uk
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Відкрити в Telegram

Показати більше
1 474
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-2130 днів
Архів дописів
በትብብር መንፈስ በብዙ ትጋት እና ልፋት አዲስ የታሪክ ገፅ በብልፅግና ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ እንደ ዳግማዊ ዓድዋ ለመግለጥ እንትጋ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እምርታ""በሚል መሪ ሃሳብ እየተሰጠ ያለው ስልጠና ወቅቱን የሚመጥን፣ ዘመኑን የዋጀ በፓርቲያችን ብልፅግና የያዝነውን ራዕይ ለማሳካት በተግባር ተደማሪ አቅም የሚፈጥርልን ነው ሲሉ በአዲስአበባ ከተማ የስራ አስኪያጅ ልዩ ወረዳ ሰብሳቢ አቶ ተፈራ ሞላ አመለከቱ። በአዲስ አበባ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ልዩ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ በየደረጃው ላሉ አመራሮችና አባላት "በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እምርታ"" በሚል የአቅም ግንባታ ስልጠና በዛሬው እለት መስጠት ተጀምሯል። በስልጠናው የስራ አስኪያጅ የልዩ ወረዳ ሰብሳቢ እና የአዲስ አበባ ከተማ ም/ዋ/ስራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ሞላ እንደገለጹት በብልጽግና ፓርቲ እንደ አገርም እንደ ከተማም በየደረጃው ላሉ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ለልዩ ወረዳው አመራሮችና አባላት መሰጠቱ በዘርፋችን ልዩ እውቀትና አቅም የሚፈጥርልን በመሆኑ በተለይም በማዘጋጃ ቤታዊ የአገልግሎት አሰጣጥና ሌሎችም ስራዎቻችን እምርታዊ ውጤት ለማስመዝገብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል። አክለውም የመደመር መንግስት እሳቤ ተራማጅ መንግስት፣ አካታችና አቃፊ መንግስት፣ ለፍጥነትን እና ለፈጠራ ለአዳዲስ ሃሳቦች ትኩረት የሚሰጥ ስለሆነ በስልጠናው በሚሰጡት አራቱም ዘርፎች ላይ ተደማሪ አቅም በመፍጠር ሁለተናዊ ብልፅግናን የምናሳካበት ከንድፍ ሀሳብ በዘለለ የተግባር እምቅ አቅም ለመገንባት የታለመ የስልጠና ፕሮግራም ነው ሲሉም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በመድረኩም "በመደመር መንግስት እይታ የከተማ ልማት ዘርፎች እምርታ"" በሚል ርእስ የተዘጋጀውን ሰነድ የስራ አስኪያጅ ልዩ ወረዳ ምክትል ሰብሳቢና የጽዳት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ደሲሳ ያቀረቡ ሲሆን ከእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አህመድ መሐመድ ጋር ሰነዱን እያወያዩ ይገኛሉ። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

