3 462
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
+930 день
Архів дописів
3 462
የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆነ።
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለሚከታተሉ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ መደረጉን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ተማሪዎች ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ፦
➡️ በዌብሳይት፦ https://student.ethernet.edu.et
➡️ በቴሌግራም ቦት @moestudentbot ምደባቸውን ማየት እንደሚችሉ ገልጿል።
የRemedial ፕሮግራም ምደባ በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
#MoE
@tikvahethiopia
3 462
የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ።
ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የRemedial ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸውን አሳውቋል።
1. በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33% ከመቶ እና ከዚያ የተቆረጠ መሆኑን።
2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡን ያሟሉ ብቻ ይሆናሉ።
የመቁረጫ ነጥብ ፦
➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216
➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204
➡️ ታዳጊ ክልል እና አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198
➡️ የማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198
➡️ ማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዓይነስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165
#MoE
@tikvahethiopia
3 462
🚨 ከርዕስ ውጪ ሰበር ዜና
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው በአማካይ ውጤታቸው 49.50 - 49.99 በመቶ ያመጡ ተማሪዎች ውጤታቸው ወደ 50 በመቶ የሚጠጋጋ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
በዚህም መሰረት 49.50 እና በላይ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች፥ ዝቅተኛውን 50 በመቶ የማለፊያ ነጥብ ያሟሉ ሆኖ የተወሰነ መሆኑን በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን መስከረም 20/2018 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከ ደብዳቤ ያሳያል።
በመሆኑም 49.50 እና በላይ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመግባት መማር እንደሚችሉ ሚኒስተሩ ገልፀዋል።
🚨 300 ነጥብ የነበረው የየኒቨርሲቲ መግቢያ ወደ 297 የተጠጋጋ መሆኑን ትምህርት ሚኒስትሩ አስታውቋል። በነዚህ ሽርፍራፊ ነጥቦች ቀርቶባችሁ የነበረ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን።
@Bisrat_sport_433et @Bisrat_sport_433et
3 462
በመጨረሻም ውጤት ተለቋል።
ውጤታችሁን ለማየት
1. result.eaes.et
2. result.neaea.gov.et
3. SMS 6284 ተጠቀሙ
ትምህርት ሚኒስቴር ✅
✅ ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
3 462
ውጤት ይፋ ሆኗል‼️
የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎች ይፋ ሆነ‼️
የ2017 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተፈተኑ ተፈታኞች በሚከተሉት አድራሻዎች ዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ፡፡ ዌብ ሳይትና ቴሌግራም አድራሻ የሚጠቀሙ ተፈታኞች ጊዜያዊ ሰርቲፊኬታቸውን ወዲያውኑ አውርደው (download አድርገው) መውሰድና መጠቀም ይችላሉ፡፡
አድራሻዎቹ፡
1. ዌብ ሳይት፡ https://result.eaes.et
2. ቴሌገራም፡ https://t.me/EAESbot
3. አጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡ 6284 ማየት ይችላሉ።
3 462
የ12ኛ ክፍል ዉጤት ሲለቀቅ በፍጥነት መረጃ ምታገኙበት እንዲሁም ውጤታችሁን ያለሰርቨር መጨናነቅ እንድታዩ የሚያግዛችሁን ቻናል አሁኑኑ ይቀላቁ! 👇
3 462
የ12ኛ ክፍል ዉጤት ሲለቀቅ በፍጥነት መረጃ ምታገኙበት እንዲሁም ውጤታችሁን ያለሰርቨር መጨናነቅ እንድታዩ የሚያግዛችሁን ቻናል አሁኑኑ ይቀላቁ! 👇
3 462
በሰኔ 2017 ዓ.ም የተሰጠውን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 48,929 ወይም 8.4% ተማሪዎች 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ በማምጣት የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸው ተገልጿል።
