cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

🦋እራስን ፍለጋ🦋🦋67

ቢራቢሮዎች ነን ኑ አብረን እንብረር ።ለራሳችን የሚያስፈልገንን እየወሰድን ትውልድን እንቃኝ ወጣትነታችንን ሳንቆጭበት በደስታ እናሳልፍ ኑ ለትውልድ አብረን እንስራ ይቀላቀሉን 👇👇👇 @erasnflega77 ይጫኑት ያገኙናል ሌላ ስንከተል ከራሳችን ጋር እንዳንተላለፍ

Більше
Рекламні дописи
1 055
Підписники
+224 години
+17 днів
-830 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Eid mubarek My bestiea!!!!!🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🫣🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🌻🌻🌻🌻🌻🌻
Показати все...
የሙዚቃው ፈርጥ ዘፋኙ የአሁኑ ዘማሪ ሙሉቀን መለሰ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል
Показати все...
ምንም ብር ሳይኖረኝ ያልተገደበ ኢንተርኔት(unlimited package)(free internet)#internet #u... https://youtube.com/watch?v=2mQ41j5barE&si=f4Oen9EU-tlhXyhq
Показати все...

የሞተ ቢናገር . ስንኖር ያልተረዳን ስንሞት አለቀሰ በቁም ያልጎበኘን ለቀብር ደረሰ በአንቋሸሸን መዳፍ ፅድቅን ተቆናጀን በእኔ ያርገው ለቅሶ ከአፈር ተወዳጀን አብረን ካልተቀበርን የሚለው ጎረፈ ከሀውልታችን ግርጌ ስማችን ተፃፈ ሊሾን አለበሱን ቆመው በእየተራ ሞትን ያጣጣለ በእኛ መሞት ፈራ . ፍትሀት እግዚኦታ ላኩ ለነፍሳችን ይማረኒ ብለው ለሰራን ጌታችን እሪታ እና ዋይታው ቆመ በሰዓታት የመጣን መቻል ነው! በማፅናኛ ቃላት ታሪክ ሆነን ቀረን የቀናት ትዝታ በሰው የታሰረ በአምላክ ተፈታ . በኪሩቤል አሰፋ ገጣሚው @erasnflega @erasnflega
Показати все...
#በድጋሜ⚠️ ውድ ቤተሰቦቻችን ጥንቃቄ አድርጉ። በሀገራችን ያለውን ከፍተኛ የሆነ የኑሮ ጫናን ለመቋቋምና ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት እንዲሁም አንዳንድ ጊዜ ብዙ ሳይደክሙ በርካታ ገንዘብ ለማግኘት በሚደረግ ጥረት በርካታ የሀገራችን ልጆች ደክመው በላባቸው ያገኙትን ፤ ከቤተሰብም ለስራ በሚል የተቀበሉትን ብር በኦንላይን አጭበርባሪ ዘራፊዎች በየዕለቱ እየተበሉ ይገኛል። ከዚህ ቀደም መላው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በኦንላይን ከሚደረጉ የማጭበርበር ስራዎች እራሳችሁን እንድትጠብቁ የአደራ ማሳሰቢያ መላክችን ይታወሳል። አሁንም ሰዎች በመቶ ሺህ የሚቆጠር ብራቸውን እየተበሉ ይገኛል። እባካችሁን በ " ዋትአፕም " ይሁን በ " ቴሌግራም " አድራሻችሁን አግኝተው የሚያናግሯችሁን የማታውቋቸውን ሰዎች መልዕክት አትመልሱ። " በተለያየ ኦንላይን ስራ ፣ በፎሬክስ ትሬዲንግ እና በሌሎችም በትንሽ እና በማያደክም ስራ ትርፋማ እናደርጋችኋለን ፤ ይሄን ይሄን ስራ ስሩ በዚህ አካውንት ገንዘብ አስገቡና እኛም መልሰን ትርፉን እናስገባለን " የሚሉ አጭበርባሪዎች ተንሰራፍተዋልና ተጠንቀቁ። በነገው ዕለት ከዚህ ጋር በተያያዘ ስላጋጠመ ክስተት እናጋራችኃል። ለአሁኑ ግን ምናልባት " ይሄን ስራ ስሩና ትርፋማ ትሆናላችሁ ፤ ገንዘብ ላኩና ትርፉን እንልካለን " በሚል እያባበሉ ገንዘብ እድትልኩ የሚጠይቋችሁን ሰዎች ከማናገር ተቆጠቡ፤ ምንም ገንዘብም አትላኩላቸው። @tikvahethiopia
