኾነ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ  በክፋት ማዕበል እየተንገላቱ የሚጨነቁና በበረኃ የሚሠቃዩትን በፍጹም ረድኤትህ ደርሰህ የምታድናቸው አንተ ነህ።    የቅዱስ ሚካኤል ጸሎቱና በረከቱ አማላጅነቱም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ይኑር። አሜን ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6 በዛሬው እለት መስከረም 11 /2018ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲ
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6 በዛሬው እለት መስከረም 11 /2018ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋዮች ወንድማችን ሐብታሙ ኤቢሳ እና  እህታችን ጽዮን ይበልጣል የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።  ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!      እንኳን ደስ አላችሁ  ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ለመስቀል ዘማርያን በሙሉ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ የበዓለ መስቀል አገልግሎት ከደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቅዳሜና እሑድ አጥኚዎች ዛሬ እሑድ መስከረም 11/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ብርሃ
ለመስቀል ዘማርያን በሙሉ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ የበዓለ መስቀል አገልግሎት ከደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቅዳሜና እሑድ አጥኚዎች ዛሬ እሑድ መስከረም 11/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ጀርባ በሚገኘው የቤተክሕነት አዳራሽ  እንድትገኙ እናሳስባለን።           ማስታወሻ:- ከጎላ ትራንስፖርት ስለተዘጋጀ ቀድመው ደብራችን ይገኙ በአቅራቢያው የምትገኙ እዛው መገኘት ትችላላችሁ።          

ለመስቀል ዘማርያን በሙሉ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ የበዓለ መስቀል አገልግሎት ከደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል አጥኚዎች ነገ እሑድ መስከረም 11/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት አካባቢ በሚገኘው የቤተክሕነት አዳራሽ  እንድትገኙ እናሳስባለን።           ማስታወሻ:- ከጎላ ትራንስፖርት ስለተዘጋጀ ቀድመው ደብራችን ይገኙ           አባላት ጉዳይ

ተቀጸል ጽጌ/አጼ- መስቀል/ 'ተቀጸል ጽጌ' ማለት 'መስቀል ሆይ! በአበባ አጊጥ' እንደ ማለት ሲሆን 'አጼ መስቀል' ደግሞ አጼ ገብረ መስቀልን አንድም አፄ ዳዊት ቀዳማዊን ይመለከታል። ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ፦ በሃገራችን ኢትዮዽያ የነገረ መስቀሉ ትምሕርት ከመጣ ጀምሮ መስቀል ይከበራል። በአደበባባይ ግን እንዲከበር ያደረጉት የቅዱስ ካሌብ ልጅ አፄ ገብረ መስቀል ናቸው። በወቅቱ ንጉሡ፣ ሠራዊቱ፣ ዻዻሱና ሕዝቡ በተገኙበት ቅዱስ ያሬድ "መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር ያድኅነነ እምጸር።" "መስቀል ከሁሉ ነገር በላይ ነው: ከጠላትም ያድነናል።" እያለ ይዘምር ነበር። የአበባ ጉንጉንም ለመስቀሉና ለንጉሡ ይቀርብ ነበር። ከ800 ዓመታት በሁዋላም አፄ ዳዊት ግማደ መስቀሉን ባስመጡ ጊዜ መስከረም ቀን ተተክሎ ታላቅ በዓልም ሆኖ ተከብሯል።