ውጤት ቢዘገይ እስከ ነገ መስከረም 05/2018 ዓ.ም ቀን 6:00 ሰዓት ይለቀቃል ተብሏል።
ውጤት የሚትመለከቱባቸውን አማራጮች ተከታትለን የምናደርሳችሁ ይሆናል።
@tikvahuniversity
3 462
+2
#MoE : የ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ የተዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ሙሉ ይዘት ከላይ ተያይዟል።
ትምህርት ሚኒስቴር ✅
✅ ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
3 462
እንኳን ለ2018 አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።
"2018 የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ፣ የጤና እና የሀብት አመት ያድርግላችሁ"
3 462
#MoE
ትምህርት ሚኒስቴር ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተማሪዎች ሞባይል ስልክ፣ ታብሌት እና መሰል ኤሌክትሮኒክስ ቁሶችን ይዘው ወደ ትምህርት ቤት እንዳይሔዱ ከልክሏል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን አጀማመር ላይ ከክልል እና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ጋር የበይነ-መረብ ምክክር አድርጓል።
የ2018 ትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ ሰኞ መስከረም 05/2018 ዓ.ም እንደሚጀመር ተገልጿል።
ተማሪዎች ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ታብሌት እና መሰል ኤሌክትሮኒክስ ቁሶችን ይዘው በትምህርት ቤት መገኘት ክልክል መሆኑን የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ገልፀዋል።
ባለፈው ዓመት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ጨምሮ ሁሉም ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት እና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ወላጆች፣ መምህራን እና የዘርፉ ባለድርሻዎች የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
@tikvahuniversity
3 462
#JinkaUniversity
ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለሁሉም አዲስ እና ነባር የመደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።
የመደበኛ ፕሮግራም ነባር ተማሪዎች፣ በ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እንዲሁም በ2018 ዓ.ም በሪሚዲያል እና በፍሬሽማን ፕሮግራም ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች፤ የ2018 ዓ.ም ምዝገባ መስከረም 05 እና 06/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
የ2018 ዓ.ም ትምህርት የሚጀመረው መስከረም 12/2018 ዓ.ም መሆኑን ተገልጿል፡፡
በሪሚዲያል እና ፍሬሽማን ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች ለምዝገባ ስትሔዱ የትራስ ጨርቅ፣ አንሶላ እና ብርድ ልብስ እንዲሁም ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ ያሉትን የትምህርት ማስረጃ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡
@tikvahuniversity
3 462
#DireDawaUniversity
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለነባር ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።
➫ ወደ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ቀን መስከረም 10/2018 ዓ.ም፣
➫ የምዝገባ ቀን መስከረም 12 እና 13/2018 ዓ.ም፣
➫ በ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የነበራችሁና የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ይህ ጥሪ አይመለከታችሁም። በተመሳሳይ Withdraw ያደረጋችሁ ወይም Readmission ተማሪዎችን አይመለከትም ተብሏል።
@tikvahuniversity
3 462
#HawassaUniversity
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለመደበኛ፣ የማታ እና የእረፍት ቀናት ፕሮግራም ነባር ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።
በዚህም የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ሴሚስተር ምዝገባ፦
➫ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ፕሮግራም እና የሁሉም የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች መስከረም ዐ8-09/2018 ዓ.ም
➫ የማታ እና የእረፍት ቀናት የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች፦ ከመስከረም ዐ8-10/2018 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።