Показати все...
ሀገራችን ኢትዮጵያ የመቻቻል የመከባበር የአብሮነት ሀገር ማሳያ መሆኗን የምናውቀው በዚህ ነው ዛሬ ታላቁ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ፆም እና የሙስሊም እምነት ተከታዮች ረመዳን ፆም ገብቷል የግቢያችን ተማሪዎች ፆሙ የሰላም ይሁንላችሁ እያለ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን @erasnflega @erasnflega
Показати все...
ትራማዶልን ተገቢ ባልሆነ መንገድ መጠቀም ለድንገተኛ ሞት ያጋልጣል #Ethiopia | ትራማዶልን ከሐኪም ፈቃድ ውጪ በአንድ ጊዜ አብዝቶ መውሰድ ከድንገተኛ ሞት እስከ ቀጣይነት ያላቸው የጤና ዕክሎች እንደሚያጋልጥ ተጠቆመ፡፡ ትራማዶል የተሰኘው ጊዜያዊ የህመም ማስታገሻ ተገቢ ባልሆነ መንገድ እየተዘወተረ እና ሱስ እየሆነ የወጣቶችን ጤና እያመሳቀለ መሆኑን በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ባለሙያ የሆኑት ዶ/ር መስፍን በኃይሉ ገልጸዋል፡፡ በአብዛኛው ከ8ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች በትራማዶል ሱስ እንደሚጠመዱ ጠቅሰው÷ ያለ በቂ ምክንያት እና ተዘውትሮ ሲወሰድ ወደ ሱስነት እንደሚሸጋገር አስረድተዋል፡፡ የትራማዶል ሱስ በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋ ያለ አደገኛ የሥነ-አዕምሮ ችግር ነው ያሉት ባለሙያው÷ ከድንገተኛ ሞት እስከ ቀጣይነት ያላቸው የጤና እክሎች እንደሚያስከትል አስረድተዋል፡፡ በአንድ ጊዜ በብዛት ከተወሰደም ለሞት ይዳርጋል ማለታቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሣይንስ ኮሌጅ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ በተጨማሪም የአንጎል ንዝረት፣ የኩላሊት መድከም (መባባስ)፣ ለጡንቻ መቅለጥ እና ለከፋ የሥነ-ልቦና ችግር እንደሚዳርግ አንስተዋል፡፡ አንዳንድ ወጣቶች ኪኒኑን በመውሰድ ሱሳቸውን ማብረድ ሲሳናቸው በመርፌ መውሰድ እንደሚጀምሩ አመላክተው÷ ይህ ሁኔታም ለስትሮክ እንደሚያጋልጥ ጠቁመዋል፡፡ 🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋 @erasnflega🦋🦋🦋 @erasnflega🦋🦋🦋🦋
Показати все...
የየካቲት 12 ሰማዕታት #Ethiopia | በዛሬው ቀን በግፍ ለተጨፈጨፉ ከ30 ሺህ በላይ ንፁህ ኢትዮጵያዊያን በአምስቱ የፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ዘመን ከተፈጸሙት ግፎች አንዱ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ የተፈጸመው በታሪክ ይጠቀሳል። አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም የተባሉ ሁለት ወጣቶች በግራዚያኒ ላይ ቦምብ ጥለው ካቆሰሉት በኋላ አዲስ አበባ የቂም በትር አረፈባት፡፡ በተናደዱ የፋሽስት ወታደሮች በሺ የሚቆጠር ወገኖች ደም ሜዳ ፈሰሰ። ለመናገር የሚሰቀጥጥ ግፍ ተፈፀመ። በአዲስ አበባ ከተማ ለሦስት ቀናት በዘለቀው ጭፍጨፋ ብቻ 30 ሺ ኢትዮጵያውያን ሰማዕት ሆኑ። እነሆ ለዚህ ታላቅ መሰዋዕትነት መታሰቢያ ይሆን ዘንድ በአዲስ አበባ ስድስት ኪሎና በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሐውልቶች እንዲቆሙ ተደረገ። የዘመናችን የጥበብ ፈርጥ እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) አያቶቻችን የከፈሉልንን ዋጋ እንዲህ ገልፃዋለች። "የተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነፃነት ሰው ተከፍሎበታል ከደምና ካጥንት ትናገር አድዋ ትናገር ትመስክር ትናገር ሃገሬ እንዴት እንደቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬ..." *** ስለ የካቲት 12 ቀን እልቂት ጳውሎስ ኞኞ የኢትዮጵያና የኢጣሊያ ጦርነት በተሰኘ መፅሐፉ እንዲህ ያስነብበናል ...የኔፕልስ ልዕልት በመወለዷ ግራዚያኒ የደስታ መግለጫ ገንዘብ እሰጣለሁ ብሎ ከዛሬው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከድሮው ቤተመንግስት ድሆች እንዲሰበሰቡ አዘዘ:: ከድሆቹም በስተቀር ታላላቅ የኢጣሊያ ሹማምንት የሜትሮፓሊታን ጳጳስ አቡነ ኪርልና ሌሎችም መኳንንት ነበሩ:: ለእያንዳንዱ ድሃም ሁለት ማርትሬዛ ብር እንዲሰጥ ተወስኖ ነበር:: እኩለ ቀን ገደማ ላይ 3000 የሚሆኑ ድሆች ከቤተ መንግስቱ ገቡ:: ጓደኛማቾቹ አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም በዓሉ ከሚደረግበት ቦታ ቀደም ብለው ደርሰዋል:: ሁለቱም በኪሶቻቸው ቦንብ ይዘዋል:: ማርሻል ግራዚያኒ ለተሰበሰበው የአዲስ አበባ ሕዝብ ንግግር ሲያደርግ የያዙትን ቦንብ ወረወሩት:: ለ3ኛ ግዜ የተጣለው ቦንብ የፋሽስት ኢጣሊያ መኳንንት ካሉበት ቦታ ፈነዳ:: ግራዚያኒ በጀርባው ወደቀ:: በቀጠለው ጥቂት ደቂቃ ውስጥ ሌሎች ቦንቦች ተከታትለው ተጣሉ:: ከጥቂት ግዜ በኋላ (ያለማቋረጥ ለ3ሰዓት ከተካሄደው ተኩስ በኋላ) ባለ ጥቁር ሸሚዞች የኢጣሊያ ሾፌሮች የቅኝ ግዛት ወታደሮች በአዲስ አበባ ከተማ እየዞሩ ሕዝቡን ይፈጁት ጀመር:: የካቲት 12 ቀን የጀመረው እልቂት በ3 ቀን 30,000 ሰዎች በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ከተገደሉ በኋላ ሌላው እየታፈሰ ወደ በረሃ እስር ቤቶች ተላከ... የተከፈለልንን አንረሳም! ክብር ለሰማዕታት! *** የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም #Ethiopia | የኢትዮጵያ ሰማዕታት ቀን ... አገር ተቃጠለ! እሳተ ጎመራ ወረደ ከሰለ። ጭስ አመድ አዋራ ሰማዩን ሸፈነው ጥቁር ሰማይ ጥቁር! ሸፈነውጨለማ ሞት በእናት ቅድስት አገር በጀግናው ሕዝብ ላይ የጠላት ግፍ ቀንበር። ፋሽስት አስተጋባ ፋስ ተሰነዘረ ባካፋ መጆሻ ሕዝቡ ተወገረ።.... ክብር ለሰማዕታት! የተከፈለልንን አንረሳም! የሰው ጭንቅላት ኳስ።…… አባቶች ተረዱ እናቶች ታረዱ ቤት ንብረት ፈረሰ ከብቶቹ ተነዱ። ዓለም መና ቀረ * ገብረ ክርስቶስ ደስታ (መንገድ ስጡኝ ሰፊ _ የደም ቀን) ክብር ለሰማዕታት! የተከፈለልንን አንረሳም!
Показати все...
Показати все...
እጅግ ልብ የሚነካ ለአስፋው መሸሻ የተገጠመ ግጥም#ወንድምሀይሉ#ebstvworldwide

#አሳዛኝግጥም#asfawmeshesha#foryou #ebs #ebstvworldwide #እሁድንበኢቢኤስ #mekdesdebesay #nafkottube #tinsaebirhan#tv #viral #amu #poem #😭😭😭😭😭😭😭

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ፍቅራችሁን አሳዪኝ ስለምታደርገለን እናመሰግናለን ክብረት ይስጥልኝ
Показати все...