1 474
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-2130 днів
Архів дописів
በመዲናዋ ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ ::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመዲናዋ ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል።
በጉባኤው ላይ የምክር ቤቱ አባላት በተመረጡበት አካባቢ ከመራጭ ህዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት የተነሱ የህዝብ ጥያቄዎችን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ አቅርበዋል።
ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል የመዲናዋን የጤና መሰረተ ልማት ሽፋን እና አገልግሎትን የተመለከተው ይገኝበታል።
በመዲናዋ የጤና መሰረተ ልማት ተዳራሽነት ለማስፋት ከተማ አስተዳደሩ እያደረገ በሚገኘው እንቅስቃሴ ሆስፒታሎችን ከማደስ እና ከማሻሻል ባለፈ ሁለት አዳዲስ ሆስፒታሎች እየተገነቡ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የጤና መድህን ፣ የመድሀኒት አቅርቦት እና የባለሙያዎችን ቁጥር ማሳደግ ላይ ከተማ አስተዳደሩ የሰራቸው ስራዎች በምክር ቤት አባላቱ አድናቆት ተችሯቸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የምክር ቤት አባላቱ ከማህበረሰቡ ጋር ባደረጉት ውይይት የጤና ጣቢያ እጥረት ያለባቸው አካባቢዎችን ችግር ለመቅረፍ ምን እንደታቀደ ተጠይቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በሰጡት ምላሽ በሁሉም ወረዳዎች ጤና ጣቢያ ከመገንባት ባለፈ የጥራት ደረጃቸውን ማሻሻል ላይ ትኩረት መደረጉን አንስተዋል።
ለአብነትም በ2017 በጀት አመት 9 ጤና ጣቢያዎች በመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ጥራት መመዘኛ ተሰርተው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን ተናግረዋል።
በተጨማሪም 13 ሆስፒታሎች የታደሱ ሲሆን የዘውዲቱ እና የሚኒሊክ ሆስፒታልን ጨምሮ 4 ሆስፒታሎች ላይ ማስፋፍያ እና እድሳት እየተከናወነ እንደሚገኝ ከንቲባዋ ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ በአለም ጤና ድርጅት መመዘኛ መሰረት የጤና ተደራሸነትን መልሳለች ያሉት ከንቲባ አዳነች፤ በቀጣይ የጥራት ደረጃን ማሻሻል እና መዲናዋን የሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ትኩረት እንደሚሰጥ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
3ተኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ለምክር ቤቱ አባላት በሰጡት ማብራሪያ እና ምላሽ እንደገለፁት ምክር ቤቱ በመደበኛነት እያደረገ ያለዉ ቁጥጥር እና ድጋፍ በበከተማችን ለተመዘገቡ ተጨባጭ ዉጤቶች ማሳያ ነዉ ብለዋል፡፡
የምክር ቤቱ የህዝብ ተወካዮች አባላት ከወከላቸዉ ህዝብ ጋር በሚያደርጉት ተከታታይ ዉይይቶች የሚመጡ አስተያየቶችና ጥያቄዎችን አስፈፃሚዉ አካላት በግብዓትነት ወስዶ በፍጥነት እንዲያርም በመቻሉ በህዝቡና በመንግስት መካከል ጠንካራ ግንኙነት እንዲፈጠር ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሃገራዊና ከተማ አቀፍ የተለያዩ ሃይማኖታዊና ህዝባዊ በዓላት ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ የድሉ ባለቤት መሆኑን እና በሰላም ወጥቶ በሰላም በግባት መቻሉ የለዉጣችን ማሳያ የሆነ ሌለኛዉ የከተማዋን ገፅታ የቀየረ እና የፖለቲካ ስብራትን መጠገን የቻለ ድል መሆኑንም ገልፀዋል፡፤
ለዚህም ሶስት አካላት በዋናነት መመስገን የሚገባቸዉና የማይተካ ሚና አላቸዉ ያሉት አቶ ሞገስ ባልቻ የከተማዋ ነዋሪ ፤የፀጥታ መዋቅሩ እና የፖለቲካ አመራሩ ናቸዉ ብለዋል፡፡
የእነዚህን ድምር ዉጤት ስናይ የከተማችንን ገፅታ በመቀየር የከተማችን ተፈላጊነት እንዲጨምር በማድረግ እና ከተማችን ዓለም አቀፋዊ እዉቅና በማግኘት የትኩረት ማእከል እንድትሆን ማስቻሉ ነዉ ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ሁለተናዊ የድል ሚስጥሩ የገባነዉን ቃል ወደ ተግባር በመቀየር መስራት የመቻላችን ዉጤት ስለሆነ ይህን አጠናክሮ ማስቀጠልና ትልቁ ህልማችን ላይ መድረስ ይገባል በማለት ለምክር ቤት አባላትና ለከተማዋ ነዋሪ ልባዊ ምስጋናቸዉን አቅርበዋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በ3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባዔ አቶ ሃፍታይ ገብረእግዚኣብሔር አለማየሁ የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አድርጎ በሙሉ ድምፅ አስፅድቋል:
