1 474
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-2130 днів
Архів дописів
የመንገድ ዳር መብራቶች ከመብራት ባሻገር:-
"የከተማዋን ውበት የገለጠ፣
የስማርት መሠረተ ልማት ግንባታው አካል ናቸው።
የከተማችን ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ናቸው
ወደፊት ኢንተለጀንት ትራንስፖርት ሲስተም መዘርጋት ሲያስፈልግ ያንን የሚደግፍ ኮምፖኔንት የያዙ ናቸው።
ትራፊክ ፍሰትን፣ጨምሮ አጠቃላይ የከማችን አንቅስቃሴን የተመለከቱ ዳታና መረጃዎችን ማግኘት የሚቻልበትን መሠረተ ልማት ያሟሉ ናቸው...."
በም/ ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager See less
እንኳን ደስ አለን !!
ሩጫ በኢትዮጵያ ትልቅ ታሪክና ቦታ አለው። ላለፉት 65 ዓመታት ኢትዮጵያ በርካታ የረጅም ርቀት ሯጮችን ለዓለም አበርክታለች። አበበ ቢቂላ በ1952 ዓ.ም በጣሊያን መዲና ሮም በተካሄደው 17ኛው የኦሊምፒክ ማራቶን ውድድር ላይ በባዶ እግሩ በመሮጥ እና የወርቅ ሜዳሊያን በማግኘት ታሪካዊ ድል ማስመዝገቡን በመከተል በተለያዩ ወቅቶች የተለያዩ ጀግና አትሌቶች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓለማ በዓለም መድረክ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ አድርገዋል።
የአትሌት አበበ ቢቂላ ድል እና ላለፉት 25 ዓመታት የመዲናችን ብሎም የኢትዮጵያ መገለጫና ተናፋቂ የአደባባይ ስፖርታዊ ክንውን የሆነው “ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ” የዓለም አትሌቲክስ ቅርስነት እውቅናን ተቀብለዋል።
ይህ እውቅና በስፖርቱ ዘርፍ የሀገራችንን ብሎም የከተማችንን ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ ፈጣሪነት የሚያጎላ ነው።
ጀግናው አትሌት አበበ ቢቂላን፣ የታላቁ ሩጫ ውድድር መስራች የሆነውን ጀግናው አትሌታችን ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴን እና ይህን ውድድር ባለፉት ዓመታት ባማረ ሁኔታ ሲያካሂዱ የቆዩትን ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ማመስገን እወዳለሁ።
በቀጣይም ውድድሩን ከዚህም በበለጠ ለማሳደግ እና ብዙ የውጭ ሀገር ተሳታፊዎችን ወደ ከተማችን እንዲያመጣ ለማድረግ የበለጠ ተባብረን የምንሰራ ይሆናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ሕዳር ሲፀዳ
ንፁሕ ከተማ ከእርስዎ ይጀምራል
Addis ababa Clen city
Addis Ababa City manager office
የአዲስ አበባ ከተማ የፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ Addis Ababa Cleansing Management Agency
ለተጨማሪ የመረጃ አማራ
ለመረጃ ሰብሳቢ ባለሙያዎችና አስተባባሪዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ።
የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የጥናትና ልማት ትግበራ ዘርፍ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን በውጤታማነት ለመምራትና ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግና የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን የሚረዱ በ2018 በጀት አመት በዉስጥ አቅምና በዉጭ አቅም የሚጠኑ ጥናቶች በተመለከተ ለመረጃ ሰብሳበቢ ባለሙያዎችና አስተባባሪዎች በዛሬዉ እለት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጥቷል።
በዚሁ የስልጠና መድረክ በ2018 በጀት አመት በዉስጥና አቅም እንዲሁም በዉጭ አቅም የሚጠኑ ጥናቶችን የያዘ በተለይም ከመረጃ አሰባሰብ፣ከመረጃ ትንተና አንፃር እንዲሁም የጥናቶቹ አስፈላጊነት የስልጠና ሰነድ ቀርቦ የጋራ ዉይይት ተደርጎበታል።