በዛሬው እለት በከተማችን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች አገልግሎት መስጠት የጀመረው አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት (Civil Registration and Vital Statistics with e-ID) ምን አይነት አገልግሎቶችን ይሰጣል? የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጄንሲ በኢትዮዽያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት የበለጸገ አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት (Civil Registration and Vital Statistics with e-ID) ቴክኖሎጂ በቀን ህዳር 27/2018 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ በክብርት ከንቲባ አዳነች አበቤ በይፋ ማስመረቁ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት (Civil Registration and Vital Statistics with e-ID) የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች እንንገርዎ፤  ባለጉዳዮች የምባይል ስልካቸውን እና የተለያዩ የቴክኖሎጂ አማራጮችን በመጠቀም በአካል ሳይገኙ ባሉበት ሆነው አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል፣  የሚከሰቱ ወሳኝ ኩነቶችን በወቅቱ መመዝገባ በሚቻልበት ሁኔታ ከኢምግሬሽን፣ ከጤና፣ ከፍርድ ቤት እና ከሎሎችም ተቋማት መካከል ቅንጅት እና መናበብን ይፈጥራል፣  ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር የተሳሰረ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑ ፣  የመታወቂያ አሰጣጥ ላይ ያለ ባለፋይሉ ባለቤት ይሁንታ ለማንም በእርሱ የቤት ቁጥር መታወቂያ እንዳይሰጥ መቆጣጠር የሚያስችል መሆኑ፣  ከዚህ ቀደም በወረቀት ይሰጡ የነበሩ የተለያዩ እንግልቶችን ያስቀራል ፣  ለተገልጋዮች መታወቂያ እና ሌሎች የምዝገባ ምስክር ወረቀቶችን አገልግሎት እንደአገኙ ወዲያውኑ ድጅታል ምስክር ወረቀት በሞባይል ስልክ እንዲደርስ ያደርጋል፣  መታወቂያን ጨምሮ ሌሎች የሚሰጡ የወረቀት እና ድጅታል ምስክር ወረቀቶች ምስጥራዊነታቸው የተጠበቀ እና ይህም ማረጋገጥ የሚያስችል የራሱ የሆነ ሲስተም (አፕሊኬሽን) ያለው ነው። ህዳር 29/2018 አ.ም ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የቤት አቅርቦትን ለመጨመር በግሉ ዘርፍ የሚደረጉ ጥረቶችን ማበረታታት አስፈላጊ ነው። ዛሬ ፊሶን ሪል እስቴት እየገነባቸው ያሉትን 1,000 ቤቶች ተዘዋውረን ተመልክተናል። እየተገነቡ ያሉት ቤቶች የከተማችንን ደረጃ ለማሻሻል የምንተገብረውን የግንባታ ስታንዳርድ የሚያሟሉ፣ ጥራታቸዉን የጠበቁ መሆናቸውን በጉብኝታችን አይተናል። ይህ ደግሞ ለኮፕ 32 ተሳታፊዎች አገልግሎት ለመስጠት ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር ነው። በዘርፉ የተሰማራችሁ የከተማችን አልሚዎች፣ እየገነባችሁ ያላችሁና ለኮፕ 32 እያደረጋችሁ ያለውን አጠቃላይ ቅድመ ዝግጅት በየክፍለ ከተማችሁ ብታሳውቁ የበለጠ ተቀራርቦ ለመስራት እና ጉባኤዉንም የበለጠ ዉጤታማ ለማድረግ ያግዛል። ለጉባኤው ወደ አገራችን የሚመጡ እንግዶቻችንን በትብብር ለማስተናገድ እና ለጉባኤዉ ዉጤታማነት በጋራ እንስራ ፣ ከወዲሁ እንዘጋጅ በማለት ለአልሚዎች ጥሪያችንን እናቀርባለን። ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የፒያሳ ነዋሪዎች የገቡበትን ሰፈር ጎበኙ፡

በመደመር መንግስት ዕይታ፣ የዘርፎች እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ ለተከታታይ ቀናት በመዲናችን አዲስ አበባ ሲሰጥ የቆየው 3ኛ ዙር የወረዳ አመራር ስልጠና በውጤታማነት ተጠናቅቋል። አመራሩ በቀረቡ የስልጠና ሰነዶችና በመስክ ምልከታዎች ተጨማሪ አቅም የገነባበት፣ እርስ በእርስ ልምድ በመለዋወጥ የተማማረበት፣ የግንዛቤ አድማሱን ያሰፋበት፣ ለአዲስ ግብና ስኬት የተዘጋጀበት፣ መነሳሳትን የፈጠረ የስልጠና መድረክ ነበር። መድረኩ በቀጣይም አመራራችን በስልጠናው ቆይታ ያገኘውን ግንዛቤ በተጨባጭ መሬት ማውረድ፣ ተግዳሮቶችን ወደ ዕድል መቀየር፣ በዚህም ያለምነው ሁለንተናዊ ብልጽግና እውን እንዲሆን በተሻሻለ የስራ ባህል 24/7 መትጋት፣ ለሕዝባችን የምንሰጠውን የአገልግሎት አሰጣጥ ፍትሃዊነት ማረጋገጥና ማላቅ፣ በከተማችን ነዋሪዎች ያለውን አዳጊ የልማት ፍላጎት እና ለዘመናት የተከማቸ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመፍታት ራስን ማዘጋጀት፣ እንዲሁም በማያቋርጥ ራስን የማብቃት፣ የፈጠራና የፍጥነት ዑደት ውስጥ ማለፍ እንደሚገባ መግባባት የፈጠርንበት ነው። በዋናነትም በትኩረት መስክነት በለየናቸዉ አገራዊ የግብርናና ገጠር ትራንስፎርሜሽን፣ የኢንዱስትሪ ዘርፍ፣ የቱሪዝምና ከተማ ልማት ዘርፎች እመርታን ለማስመዝገብ እንዲቻል ከአመራሩ በሚጠበቁ የመሪነት ሚናዎች እንዲወጣ ለማድረግ የጋራ መግባባት የፈጠርንበት ስኬታማ የስልጠና መድረክ ነበር። በማያቋርጥ “መፍጠር እና መፍጠን” መርህ እየሠራን የኢትዮጵያን ብልጽግና እናረጋግጣለን! ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ኢትዮጵያ ከተመፅዋችነት ተላቃ የአፍሪካ የስንዴ ምርት ቁንጮ ሆናለች ሲል አልሹሩቅ አል አረቢያ ዘግቧል:: የረሃብና የተመፅዋችነት ዘመን መሻገሯን የገለፀው ሚዲያው … See more

