cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

✞ግቢ ጉባኤ✟

ለዩኒቨርስቲ ግቢ ጉባዔ አና ለኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች በሙሉ የተከፈተ ነዉ በዚህ channal የኦርቶዶክስን ዶግማ ቀኖና አና ትውፊት የጠበቁ ✞ትምህርቶች ✞✞መዝሙሮች ይለቀቃሉ ይቀላቀሉን

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
2 644
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Gaaffilee Ortodoksootaa hatattamaan deebii Mootummaa barbaadan! 1. Ergaalee fi qabiyyeen Heera mootummaa, ejjennoo siyaasa partilee, Barumsa idilee fi qabiyee midiyaalee keessaatti kalaqamuun Ortodoksootaa fi Barumsa Ortodoksii jibbaa fi balaa adda addaaf saaxilan hatattamaan seeraan akka dhorkaman. 2. Ortodoksoota adda baasee Carraa hojii kan dhorku, angoo itti gafatamummaa mootummaa keessatti akka gahee hin arganne, carraa qabeenya horachuutti akka hin fayyadamne kan taasisu, Caasaan mootummaa Amantaa sadarkaa federaalaa hanga gandaatti diriire hatattamaan dhaabbatee, Amantaa kan bu’uureffate osoo hin taane Ummata giddu gala kan godhate ta’uun isaa hojiin akka mul’atu. 3. Mana Kiristaana Ortodoksii Tawaahido Itophiyaa shira siyaasaatiin qooqaaniifi Sabaan diiguuf yaaliin taasifamu, akkasumas maqaa qorannoo sayinsiitiin shirriiwwan tokkummaa Mana Kiristaanaa diiguuf taasifaman akka dhorkaman. 4. Gochaaleen Ortodoksoota dimshaashaan ajjeesuu, qe’ee isaaniirraa buqqisuu, miiraan daraaruu, Mirgoota isaanii sarbuu, hirmaannaa Siyaasaa fi waltajiilee biyyoolessaa keessaa fo’u hatattamaan akka dhabbatan. 5. Yaakkawwan hanga Ammaatti Mana Kiristaanaa fi Ortodoksoota irratti rawwatamaniif yakkamtoonni seeratti akkaa dhiyaatan. Akkasumas midhamtoonni hundii fi kanneen qe’ee isaaniirraa buqa’an Beenyaa fi gumaa akka argatan. 6. Guutuu biyyatitti Ortodoksoonni qe’ee isaaniirraa buqa’an hatattamaan gara qe’ee isaanitti akka deebi’anii fi mirigi isaanii akka kabajamu. 7. Moqsa Itoophiyaa ishee haraa ijaarra jedhuun Ashaaraa fi Mallatoolee seenaa Ortodoksii balleesuuf adeemsi taasifamu hatattamaan akka dhaabbatuu fi shira ummatarratti jalqabame kanaaf ifaan dhiifamni akka gaafatamu. Gochaaleen badii rawwatamanis akka sirreeffaman. https://chng.it/2zsqkZ9QLN
Показати все...
Can you spare a minute to help this campaign?

Prevent Cultural and Religious Based Genocide of Ethiopian Orthodox Christians.

