150
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
- Підписники
- Перегляди допису
- ER - коефіцієнт залучення
Триває завантаження даних...
Приріст підписників
Триває завантаження даних...
. [ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ]
=================
የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 2 / 2014 በወራቤ ከተማ አቡ በክር መስጂድ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ይጠብቀዎታል በእለቱም :-
(1) ሙሐመድ አሕመድ (ኢብኑ ሙነወር)
(2) ሰዒድ ሙሳ (አቡል ቡኻሪ)
(3) ዐብዱ ናሲር መንኑር (አልጃቢሪ) እና ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ይሳተፋሉ።
🌐 https://t.me/Abulbuhari/100
610
በነገራችን ላይ ሙስሊም ተማሪዎችን ፈተናና ፆም እየጠበቁ ማንገላታት እዚህ ሃገር ላይ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ልማድ ነው። አላማው ብዙ መልክ ያለው ነው። ከነዚህ ውስጥ አንዱ ስነ ልቦናቸውን በመጉዳት እና ዝግጅት እንዳያደርጉ በማስተጓጎል ውጤታቸውን ማበላሸት ነው። ችግሩን ለመፍታት በማህበራዊ ሚዲያ መጮሁ የራሱ ዋጋ አለው። በተለይ በዚህ ለሙስሊም ዳያስፖራዎች ጥሪ እየተደረገ ባለበት ሰዓት ይሄ ነውረኛ ተግባር መፈፀሙ ተጨማሪ ንቀትን ማሳያ እንደሆነ ማጋለጥ ይገባል።
ነገር ግን ጩኸቱ ትርጉም የሚኖረው መሬት ላይ ያለውን ስራ መስራት የሚችል ጠንካራ አካል ሲኖር ነው። ከዚህ በፊት ለረጅም ዘመናት በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች የመጅሊስ ተወካዮች፣ ሙስሊም መምህራን እና በርካታ የተማሪ ወላጆች ለአንዳንድ ነውረኛ ፀረ ኢስላም ኃላፊዎች ጫና እየተንበረከኩ የሙስሊም ተማሪዎችን ጥያቄ ለሚያዳፍኑ አካላት አጋር ሲሆኑ ቆይተዋል። ይሄ ሊታረም ይገባል። "እኛ ተማሩ እንጂ ስገዱ ብለን አልላክናቸውም" ብለው ዱላ አቀብለው የተመለሱ ወላጆች፣ የመጅሊስ ሰዎች እና የመስጂድ ኮሚቴዎችን አውቃለሁ። በሌላ በኩል "እኔምኮ ሙስሊም ነኝ" እያለ ተልእኮ ተቀብለው የተማሪዎችን የመብት ጥያቄ ሲያስናክሉ የነበሩ መምህራን ቀላል አይደሉም። ይሄ ህሊና ቢስ የሆነ አካል የሚፈፅመው አሳፋሪ ተግባር ነው።
በነገራችን ላይ ይሄ በትምህርት ተቋማት ውስጥ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚደርሰው እንግልት እንዳጠቃላይ ሙስሊሙ ህብረተሰብ ላይ ለሚደርሱ ጭቅናና በደሎች አንድ ማሳያ ነው። ከዚህ በተጨማሪ ውጤት ማበላሸትን ጨምሮ ሌሎች ብዙ አይነት በደሎች አሉ። ጨርሰው ሲውጡም በቅጥርና ምደባ ላይ ብዙ አሻጥር አለ። አንድ ሙስሊም ተማሪ በትምህርቱ ስኬት ላይ ለመድረስ ከሌሎች በተለየ ብዙ አይነት መሰናክሎችን ማለፍ ይጠበቅበታል፡፡
በሌሎችም ሴክተሮች እንዲሁ ብዙ ግፍ አለ። በተለይ ፊታቸውን በሸፈኑ ሙስሊም ሴቶች ላይ የሚኖረው በደልና ጫና ከሌሎችም ይጨምራል። መታወቂያ ለማውጣት፣ ባንክ ቤት፣ ፍተሻ ቦታዎች፣ ሃኪም ቤቶች ፣ ... ሌሎችን የማይጠይቁትን ጥያቄ እየጠየቁ አቃቂር ሲያወጡ ያጋጥማሉ።
ሁሉን እንዳመጣጡ ማስተናገድ እንዳለ ሆኖ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ጠንክሮ መማርና ማስተማር ይገባል። ችግሩ የሚፈታበትን ሰበብ በሩን ከርችመን ዘግተን በሚደርሱት በደሎች መነፋረቅ ይበልጥ እራስን ማስናቅ ነው። ስለዚህ በመማር ማስተማሩ ላይ ርብርብ ሊኖር ይገባል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