መንግሥታችን ሕዝብን ያዳምጣል፣ ከሕዝብ ለሚነሱ ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ ይሰጣል። በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በዛሬው እለት የጉባ_ብስራቶች_የመደመር_መንግሥት_ትሩፋቶች በሚል ርእስ የህዝብ ውይይት መድረክ ተካሔዷል። የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ቱሩፋት በሚል ርዕስ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የሕዝብ መድረኮች ላይ ከነዋሪዎቻችን ለተነሱ ጥያቄዎች፣ ቅሬታዎች እና አስተያየቶች በተግባር የተሰጡ ምላሾች፣ እንዲሁም ቀሪ ሥራዎችን አስመልክቶ በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል። በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በተካሔደው የህዝብ የውይይት መድረክ ወሮ አይናለም ንጉሴ የኢፌዲሪ ገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ክብርት አለም ፀሀይ ጳውሎስ የጠቅላይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት ሀላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚኒስትር፣የአዲስ አበባ ከተማ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ በጋራ መርተውታል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በከተማችን በተለያዩ የልማት ሥራዎች አስደናቂ ስኬቶች የተመዘገቡት መንግሥትና ሕዝብ አንድ ሆነው በመቀናጀትና በመናበብ ሊፈጽሟቸው በመቻላቸው መሆኑን በውይይቱ ተብራርቷል። በውይይቱ በመንግሥትና በሕዝብ ትብብር የተሰሩ በርካታ ሥራዎችን እና የተመዘገቡ ውጤቶችን ይበልጥ ለማጠናከር፣ እንዲሁም የሕዝብን ተሳትፎ ይበልጥ በሚያረጋግጡ ቀጣይ የጋራ ዕቅዶች ላይ ዳር ማድረስ እንደሚገባ መግባባት ተፈጥሯል። በውይይቱ ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ ባለሀብቶችና ምሁራንን ጨምሮ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ተሳታፈዋል::

የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ቱሩፋት በሚል ርዕስ ከነዋሪዎች ለሚነሱ ጥያቄዎች ተገቢን ምላሽ መስጠት የሚያስችል ህዝባዊ ውይይት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ተካሂዷል። በውይይቱ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ ባለሀብቶችና ምሁራንን ጨምሮ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ተሳታፊ ሆነዋል። ውይይቱን የመሩት የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ዶ/ር ተስፍዬ በልጅጌ :በሚኒስትር ማዕረግ የስትራቴጂክ ስራ አመራርና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ ኃላፊ አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር እና የአዲስ አበባ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ አብረሃብ ታደሰ ከህዝብ የተነሱ ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፤ መታየት አለባቸው ያሏቸውን ጉዳዮችም የቤት ስራም ወስደዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክፍለ ከተማው በተለያዩ የልማት ሥራዎች አስደናቂ ስኬቶች የተመዘገቡት፤ መንግሥትና ሕዝብ አንድ ሆነው በመቀናጀት መፈፀም በመቻላቸው ትልቅ ውጤት መጥቷል ያንን ውጤት በተሻለ መልኩ ለማስቀጠል ውይይቱ ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑን የውይይቱ ተሳታፊዎች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ውይይቱ በመንግሥትና በሕዝብ ትብብር የተሰሩ በርካታ ሥራዎችን እና የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማጠናከር፣ እንዲሁም የሕዝብን ተሳትፎ ይበልጥ ለማረጋገጥ እና ጠቃሚ ግብዓት የተገኘበት እንደሆነም ተገልፃል፡፡ #aa_prosperity