cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

አዲስ ሪፖርተር - NEWS

🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው ! => በቻናሉ 📌 ፈጣን ፥ 📌 ትኩስ ፥ 📌 ወቅታዊ እና 📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል ! 🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል ! For promotion @Addis_reporter_bot #ADDIS ABABA, ETHIOPIA

Більше
Рекламні дописи
40 411
Підписники
-1824 години
-1417 днів
-51330 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

በቻይና አንድ የ86 ዓመት አዛውንት የ81 ዓመት አዛውንት የመጀመሪያ ፍቅራኛቸውን አገቡ ከ60 ዓመታት በፊት ፍቅረኛሞች ነበሩ ። በመጨረሻም የትዳር ጓደኞቻቸው ሲሞቱ ሰሞኑ መጋባታቸውን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። @Addis_Reporter
Показати все...
🤔 6 5👍 1
የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት ተከናወነ። ዛሬ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክሃይማኖት መሪነት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት ተከናውኗል። በስነ ሥርዓቱ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ቆሞሳት ፣ ካህናትና በርካታ ምዕመናን ተገኝተው እንደነበር ከቤተክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተገኘው መረጃ ያሳያል። @Addis_Reporter
Показати все...
ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እየሄዱ የነበሩ ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤትን ጨምሮ የ4 ሰዎች ህይወት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ መከላከል መረጃና ስታቲክስ ክፍል ኃረፊ ኢንስፔክተር ታምራት ደሳለኝ እንደገለፁት በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ማዞሪያ ቀበሌ ሌሊት 11 ሰዓት 40 ከወላይታ ሶዶ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ ፒካፕ መኪና በተቃራኒ አቅጣጫ ከሚጓዝ ባለሶስት እግር ባጃጅ ጋር ተጋጭቶ በውስጡ የነበሩ 3 የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤት በድምሩ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተናግረዋል። በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው። ከሟቾቹ መካከል ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እያመራች የነበረች እናት እንደምትገኝበት ነው ኢንስፔክተር ታምራት የገለጹት። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑንም ኢንፔክተር ታምራት ጠቁመዋል። @Addis_Reporter
Показати все...
😢 11👍 3 1
ሰበር የእስር ዜና ! በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24/2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸው ታውቋል። የሁለቱ አገልጋዮች መኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል። በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የሚገኙ ሲሆን የተያዙበት ምክንያት አልታወቀም። Via: ማህበረ ቅዱሳን @Addis_Reporter
Показати все...
👍 5🤔 4😢 3
ደንበኞች ከትንሳኤ በዓል ዋዜማ ጀምሮ ኃይል ቆጣቢ አጠቃቀምን ተግባራዊ እንዲያደርጉ አገልግሎቱ ጠየቀ በትንሳኤ በዓል ዋዜማና ዕለት የኃይል መዋዥቅና መቆራረጥ ለመቀነስ፤ ከተከሰተም አፋጣኝ ምላሽ ለመሰጠት የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያጠናቀቀ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። እንዲያም ሆኖ ሊያጋጥም የሚችለውን የኃይል መዋዠቅና መቋረጥ ለመቀነስ በውጭ ንግድ ላይ ከተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች በስተቀር ሌሎች ሁሉም የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ከዋዜማው ከቀን 7 ሰዓት ጀምሮ እስከ በዓሉ ዕለት ድረስ ከዋናው ግሪድ የሚጠቀሙትን ኤሌክትሪክ እንዲያቋርጡ አገልግሎቱ ጥሪ አቅርቧል። ደንበኞች በቤት ውስጥ የሚገለገሉባቸው የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶች ኃይል ቆጣቢና ለአደጋ የማያጋልጡ መሆናቸውን እንዲያረጋግጡ እና የኤሌክትሪክ ኃይል ጭነት በማይበዛበት ሰዓት በተለይ ከምሽቱ 4፡00 እስከ ንጋቱ 11፡00 ባሉት ጊዜያት እንዲጠቀሙ ጠይቋል። የቅድመ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ደግሞ በዓሉ ሲደርስ የሚኖረውን አላስፈላጊ ወረፋ ለማስቀረት እንዲችሉ ከወዲሁ የሚበቃቸውን ያህል የኤሌክትሪክ ኃይል አስቀድመው እንዲገዙ (ካርድ እንዲሞሉ) አገልግሎቱ መክሯል። @Addis_Reporter
Показати все...
👍 5
የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፈተና መቼ ይሰጣል ? እንደ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ፤ የ2016 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል። ፈተናው ለ15 ቀናት በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ለመስጠት እየተሠራ ነው። ከ70 በመቶ የሚዘጋጀው ፈተና በኦንላይንና በወረቀት ወይም በጥብቅ ቁጥጥር በወረቀት ይሰጣል ተብሏል። ባለፈው ዓመት የተፈጠረውን ችግር ለመቅረፍ የሪሚዲያል ፈተናውን በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች #ብቻ ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራበት ነው። ዘንድሮ 32,500 ተማሪዎች 50 በመቶ በላይ ውጤት በማምጣት በቀጥታ ዩኒቨርሲቲ ገብተው መደበኛ ትምህርት እየተከታተሉ ሲሆን ከ78 ሺህ በላይ ተማሪዎች ደግሞ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ሪሚዲያል ትምህርት እየወሰዱ እንደሚገኙ ሚኒስቴሩ ለኢፕድ ከሰጠው መረጃ ተመልክተናል። በሌላ በኩል ፤ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደቡ የሬሜዲያ ተማሪዎች ከታህሳስ ወር ጀምሮ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ቢሆንም በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የተመደቡ ተማሪዎች እስካሁን ጥሪ አልተደረገላቸውም። @Addis_Reporter
Показати все...
በቴክሳስ ዩኒቨርሲቲ ዳላስ ቢያንስ 20 የፍልስጥኤም ደጋፊዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ ቢያንስ 20 የፍልስጤም ድምፅ በማሰማት የሚቃወሙ ሰዎች በቴክሳስ ዩኒቨርስቲ በዳላስ ካምፓስ የጋዛ ህብረት ካምፕ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአካባቢው ፖሊስ ገልጿል።  ረቡዕ ጠዋት ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ድንኳኖችን በመትከል እንኳን ወደ ጋዛ ነፃነት ስፍራ በሰላም መጡ ሲሉ መልዕክት አጋርተዋል። ረቡዕ ከሰአት በኋላ ፖሊስ ካምፑን ሲያፈርስና ተቃዋሚዎችን በቁጥጥር ስር ሲያውል ታይቷል። ከሰልፈኞቹ መካከል ምን ያህሉ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች እንደሆኑ ግልጽ አይደለም። ፍልስጤምን የሚደግፉ ዋና ዋና ሰልፎች በአሜሪካ የኮሌጅ ካምፓሶች ተሰራጭተዋል፣ በኦስቲን የሚገኘው የቴክሳስ ዩኒቨርሲቲ በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች በተመሳሳይ በቁጥጥር ስር አውሏል።ፍልስጤማውያን በዩናይትድ ስቴትስ በሚገኙ የዩንቨርስቲው ካምፓሶች ፀረ-ጦርነት ሰልፎችን ላደረጉ ተቃዋሚዎች ምስጋናቸውን ለመግለጽ በጋዛ ጎዳናዎች ላይ ወጥተዋል። በማዕከላዊ ጋዛ ዲየር ኤል ባላህ በስደተኛ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ሰዎች በአሜሪካ ኮሌጆች ተቃዋሚዎችን የሚያመሰግኑ ምልክቶችን ይዘው ወጥተዋል። ሰልፎቹ ጦርነቱ እንዲቆም በዩንቨርስቲው አስተዳደሮች፣በ አሜሪካ መንግስት እና በአለም አቀፉ ማህበረሰብ ላይ ጫና እንደሚፈጥር ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል። በሌላ በኩል በዮርዳኖስ መንግስት ስር የሚተዳደረው ፔትራ የዜና ወኪል እንደዘገበው ሁለት የዮርዳኖስ የእርዳታ ልዑካን ምግብ፣ ዱቄት እና ሰብአዊ ርዳታዎችን የያዙ ምርቶችን ሲያጓጉዙ በእስራኤል ሰፋሪዎች ጥቃት እንደደረሰባቸው ዘግቧል። @Addis_Reporter
Показати все...
👍 2
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የጸሎተ ሐሙስ ሥነ ስርዓት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል። @Addis_Reporter
Показати все...
በትግራይ ክልል የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች የ17 ወር ውዝፍ ደሞዝ እስካሁን አልተከፈላቸውም ተባለ፡፡ በክልሉ የሚገኙ ሁሉም የጤና ባለሙያዎች የ17 ወር ደሞዝ ሳይከፈላቸው በመቆየቱ ከቤት ኪራይ ጀምሮ በተለያዮ ወጪዎች በእዳ ተይዘው እንደሚገኙ የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ አስታውቋል፡፡ የክልሉ ጤና ቢሮ የፈውስና ተሃድሶ ዋና የስራ ሂደት ተተኪ ዶክተር ስምኦን ገብረጻዲቅ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት ባለሙያዎቹ ለመኖር ሲሉ ለሚያስፈልጋቸው ወጪ በብድር ሲጠቀሙ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡ ይህም የጤና ባለሙያዎቹ አገልግሎት ለመስጠት ችግር እንደሆነባቸው ጠቅሰዋል፡፡ ሌላው ከጣቢያችን ጋር ቆይታ የነበራቸው የአይደር አጠቃላይ ሪፈራል ሆስፒታል ዳይሬክተር ዶ/ር አብርሃ ገ/እግዚአብሔር እንዳሉት ውዝፍ የ22 ወር የትርፍ ሰአት ክፍያም እስካሁን እንዳልተከፋላቸው አንስተዋል፡፡ ችግሩን የክልሉም ሆነ የፌደራሉ መንግስት ቢያቁም እስካሁን ምላሽ አልተሰጠንም ብለዋል፡፡ @Addis_Reporter
Показати все...
👍 3
በገበታ ለሀገር የተገነቡ ሎጆችን የማስተዳደር ኃላፊነቱ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ተሠጠ። በገበታ ለሀገር የተገነቡ ሎጆችን ስራ የማስኬድ ተግባርን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በስካይ ላይት ሆቴል ተቋሙ በኩል እንዲወጣ ዛሬ የስምምነት ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል። ስምምነቱ በቅርቡ የተመረቁትን ሃላላ ኬላ ሎጅ፣ ጨበራ ጩርጩራ የዝሆን ዳና ሎጅ እና ወንጪ ኢኮ ሎጅ እና በመጠናቀቅ ላይ ያለውን የጎርጎራ ፕሮጀክትንም ያካትታል። "ቀጣይ የስራ ማስኬድ እና ማስተዳደር ተግባሩ ለብሔራዊ ሰንደቅ ተሸካሚው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሃላፊነት መሰጠቱም የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ ከማስቻሉም ባለፈ ለአለምአቀፍ የቱሪዝም መዳረሻነት ትውውቅ ከፍ ያለ ዕድል ይፈጥራል።" ሲል የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት አስታውቋል። @Addis_Reporter
Показати все...