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ የኑሮ ውድነት ጫና ለማቃለል የሚደረገውን ብርቱ ጥረት በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያ :-
👉በበዓላት ወቅት የሚፈጠሩ የዋጋ ውድነቶችን ለመከላከል አቅደን ሰርተናል።
👉በታላላቅ የገበያ ማዕከላት የምርት እጥረት እንዳይኖር ተሰርቷል።
👉በክቡር ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ አቅጣጫ መሰረት ምርቶች ከሁለም ክፍሎች እንዲገቡ ከማህበራት በጋራ እየተሰራ ነው።
👉የንግድ ኮርፖሬሽንን የማጠናከር ስራ ተሰርቷል። የእሁዱ ገበያ እና የምገባ ማዕከላትን ማጠናከር ስራ ተከናውኗል። 500 ሺህ ለሚሆኑ ነዋሪዎችም የማዕድ ማጋራት ስራ ባለሀብቶችን በማሳተፍ ተከናውኗል። የዳቦ ዋጋንም በመደጎም ለህዝባችን ማሻሻል ተችሏል።
👉የእሁድ ገበያን ለማጠናከርም ብርቱ ስራዎች ተሰርተዋል ፤ ክፍተቶች እንዲታረሙ ይሰራል።
👉የጤና መድህን ፣ ትራንስፖርት ወዘተ 14 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት ተይዞ እየተሰራ ሲሆን በዋንኛነት ግን የህዝባችንን ህይወት በዘላቂነት ለማሻሻል እየተሰራ ነው፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በከተማዋ የተከናወኑ ሁነቶች እና አበይት የአደባባይ በዓላት ስኬት ከህዝቡ ጋር በጋራ በመሰራቱ የተገኘ ውጤት መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ
3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል ፡፡
በጉባኤው የተለያዩ የምክር ቤት አባላት ምላሽና ማብራሪያ ያስፈልጋቸዋል ያሉትን ጥያቄና አስተያየት አቅርበዋል ፡፡
የምክር ቤት አባላት ያቀረቧቸውን ጥያቄ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ ፡፡
አዲስ አበባ ላይ በተሰሩና እየተሰሩ ባሉ የኮሪደር ልማት ከተማዋ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤዎችን የማዘጋጀት ዓቅሟ እያደገ መጥቷል፤ በእነዚህ ጉባኤዎችና በመስከረም ወር የተከናወኑ ዓበይት የአደባባይ በዓላት በከተማዋ የተከናወኑበት ወር ሲሆን እነዚህ ሁነቶች በድምቀት ተከብረው አልፈዋል ለዚህ ሰኬት የተሰሩ ስራዎች ምንድናቸው ለሚለው የምክር ቤት አባላት ጥያቄ ከንቲባዋ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ለበዓላቱና ለሁነቶቹ ስኬት ከህዝቡና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ ግልፅነት በመፍጠር ወደ ስራ መገባቱን ነው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የገለፁት፡፡
በተለይ በተከናወኑ ጉባኤዎች፣ ሆቴሎች የአገልግሎት ጥራትን በማሳደግ እና ክፍያን ተመጣጣኝ በማድረግ ላደረጉት ትብብር ምስጋና ይገባል ሲሉ ከንቲባዋ ገልፀዋል፡፡
ህዝቡ አጠቃላይ እንግዶቹን በኢትዮጵያዊ አንግዳ ተቀባይነት ያደረገው ተሳትፎ የሚደነቅ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ በከተማዋ የተከናወኑ ሁነትና የአደባባይ በዓላት አብሮነትን እና አንድነትን በተግባር ያሳዩ ናቸው ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ህዝቡ መሰረተ ልማቶች የኔ ናቸው ብሎ በመንቀሳቀሱ በከተዋማ በተከበሩ በርካታ ዓበይት በዓላት እና ሁነቶች አንድም የተበላሸ የኮሪደር ልማት አለመኖሩን የገለፁት ከንቲባዋ ይህም በሌሎቹ ስራዎች ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
3ተኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛመደበኛ ጉባዔ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡
በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር በሰጡት ማብራሪያ እና ምላሽ እንደገለፁት የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የተገልጋዩን እርካታ ለማረጋገጥ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በከተማችን በቅርቡ ተመርቀዉ ወደስራ የገቡት አዲስ የመሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ለዚህ ማሳያ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በዚህ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሰፊ አገልግሎት እና ሰፊ ተገልጋይ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸዉ ተቋማት በመለየት አደረጃጀትን እና አሰራርን በመዘርጋት እንዲሁም ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ወደ ትግበራ መግባት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