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ሞዐ ተዋሕዶ የሞዐ ተዋሕዶ ጥሪ ለኦርቶዶክሳዊያንና በማንኛውም የእምነት መሥመር  ውስጥ ለሚገኙ እና ለሰው ልጅ እኩልነት፣ በነፍስ የመኖር መብት፣ የዜግነት ክብር የማግኘት እና አምልኮተ እግዚአብሔርን በነፃነት የመፈጸም መብት ለምታምኑ ሁሉ፡-  ጉዳዩ፡- የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትናን  ማንነት (Cultural and religious identity) እና የኦርቶዶክስ ክርስቲያንን ዘር ማጥፋትን (Orthodox Christian Genocide ) ስለ መከላከል ፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን እንደ አንድ የሃይማኖት ሥርዓታዊ ተቋም ለማዳከምና ተከታዮቿ ክርስቲያኖችን ለማጥፋት ግልጽ ርእዮተ ዓለማዊ፣ ሥርዓታዊና መዋቅራዊ ጥቃት ከተጀመረበት ከ1966 ዓ.ም. እስከ ዛሬ ድረስ ጥቃቱ ቀጥሏል።  በአብዮት፣ በብሔር እኩልነት፣ በመንግሥት ለውጥ እና በጎሣ ግጭት ስም ተሸፍኖ  ሲካሄድ ቆይቶ በአሁኑ ጊዜ ወደ ግልጽ ጥቃት ተሸጋግሯል።   በተለም ባለፉት 4 ዓመታት በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በደቡብ ክልል፣ በኦሮሚያ ክልል፣ በአዲስ አባባ ከተማ፣ በአማራ ክልል ልዩ ዞኖች፣ በሶማሌ ክልል፣ በትግራይ ክልል አክሱም  ዳንግላት ማርያም ወዘተ ኦርቶዶክሳዊያን በሃይማኖታቸው ምክንያት ከፍተኛ ፍጅትና ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል፣ አቢያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፣ ክርስቲያኖች ተፈናቅለው ተሰዳዋል። ኦርቶዶክሳዊንን ማግለል፣ መግደልና ሁለገብ ጥቃት ሥር ማዋል በግልጽ ቢካሄድም አጥፊዎች ሲቀጡ፣ የዜጎችን ደኅንነት መጠበቅ የሚገባው የመንግሥት መዋቅር ግዴታውን ከመወጣት ይልቅ ሲሸፋፍን ማየት የተለመደ  ሆኗል።   ኦርቶዶክሳዊያንን በገዛ አገራቸው በዘር በቋንቋ እየከፋፈሉ፣ ድብቅ የዘር ፖለቲካ አጀንዳን ወደ ፖለቲካዊ ርእዮት በማሳደግ፣ በመደራጀት፣ በመዋቀርና አመራር በመሥጠት ኦርቶዶክሳውያንን የማጥፋት ሂደቱን ዝም ሊባል ከማይገባው ደረጃ ላይ ደርሷል።   በመሆኑም የፌዴራል መንግሥት እና የክልል መንግሥታት እና መዋቅሮቻቸው  የዜጎችን ሰላምና ደኅንነት የኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ግፊት ለማደርግ የተባበረ ድምጽ ማሰማት ጊዜ የሚሰጠው አይደለም።   እናም “እዚህ ላይ ይበቃል” ማለት ይገባል የምትሉ ሁላችሁ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች እና በሰው ልጅ እኩልነትና ክብር የምታምኑ የሌላ እምነት ተከታዮች ሁሉ ይህን ፔትሽን በመፈረም ለእውነት፣ ለፍትሕ፣ ለሰብአዊነት እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን። እውነትና ፍትሕ ለዘላለም ያሸንፋሉ!!! አስቸኳይ የመንግሥት ምላሽ የሚፈልጉ የኦርቶዶክሳዊያን ጥያቄዎች 1.      በሕገመንግሥት፣ በፖለቲካ ማኒፌስቶ፣ በመደበኛ ትምህርት፣ በሚዲያና መሰል መንገዶች ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮንና ኦርቶዶክሳዊያንን ለጥቃት የሚያጋልጡ መልዕክቶች በአስቸኳይ በሕግ እንዲታገዱ:: 2.     ኦርቶዶክሳዊያንን ለይቶ ከሥራ፣ ከመንግሥት ኃላፊነት፣ ከሀብት ማፍራት እድሎች የሚያገል ከቀበሌ እስከ ፌደራል የተዘረጋው ሃይማኖታዊ መንግሥትና መዋቅር በአስቸኳይ እንዲቆምና ሃይማኖታዊ ሳይሆን ሕዝባዊ መሆኑን በተግባር እንዲያረጋግጥ:: 3.     ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን በቋንቋና በተለያዩ ዘውጎች ለመከፋፈል የሚደረገው ፖለቲካዊ ጥረት በጥናትና በምርምር ስም የሚደረጉ የመከፋፈል ዘመቻዎች እና ተግባራት እንዲታደጉ:: 4.     በኦርቶዶክሳዊያን ላይ ያነጣጠሩ የአካል፣ የሥነልቦና፣ የኢኮኖሚ፣ የማኀበራዊ፣ የፖለቲካ፣ የማፈናቀል፣ ከአገራዊ ተሳትፎ የመገለልና የፍጅት ጥቃቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ:: 5.     እስከ አሁን የተፈጸሙ ጥቃቶች በዝርዝር ተገልጾ አጥፊዎች ለሕግ እንዲቀርቡ እና የተጎዱት እንዲካሱ:: 6.     በመላው አገሪቱ የተፈናቀሉ ኦርቶዶክሳዊያን ወደ ቀደመ ቦታቸው እንዲመለሱ:: 7.     “አዲሲቷ ኢትዮጵያ” በሚል ሽፋን ኦርቶዶክሳዊ አሻራዎችን የማጥፋት ፖለቲካዊ ሂደት በአስቸኳይ እንዲገታ እና በግልጽ ይቅርታ ተጠይቆ እርምት እንዲወሰድ https://chng.it/2zsqkZ9QLN
Показати все...
Can you spare a minute to help this campaign?

Prevent Cultural and Religious Based Genocide of Ethiopian Orthodox Christians.