http://t.me//IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
دروس وفوائد ابن منور
1000
"ከዐርሹ በላይ" መፅሀፍ ገበያ ላይ ወጥቷል። አልሐምዱ ሊላህ ቢኒዕመቲሂ ተቲሙ ሷሊሓት።
መገኛ፦ አተውባ መክተባ (አንዋር መስጂድ አጠገብ)
=
https://t.me/IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
دروس وفوائد ابن منور
2700
ቃል እና ተግባር
~
ዙበይድ ብኑል ሓሪሥ አልያሚ ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፦
"አንዲት የኢብኑ መስዑድ ንግግር ሃያ አመት ዝም አሰኝታኛለች፤ 'ንግግሩ ከተግባሩ ጋር የማይገጥም ሰው እራሱን ነው የሚኮንነው' የምትለዋ።" [ዑዩኑል አኽባር ፡ 1/ 204]
=
https://t.me/IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
دروس وفوائد ابن منور
1600
ሰበር ዜና
አስደሳች ዜና እንኳን ደስ አለቹ
ልጆች በአላህ ፍቃድ ተገኝቶዋል
NB: ወላጆች! እባካችሁ ስለምትቀጥሯቸው የቤት ሠራተኞችና ጥበቃዎች የተጣራ መረጃና አስተማማኝ ተያዥ ይኑራችሁ።
2110
አፋልጉን‼
=========
✍ ወለቴ አከባቢ ይህች ሱሴ አጃማ የተባለች የቤት ሠራተኛ የ4 አመት ልጅ እና 11 ወር ህጻን ልጅ ሰርቃ ይዛ ጠፍታለች። በመታወቂያዋ ማግኘት አልተቻለም። ሰራተኛዋ አንድ እግሯ ያነክሳል። ልጆቹ ትልቋ ሴት ትንሹ ወንድ ነዉ።
የትኛውም አይነት መረጃ ያላችሁ ሁሉ በአካባቢያችሁ ወደሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ በማመልከት፤ 0913329208
እና 0975298575 ብትደውሉልን ወረታ ከፋይ ነን። ለአላህ ብለችሁ ሼር አድርጉልን።
ፈላጊ ቤተሰቦቿ!
NB: ወላጆች! እባካችሁ ስለምትቀጥሯቸው የቤት ሠራተኞችና ጥበቃዎች የተጣራ መረጃና አስተማማኝ ተያዥ ይኑራችሁ።
||
t.me/HalalDigitalNetwork
2700
#አይሰጥም_ልቦና__!!
---------------------------------
በአባቶች አደራ በቀደምቶች ምክር፡
ሁላችን በአንድነት አንድ ሀቅ እንዘክር፡
ከቃል የዘለለ በተግባር እንመስክር፡
ቆራርጠን እንጣለው የሽርክን ትብትብ ክር፡
⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
የሸይጧንን ወጥመድ የሸረሪቱን ድር፡
በሱና እናፍርሰው የቢዲዓን ድድር፡
በሀቅ አንቀልድ ይቅርብን ድርድር፡
⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ቆርጠን እንነሳ እንጠንክር እንፅና፡
በነብያት ፈለግ በተውሒድ በሱና፡
የቀደምት አባቶች አደራ ሰጥተዋል፡
የኢስላምን መልዕክት ለኛ አበርክተዋል፡
ብዙ ጭቆናና ብዙ ግፍ ችለዋል፡
ደማቅ አኩሪ ጀብዱ ውብ ታሪክ ሰርተዋል፡
⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከስህተታችን ቆርጠን እንመለስ፡
ከባጢል ተሰደን ወደ ሀቅ እንፍለስ፡
በሱና ክልል ውስጥ እንበል መለስ ቀለስ፡
⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ለልጅ ያስረከቡት የአባቶች አደራ፡
ዘውታሪ የሆነ ከዱንያ እስከ አኸይራ፡
እኛም በምክራቸው ጠንክረን እንፅና፡
አባት ምክር እንጅ አይሰጥም ልቦና፡
⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
#ኑረዲን_አል_አረቢ(2014)
-------------------------------------------
https://t.me/nuredinal_arebi
https://t.me/nuredinal_arebi
5000
Оберіть інший тариф
На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.