በዋና መስሪያ ቤት በአራዳ ክፍለ ከተማ 13 የሚሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት 107 አገልግሎቶችን በመያዝ የተለዩ የፌደራል ተቋማትን በማካተት እየተሰራ አንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይም በቦሌ ክፍለ ከተማ በአዲስ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 12 የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት 96 አገልግሎቶችን እንዲሁም የተለዩ የፌደራል ተቋማትን በማካተት በጥቅሉ 114 አገልግሎቶች እንዲገቡ ተደርጓል፤
በአመለካከት ፣በእዉቀት እና በክህሎት የበቁ ነባርና አዳዲስ ተመረቂ ባለሙያዎችን በማሰልጠንና በመመደብ ፤የቅሬታ አፈታት ስርዓትን በማዘመን ፤ከተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት ይፈጠራሉ ተብለዉ የሚገመቱ ችግሮችን ከወዲሁ ለማረም የተቻለበት ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል፡፡
በዚህም ከየትኛዉም በኩል የሚመጡ የዜጎች ምልልስ በማስቀረት፤ወጪና ጊዜን በመቆጠብ የተገልጋይን እርካታ ከፍ ማድረግ የተቻለበት ሁኔታ መፈጠሩን ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር ተናግረዋል፡፡
ይህም ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በሌሎች ክፍለ ከተሞች ለማስፋፋት እቅድ ተይዞ በልዩ ትኩረት በቅንጅት እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡
በሌላ በኩልም አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ በተመለከተ ለተነሳላቸዉ ጥያቁ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸዉና ክፍያዉ በቅርቡ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንደሚሆን አመላክተዋል ::
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ባለፉት 3 ወራት ከ96 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ አቶ ጥራቱ በየነ
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ተመራጭ አባላት በኩል ከመራጩ ህዝብ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት 3 ወራት ከ96 ሺህ 200 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል ብለዋል፡፡
የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል 10 በመቶ ለአዳዲስ ምሩቃን እንዲሁም 56 በመቶ ለሴቶች ስራ እድል እንደተፈጠረላቸው አቶ ጥራቱ በየነ ተናግረዋል፡፡
ለኢንተርፕራይዞች በመንግስት የልማት ስራዎችና ለኢንዱስትሪዎች የጥሬ እቃ እንዲያቀርቡ በማድረግ የ2 ቢሊዮን የገቢያ ትስስር እንደተፈጠረላቸውም ገልጸዋል፡፡
በተመሳሳይ 996 የመስሪያ ሸዶችን ለአዳዲስ ስራ ፈላጊዎች ማስተላለፍ መቻሉንም እና ሌሎችን በፍጥነት ለማስተላፍ በአመቱ መጨረሻ ለ350 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አቶ ጥራቱ በየነ አስረድተዋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት የተነሱ ጥያቄዎች
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል፡፡
በጉባኤው የምክር ቤት አባላቱ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ባደረጉት የመራጭ ተመራጭ የገፅ ለገፅ ውይይት ምላሽ ያስፈልጋቸዋል ተብለው የተነሱ የህዝብ ጥያቄዎችን ለከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አቅርበዋል፡፡
የተነሱት ጥያቄዎች ፡-
👉 በበዓል ሰሞን እና ምሽትን ተገን በማድረግ የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪ ነዋሪዎችን ያማረሩ በመሆናቸው ለዚህም በቀጣይ ምን ታስቧል?