በስልጠና መድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ የጥናትና ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አማረ ሙላዉ እንደገለፁት በጽ/ቤቱ በ2018 በጀት አመት በዉስጥ አቅምና በዉጭ አቅም የሚጠኑ ጥናቶች አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉ ሲሆን ጥናቶቹ በተለይም የተቋሞቻችን የአገልግሎት አሰጣጥን ፈጣን፣ ቀልጣፋና ከተማችን የደረሰችበት እድገት የሚመጥን ከማድረግ አንፃር ሁሉም መረጃ ሰብሳቢ የመረጃ ጥራት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባው ገልጸዋል።
አቶ አማረ አክለዉም የሚሰጡ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን የተገልጋዩን የእርካታ መጠን ከፍ ለማድረግ ጥናቶችን በምርምር ላይ እና የነበሩ ችግሮች እንዲሁም የአሰራር ክፍቶች ላይ ተመስርቶ ዉጤታማ አሰራሮችን ለመዘርጋትና መፍትሄም አመላካች ጥናቶች ለማካሄድ በቀጣይ የሚከናወኑ የመረጃ የመሰብሰብ ስራ ላይ ሁሉም መረጃ የሚሰበስበው ባለሙያ በትኩረትና ጥራት ያለዉ መረጃ በመሰብሰብ ጥናቶቹ ዉጤት ያላቸዉ እንዲሆኑ ሀላፊነት በተሞላበት መልኩ መረጃዎችን መሰብሰብ ያስፈልጋል ብለዋል።
አዲስ አበባ የተተከሉ ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራቶች ብርሃን ከመስጠት ባሻገር በመረጃ ላይ የተመሰረተ የከተማ አስተዳደር ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችሉ ይነገራል፡፡
ለመሆኑ እነዚህ የመንገድ ዳር መብራቶች ከብርሃን ባሻገር ያላቸው ፋይዳ ምንድነው?
በአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ ቤት የዘንድሮውን የ20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አስመልክቶ በተዘጋጀ የመወያያ ሰነድ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡
በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዛሬው እለት የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች 20ኛውን የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከባበር አስመልክቶ በተካሄደ ውይይት ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት በአገራችን ተግባራዊ የሆነው ፌዴራላዊ ስርአት ብዝሃነትን ያካተተ ህብረ ብሔራዊነትን ያጎለበተና የህዝቦችን የእርስ በእርስ ትብብርና ትስስር ያጠናከረ ነው ብለዋል።
ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አክለው እንደገለፁት የፌዴራል ስርአታችን መጠናከርና የዴሞክራሲያዊ ስርአቱ እየጎለበተ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞም የአገራችን ህዝቦችና የከተማችን ነዋሪዎች በአብሮነት፣ በመከባበር፣ በመተጋገዝና በመደጋገፍ ባህልና እሴት በማዳበር በርካታ የእድገትና የፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ያረጋገጡ ሰፋፊ ኘሮጀክቶችን ከመንግስት ጎን በመሆን ጀምረው ማጠናቀቅ ተችሏል ሲሉም ተናግረዋል።
አያይዘውም የተገኙ አኩሪ የልማት ዉጤቶችን በማስቀጠል እንዲሁም የተጀመረውን የእድገትና የልማት ጉዞ በህብረት በማስቀጠል በተለይም ዴሞክራሲን በማስቀደም የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመመካከርና በመነጋገር በመፍታት በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
በመድረኩ የፌደራል የዲሞክራሲ ስርዓት ምንነት፣የዲሞክራሲ ፅንሰ ሀሳብ፣የዲሞክራሲ ገፅታዎች፣የፊደራል ስርዓት ምንነት፣የፊደራሊዝም ምንነተ፣የዴሞክራሲ ምንነት እነዚህ እና ሌሎች ሀሳቦች የያዘ ሰነድ ቀርቦ ዉይይት ተካሂዶበታል።
በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ በሚል ርዕስ የሚሰጠው ስልጠና እንደ አዲስ አበባ በጋራ ኦሬንቴሽን ተጀምሯል።