የ2ኛ ዓመት መደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ በየተመደባችሁበት ካምፓስ ይከናወናል ተብሏል።
@tikvahuniversity
3 462
#MoE
ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ካላንደርን ይፋ አድርጓል፡፡
በትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ኮራ ጡሹኔ በቀን ነሐሴ 12/2017 ዓ.ም የተፈረመ የ2018 ትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ካላንደር ዝርዝር ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተልኳል፡፡
መስከረም 05-06/2018 ዓ.ም
➫ የመጀመሪያ ዓመት የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች (ሪሚዲያል ተማሪዎችን ጨምሮ) በየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ሪፖርት ያደርጋሉ፡፡
መስከረም 08-09/2018 ዓ.ም
➫ የሁሉም የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ተማሪዎች (ሪሚዲያል ተማሪዎችን ጨምሮ) ምዝገባ ያደርጋሉ፡፡
መስከረም 12/2018 ዓ.ም
➫ የሁሉም የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ተማሪዎች በቅጣት ምዝገባ፣
➫ የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት ይጀመራል፡፡
(ሙሉ የ2018 ትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ካላንደር ከላይ ተያይዟል፡፡)
@tikvahuniversity
3 462
#SidamaEducationBureau
በሲዳማ ክልል የ2017 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።
ተፈታኝ ተማሪዎች ውጤታችሁን በተከታዮቹ አማራጮች ማየት ትችላላችሁ፦
➫ ለ8ኛ ክፍል https://sidama.ministry.et እና ለ6ኛ ክፍል https://sidama6.ministry.et አድራሻ ላይ በመግባትና የተማሪውን የመለያ ቁጥር በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።
➫ በተጨማሪም በቴሌግራም ቦት አማካኝነት ውጤትዎን ይመልከቱ።
👉 @MinistryResultQMTBOT
👉 Start የሚለውን ይጫኑ፣
👉 ክፍልዎን ይምረጡ፣
👉 ከዚያ ክልልዎን ይምረጡ
👉 የምዝገባ መለያ ቁጥር እና የመጀመሪያ ስም በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።
➫ ማንኛውም ከውጤት ጋር የተያያዘ ቅሬታ ያላችሁ ተማሪዎች ቅሬታ ለማቅረብ፦ ለ8ኛ ክፍል (https://sidama.ministry.et/#/complaint) እና ለ6ኛ ክፍል (https://sidama6.ministry.et/#/complaint) አድራሻ ላይ በመግባትና በሚመጣው ቅጽ ላይ የመለያ ቁጥር እና የመጀመሪያ ስም በማስገባት Fetch Course የሚለውን ቁልፍ በመጫን ቅሬታ ማቅረብ የሚፈልጉበትን ይምረጡ። በመጨረሻም Add Complaint የሚለውን በመጫን ቅሬታችሁን ማቅረብ ይችላሉ።
ቪ.ፒ.ኤን. የሚጠቀሙ ከሆነ በቅድሚያ ማጥፋት አይዘንጉ፡፡
@tikvahuniversity
3 462
+1
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል፡፡
በክልሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠውን የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 75 በመቶዎቹ የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸው ተገልጿል፡፡
የተፈታኞች የማለፊያ መቁረጫ ነጥብ በመደበኛ 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ እንዲሁም ለአካል ጉዳተኞች 45 በመቶ እና ከዚያ በላይ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አንተነህ ፈቃዱ ገልፀዋል፡፡
85,547 ተማሪዎች በ1,803 ትምህርት ቤቶች ለመጀመሪያ ግዜ የተሰጠውን ፈተና የወሰዱ ሲሆን፤ 64,125 ተማሪዎች (75%) የማለፊያ ውጤት በማምጣት ወደ 7ኛ ክፍል መሸጋገራቸው ተጠቁሟል፡፡
424 ትምህርት ቤቶች (23.5%) በመቶ ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸውን የገለፁት ኃላፊው፤ 19 ትምህርት ቤቶች ካስፈተኗቸው ተማሪዎች ውስጥ ምንም ማሳለፍ አለመቻላቸውን አመላክተዋል፡፡
ውጤት ለማየት 👇
https://ce6.ministry.et/
@tikvahuniversity
3 462
ለአምስት ቀናት የተሰጠው የ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ዛሬ ተጠናቋል።
ከአራት ወራት በላይ የአቅም ማሻሻያ ትምህርት የወሰዱ 77 ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎች፥ የሪሚዲያል ፈተና እንደሚወስዱ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወሳል።
የሪሚዲያል ፈተናው በ41 ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በተዘጋጁ 64 የፈተና ማዕከላት መሠጠቱ ተገልጿል።
ምስል፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ
✅ ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ
https://t.me/Timhirtminister