👉 ንፁህ የመጠጥ ውሃ ለነዋሪዎች ለማቅረብ ከተማ አስተዳደሩ የያዛቸው እቅዶች ምንድን ናቸው?
👉 በአንድ አንድ የእሁድ ገበያ መደብሮች ከተቀመጠው ዋጋ በላይ ማስከፈል፣ ጥራታቸው ዝቅ ላሉ ምርቶች እኩል ዋጋ መጠየቅ እንደሚስተዋል እና ይህን ችግር ለመቅረፍ በቀጣይ ምን ታስቧል?
👉 በመዲናዋ የኮሪደር ልማት ያልደረሰባቸው አካባቢዎች የኮሪደር ልማትን ለማዳረስ ከተማ አስተዳደሩ ምን አቅዷል?
👉 የጤና ጣብያ እጥረት ያለባቸው አካባቢዎችን ችግር ለመቅረፍ ምን እንደታቀደ ቢገለፅ?
👉 መሰረቱ የማይናወጥ አካታች የወል ትርክት ለመገንባት ብሎም ተራማጅ አስተሳሰብ ማስረጽ፤ የእንችላለን ስነ-ልቦና ብሎም ልመናና ኋላ ቀር አስተሳሰብን በመስበር በኪነ- ጥበብ እያዋዙ ጠንካራ ኢንዱስትሪ ለመገንባትና ዘርፉን ለመደገፍ ከተማ አስተዳደሩ ምን አስቧል?
👉 የኑሮ ሁኔታን በተመለከተ እየተሰራ ያለው ስራ ጎን ለጎን የኑሮ ጫናን ለመቀነስ፣ የነዋሪዎችን እርካታ ለማረጋገጥ የት፣ ምን ተሰርቷል?
👉 በመስከረም ወር የተካሄዱት ታላላቅ በዓላት በስኬት የመጠናቀቃቸውን ያህል በቀጣይም መሰል በዓላት በስኬት እንዲጠናቀቁ ምን ታስቧል? ይሄንንስ ድል እንዴት አገኘነው?
👉 የኮሪደር ልማቱን ህብረተሰቡ በእኔነት እንዲጠብቀው፤ ከተማውን ከተሜ ሆኖ እዲጠብቃት የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል ወይ?
👉 ህብረተሰብ ከተማዋን ከተሜ ሆኖ እዲጠብቃት የሕግ ማዕቀፍ አለ? ማዕቀፍ አያስፈልግም ወይ?
👉 ወጣቶች ኮደርስ ስልጠና ወስደው ወደ ስራ አልገቡም፤ ምን ታስቧል?
👉 የፌዴራል መንግስት የሰራተኞች ደሞዝ እንዲስተካከል ወስኗል ከተማ አስተዳደሩ ይህንን ተፈፃሚ ለማድረግ ምን ዝግጅት አድርጓል?
የሚሉ ጥያቄዎች በምክር ቤቱ አባላት የተነሱ ሲሆን ለጥያቆዎቹም በከንቲባ አዳነች አቤቤ ምላሽ ይሰጥባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤያችንን ማካሄድ ጀምረናል ።
በመራጭ ተመራጭ መድረክ ላይ ከመረጠን ህዝብ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ የሚሰጥ ይሆናል።
Mana maree 3ffaa magaalaa Finfinnee bara hojii 5ffaa yaa'ii idilee 1ffaa gaggeessuu eegalleerea.
Waltajjii filataa fi filatamaa irratti gaafiilee uummata nu filate irraa ka'aniif deebii fi ibsi kan kennamu ta'a.
Waaqni Itoophiyaa Uummata Ishee Haa Eebbisu
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዛሬ 18ኛውን የሠንደቅ ዓላማ ቀንን በአድዋ ድል መታሰቢያ በድምቀት አክብረናል!
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
3ተኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባዔ እየካሄደ ይገኛል ::… See more