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ በኦሬንቴሽን ፕሮግራሙ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በየወቅቱ የሚሰጡ ስልጠናዎች በፓርቲያችን እሳቤዎች ፣ በመንግስት ፖሊሲዎች እና አቅጣጫዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ ከመፍጠር ባሻገር የወንድማማችነት እና የእህትማማችነት እሴቶች እንዲጎለብቱ ማስቻላቸውን ጠቅሰዋል።
ከነገ ጀምሮ ለስምንት ቀናት በሚሰጠው ስልጠና የመደመር መንግስትን እይታ ከዘርፎች እመርታ ጋር ተሰናስኖ እንደሚቀርብ ያብራሩት አቶ ሞገስ አገልጋይ እና ሁለገብ አመራር ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት አጋዥ እንደሚሆን ገልፀዋል።
ስልጠናው የአመራሩን የአስተሳሰብ አንድነት እንደሚገነባ የጠቀሱት አቶ ሞገስ የሚኖሩ የቡድን ውይይቶችም በፌዴራል ተቋማት እና በከተማችን አመራሮች ዘንድ ቅርርብን እንደሚያጠናክሩ አስገንዝበዋል።
ሀገራዊ ፣ ቀጠናዊ ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ተተንትነው የሚቀርቡበት ነገ የሚጀምረው ስልጠና ግቡን እንዲመታ በዲሲፕሊን በመከታተል ፣ እርስ በእርስ በመማማር ተቀራራቢ አቅም ይዞ መውጣት እንደሚገባም አቶ ሞገስ አሳስበዋል።
"በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ " በሚል ርዕሰ እንደ ሀገር በሁለተኛ ዙር በሚሰጠው ስልጠና በአዲስ አበባ ከ 2ሺህ በላይ ከፌዴራል እስከ ወረዳ የሚገኙ አመራሮች የሚሳተፉበት ሲሆን ፤ በስልጠናው ማጠቃለያም ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን እንደሚጎበኙ ይጠበቃል።
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት
#aa_prosperity
ዛሬ ክቡር የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሴሪ አንዋር ኢብራሂም የመላው ጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነውን የዓድዋ ድል መታሰቢያ ጎብኝተዋል።
ክቡር የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሴሪ አንዋር ኢብራሂም በምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንዲሁም በውቧ መዲናችን አዲስ አበባ የሚያደርጉት ቆይታ ፍሬያማ እንዲሆን በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም እመኛለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ
A true honor to welcome H.E. Prime Minister of Malaysia, Dato' Seri Anwar Ibrahim at Adwa Victory Memorial today! 🇪🇹🇲🇾
H.E. PM Anwar visited the Adwa Victory Memorial, a beacon of pride for all Black people.
We thank him for his time at the Adwa Museum and wish him a fruitful stay in the land of origins, Ethiopia.
Har'a kabajamoo Muummeen Ministiira Maaleezhiyaa Daatoo Seerii Aniwaar Ibraahim boonicha guutuu uummata gurraacha kan ta'e Yaadannoo Injifannoo Adwaa daaw'ataniiru.
Kabajamoo Muummeen Ministiira Maaleezhiyaa Daatoo Seerii Aniwaar Ibraahim dursituu dachee Itoophiyaa akkasuumas madiinaa teenyaa miidhagduu Finfinneetti turtiin taasisan milkaawaa akka ta'u maqaa koo fi maqaa bulchiinsa magaalaan hawwa.
Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu
ሰሞኑን በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ክቡር ዶ/ር አቢይ አህመድ፣ በክብርት ከንቲባችን አዳነች አቤቤና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት በአዲስ መልክ ይፋ የተደረገው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ኢትዮጵያ በዲጂታል መስክ… See more