ሰበር ዜና - አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጠራ !!! ጥር 2 ቀን 2014 ዓ.ም (ተሚማ/አዲስ አበባ) *** የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በመስቀል አደባባይ ጉዳይ ለመነጋገር አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጠርቷል። በሀገር ውስጥ የሚገኙ ብፁዓን አባቶች በምልዓተ ጉባኤው እንዲገኙ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ለብፁዓን አባቶች የስልክ ጥሪ እያደረገ እንደሚገኝ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ ነገ ከቀትር በኋላከ 9:00 ሰዓት ጀምሮ እንደሚከናወን ይጠበቃል #Ethiopia ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል አባቶች አለን ካሉን እኛም አለን ብለን ልንከተላቸውና ረቡዕ ቦሌ መድኃኔዓለም 10 ሰዓት ላይ እንገናኛለን።
Показати все...
7.61 MB
4.67 MB
👏ጊዮርጊስ ኃያል2× መስተጋድል👏     👏ገባሬ ተዓምር2× ኮከበ ክብር 👏              ◦◦◦      🍂 #ቅዱስ_ጊዮርጊስ ሆይ     ከላይ ባለ በሰማይ  ከታች ባለ በምድር    በብዙ ወገን ለእርዳታ ፈጥነህ አደራረስህ    የኤፍራታ ርግብ እነደ ተባለችው እመቤትህ ማርያም ነው    በመሆኑም በእናትህ ቴዎብስታ ስም   እንደ ስምህ መንታነት የባለሟልነት ስምህን    ትሰጠኝ ዘንድ እማልድሀለው።         ( መልክዐ ጊዮርጊስ )    የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት በረከት አየለየን    🙏 ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይሰውረን 🙏 ሠዐሊ ቀሲስ አማረ ክብረት እንደሣሉት ዲ/ን ጌታባለው አማረ ( ሠዐሊ ) @deacongetabalewamare @deacongetabalewamare
Показати все...
#ድንግል_ሆይ_ከሚያስብ_ሁሉን_ከማይዘነጋ_ከልጅሽ_ዘንድ_አሳስቢ           ◦◦◦ #ድንግል_ሆይ በቤተልሔም ካንቺ የተወለደውን መወለድ በጨርቅ የተጠቀለለውንም አድግና ላህም በብርድ ወራት እስትንፋስን ያሟሟቁትንም #አሳስቢ           ◦◦◦ #ድንግል_ሆይ ርጉም በሆነ በሄሮድስ ዘመን ከርሱ ጋራ ከሀገር ወደ ሀገር ስትሸሺ ካንቺ ጋራ መሰደዱን #አሳስቢ           ◦◦◦ #ድንግል_ሆይ ከዐይኖችሽ የፈሰሰውንና በተወደደ ልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር ዕንባ #አሳስቢ           ◦◦◦ #ድንግል_ሆይ ረኃቡንና ጥሙን ችግሩንና ኃዘኑን ከእርሱ ጋራ የደረሰብሽንም ጭንቅ ሁሉ #አሳስቢ           ◦◦◦ ጥፋትን ያይደለ ይቅርታን አሳስቢ መዓትን ያይደለ ምሕረትን አሳስቢ ለጻድቃን ያይደለ ለኃጥአን አሳስቢ ለንጹሐን ያይደለ ለተዳደፉት አሳስቢ           ◦◦◦    #ሠዓሊ_ቀሲስ_አማረ_ክብረት እና እኔ #ሠዓሊ_ዲን_ጌታባለው_አማረ ልጃቸው በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማን ከቀኖና ስርዓትን ከትውፊት የጠበቁ ቅዱሳት ስዕላትን ሰዓልያን  @deacongetabalewamare @deacongetabalewamare https://www.instagram.com/p/CVrwgAeIAyb/?utm_medium=copy_link
Показати все...
🍂 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት ያስነሣው #የማርታ_እና_የማርያም #እንተ_ዕፍረት_ወንድም #የአልዓዛር ሥጋው ከቆጵሮስ የፈለሰበት መታሰቢያ ሆነ #ጥቅምት_21 ከክርስቲያን ነገሥታት አንዱ የሆነ ሥጋው በቆጵሮስ እንዳለ በሰማ ጊዜ ከቆጵሮስ ደሴት ወደ ቁስጥንጥንያ አፈለሰው። ሊአፈልሱትም በወደዱ ጊዜ በከበረ የደንጊያ ሣጥን ሆኖ በምድር ውስጥ አግኝተውታል በላዩም እንዲህ የሚል ጽሑፍ ነበረ #ይህ_በመቃብር_ውስጥ_አራት_ቀን_ከኖረ_በኋላ_ከሙታን_ለይቶ_ላስነሣው_ክብር_ይግባውና_የጌታችን_የኢየሱስ_ክርስቶስ_ወዳጁ_የሆነ_የቅዱስ_አልዓዛር_ሥጋ_ነው። ይህንም በተመለከቱ ጊዜ ደስ ተሰኝተው ተሸክመው ወደ ቁስጥንጥንያ አገር ወሰዱት ካህናቱም ሁሉ ወጥተው በታላቅ ክብር በመዘመርና በማመስገን ተቀበሉት በአማረም ቦታ አኖሩት በዚህችም ቀን በዓልን አድርገዎል። 🙏 የቅዱስ አባታችን አልዓዛር ረድኤት በረከት አይለየን🙏 ቢታንያ በተባለች ከኢየሩሳሌም በስተምስራቅ15 ምዕራፍ ማለትም 5 ኪ.ሜ  በምትርቅ ከተማ ማርታ እና ማርያም ( እንተ ዕፍረት ) ከወንድማቸው ከአልዓዛር ይኖሩ ነበር ።ወንድማቸው አልዓዛር ተሞ ነበርና ፤ ወደ ጌታችን መልእክተኛ ላኩ። ጌታችን ግን ትንሣኤና ሕይወት መሆኑን በእርሱም ያመኑ አንደማይሞቱ ስለ ትንሣኤ ሙታን ያስተምራቸው ዘንድ ፍቃዱ ነውና በዕለቱ ይሄድ ዘንድ አልወደደም ከሁለት ቀንም በኋላ ሄደ። ቢሄድ ግን አለዓዛር ሙቶ ነበር። 🍀 በዚህም ቀን ቶሞስ በሞት ጉዳይ ሀሳብ ሲሰጥ እንሰማዋለን      ቁ.15 " ከእርሱ ጋር እንሞት ዘንድ እኛ ደግሞ እንሂድ "      ጌታችንን አይሁድ ሊይዙት ሊገድሉት እንደሚፈልጉ ስላወቀ ወደዚያ ከምንሄድ ከአንተ ሳንለይ እዚሁ መሞት ይሻለናል ማለቱ ነበር። ያን ጊዜ ጌታችን " ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ " ብሎ አጸናቸው። ✨ ይህ ሁሉ ግን ወደ ቢታንያ ሳይሄድ ነበር ጌታችን የአልዓዛርን መሞት የነገራቸው። በዚያ ከደረሱ በኋላ ግን መድኃኒታችን    👉 ወዴት አኖራችሁት ፦ አላቸው አስቀድሞ አዳምን በገነት ወዴት ነህ ያልኩት እኔ ነኝ ሲላቸው       ኢየሱስም በአልዓዛር መሞት አዘነ አለቀሰም ማልቀሱም ስለ 3 ነገር ነው። 1, ፍጹም አምላክ እንደሆነ ፍጹም ሰው መሆኑን ለማስረዳት     ✨ሰብአዊ ፍጡር የሆነ ጽኑዕ ሐዘን ሲሰማው ያነባልና 2, የሰው ልጆችን የሚወድ መሆኑን ለመግለጽ     ✨ የእንባውን መፍሰስ የተመለከቱ አይሁድ       " እንዴት ይወደው እንደነበር እዩ " 3, ማኅበራዊ ኑሮን ለማስተማር       ✨ " ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችኁ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ "  እነዲል ቅ.ጳ ( ሮሜ 12 ፥ 15 ) ከዚያም ከሞተ አራት ቀን የሞለውን አልአዛር ከሞት አስነሣው ፍቱትና ይሂድ ብሎ ትንሣኤ ሙታን መኖሩን የማያምኑ ሰዱቃውያንን ከሞት በኋላ ስላለው ሕይወት አስተምሯቸዋል።    👉 አልዓዛር ቢነሣ አስነሺ ክርስቶስን ይሻል    👉 አልዓዛር ቢነሣ ዳግም ሞቷል   👉 አልዓር ቢነሣ ሊሞት ነው ሞቶም በዳግም ትንሣኤ ይነሣል   አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቢነሳ ✨ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ አንዲት በሆነች በራሱ ሥልጣን ነው ✨ ጌታችን ቢነሣ ልዩ በሆነ ትንሣኤ ነው። ✨ ጌታችን ቢነሣ ለዘለዓለም ሕያው ነው።          " ክርስቶስንም ቢሆን በስጋ ያወቅነው ብንሆን እንኳ             ከእንግዲህ እንደዚህ አናውቀውም " እንዲ ቅ.ጳው የሞታችን ትንሣኤ ፤ የትንሣኤያችንም በኲር መድኃኔ ዓለም      ትንሣኤ ህሊናን፣ ትንሣኤ ልቡናን፣ ያድለን ሠዐሊ ቀሲስ አማረ ክብረት እንደሳሉት ዲ/ን ጌታባለው አማረ ( ሠዐሊ ) @deacongetabalewamare @deacongetabalewamare https://www.instagram.com/p/CVqLJPYIsoN/?utm_medium=copy_link
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.