cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Zehabesha

Ethiopian News

Більше
Рекламні дописи
59 978Підписники
-3824 години
-1647 днів
-17130 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

በእስር ላይ ከሆነች 2ኛ ሳምንቷን የያዘችው አርቲስት አዲስ ዓለም ጌታነህ በምርመራ ላይ ከ2 ዓመት በፊት ጎንደር ላይ ስለነበራት ቆይታ ተጠየቀች። ከናሁሰናይ ጋር የፍቅር ግንኙነት አላት በሚል ከዱባይ እንደተመለሰች ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ታስራ የገባችው አርቲስቷ፤ በአሁኑ ሰዓት ላይ ከናሁሰናይ ጋር ግንኙነት የለኝም፤ እንደውም እኔ ቪክትም ነኝ የሚል ማብራሪያ ለፖሊስ እንደሰጠች የነገሩን የፖሊስ ምንጮች፤ ፖሊሶች ምርመራ ሲያደርጉባት የሚጠይቋት ጥያቄ ግን ከ2 ዓመት በፊት ከናሁሰናይ ጋር ጎንደር ላይ ሲተዋወቁ ምን እንደተፈጠረ፣ እንዴት እንደተዋወቁ እንደሆነ ነግረውናል። እስካሁን ክስ ያልተመሰረተባት አዲስ ዓለም የምታውቀው ነገር እንደሌለ፤ ለጥምቀት በዓላት ጎንደር እንደምትሄድ ለፖሊስ ገልጻለች።
Показати все...
👍 28😭 7🔥 6
የእናቶች ቀን ስጦታውን ገዝተዋል? እስኪ በአማዞን የቀረቡ የእናቶች ቀን ስጦታዎችን ይመልከቱ https://amzn.to/3QkT2Wn
Показати все...
👍 7
የኖክ ነዳጅ ማደያ ስራ አስኪያጅን በማስፈራራት ገንዘብ የተቀበሉ በእስራትና በገንዘብ ተቀጡ የኖክ ነዳጅ ማደያ ስራ አስኪያጅን በወንጀል ትፈለጋለህ በማለት አስፈራርተው ገንዘብ ተቀብለዋል ተብለው ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ሙስና ወንጀል የተከሰሱ አምስት ግለሰቦች እስከ 13 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ ተወሰነ። የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎት የቅጣት ውሳኔ የወሰነባቸው ተከሳሾች 1ኛ ጫላ መገርሳ፣ ለሊሳ በቀለ፣ ዳዊት ጉደታ፣ ዮሃንስ ደረጄ እና ብርቱካን ለታ ናቸው። የክልሉ ፍትህ ቢሮ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ተከሳሾቹ የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 ሀ ና ለ እንዲሁም የሙስና ወንጀልን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9 ንዑስ ቁጥር 2 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ እና በአዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29/1 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ መተላለፋቸውን ጠቅሶ በ2015 ዓ.ም ክስ መስርቶባቸው ነበር። በክሱ ዝርዝር ላይ እንደተመላከተው፤ ከ1ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ተገቢ ያልሆነ ብልጽግና ለማግኘት ወይም ለሌሎች ለማስገኘት በማሰብ በመጋቢት 19 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ላይ በሸገር ከተማ ገፈርሳ ክፍለ ከተማ አካባቢ በሚገኝ የኖክ ነዳጅ ማደያ ስራ አስኪያጅ የሆነ የግል ተበዳይን የፀጥታ አካላት ነን፣ በወንጀል ትፈለጋለህ በማለት መንገድ ላይ በማስቆም ከውጭ ወደ ውስጥ እንዳይታይ አድርገው በስቲከር ሸፍነው ወደአዘጋጁት የቤት መኪና ውስጥ በማስገባት ወደ መልካ ናኖ ክ/ከ አንፎ ወደ ተባለ አካባቢ ወስደውታል። ከዚህም በኋላ የሞተ ሰው ፎቶ ለግል ተበዳዩ በማሳየትና በመሳሪያ በማስፈራራት ግማሽ ሚሊየን ብር እንዲያመጣና እንደሚለቁት በመግለጽ ገንዘቡን ካልከፈለ ደግሞ ወደ ጦር ኃይሎች እንወስድኃለን በማለት ገንዘብ እንዲከፍል መጠየቃቸውን ተከትሎ የግል ተበዳዩ በባንክ ሂሳቡ ውስጥ 100 ሺህ እንዳለው ገልጾ መልስ መስጠቱ በክሱ ተመላክቷል። በዚህም ጊዜ 1ኛ ተከሳሽ ባለቤቱ በሆነችው በ5ኛ ተከሳሽ የባንክ ሂሳብ በሞባይል ባንኪንግ የግል ተበዳዩ 100 ሺህ ብር እንዲያዘዋውር ያደረገና ቀሪውን 400 ሺህ ብር እንዲያመጣ በማስጠንቀቅ የለቀቁት መሆኑን ዐቃቤ ሕግ በክሱ ላይ የጠቀሰ ሲሆን፤ በህገወጥ መንገድ የተገኘውን ገንዘብ ደግሞ 5ኛ ተከሳሽ ከአንደኛ ተከሳሽ ጋር በመሆን ምንጩን ለመደበቅ በማሰብ በተለያዩ መጠኖች ወጪ በማድረግ ለግል ጥቅም ያዋሉት መሆኑ በክሱ ዝርዝር ላይ ሰፍሯል። ተከሳሾቹ ክሱ ከደረሳቸው በኋላ ድርጊቱን ክደው በመከራከራቸው ዐቃቤ ሕግ የሰው ምስክሮችን፣ አስረጂና ገላጭ የሰነድ ማስረጃዎችን ለችሎቱ አቅርቧል። ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መርምሮ ተከሳሾቹ በተከሰሱበት ድንጋጌ እንዲከላከሉ ብይን ቢሰጥም ተከሳሾቹ በተገቢው መከላከል ባለመቻላቸው የጥፋተኝነት ፍርድ አስተላልፎባቸዋል። ከዚህም በኋላ ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ሕግን ቅጣት ማክበጃ አስተያየትንና የተከሳሾቹ የቅጣት ማቅለያ አስተያየት በመያዝ 1ኛ ተከሳሽን በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ወስኗል። ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾችን ደግሞ እያንዳንዳቸውን በ7 ዓመት ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጡ የወሰነው ፍርድ ቤቱ 5ኛ ተከሳሽን በሚመለከት በ1 ዓመት እስራትና በ1 ሺህ ብር ገንዘብ እንዲቀጡ ወስኗል። በታሪክ አዱኛ ((ኤፍ ቢ ሲ)
Показати все...
👍 31🤣 18🥰 2👏 1
የስዊድን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር Tobias Billström በተገኙበት ዛሬ Alexandra Völker የአማራን የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ በተመለከተ የስዊድን መንግስት ምን እየሰራ ነው ?በማለት ሞግታለች:: በስዊድን ፖርላማ በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ጭፍጨፋ እንዲቆም ተጠየቀ: በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸመ ያለው ግፍ እንዲቆም ወንጀለኞች እንዲጠየቁ እና ሰላም እንዲሰፍን ጥሪ አቅርባለች::
Показати все...
👍 125 15🏆 4😁 3
Показати все...
Ethiopia: ዘ ኢትዮጵያ የዕለቱ ዜና | The Ethiopia Daily Ethiopia News April 26, 2024

The Ethiopia News and Views Ethiopia: ዘ ኢትዮጵያ የዕለቱ ዜና | The Ethiopia Daily Ethiopia News April 26, 2024 Amanuel Habtamu Addisalem Getaneh

👍 4
💔 38😭 31👍 3🙏 3
የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ፕሮቶኮል በቤልጀም ብራስልስ ጥገኝነት መጠየቁ ተሰማ::
Показати все...
Показати все...
Ethiopia: አሁን የደረሱን መረጃዎች | ዘ ኢትዮጵያ | The Ethiopia News NOW April 26, 2024

The Ethiopia News and Views | Ethiopia: ዘ ኢትዮጵያ የዕለቱ ዜና | The Ethiopia Daily Ethiopia News April 26, 2024 Amanuel Habtamu #ethiopianews #ethiopia Semen Mountains North Mountains Ethiopia አማኑኤል ሃብታሙ Kesis Belay Mekonnen

👍 7
👍 6👎 3 2🤔 1
የእናቶች ቀን ስጦታውን ገዝተዋል? እስኪ በአማዞን የቀረቡ የእናቶች ቀን ስጦታዎችን ይመልከቱ https://amzn.to/3QkT2Wn
Показати все...
👍 6