cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

...Poet, writer & film maker🎬🎥

Більше
Ефіопія5 741Амхарська4 274Книги7 392
Рекламні дописи
2 823
Підписники
+124 години
-27 днів
+330 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Фото недоступнеДивитись в Telegram
አመሰግናለሁ!
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
Показати все...
[በስቅለት ቀን ያጋጠመኝ አስገራሚ ክስተት] : መስገጃ ቦታ እንዳላጣ ብዬ በግዜ ብሄድም አልተሳካልኝም ነበር! የቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ በሰው ተሞልቶ ጠበቀኝ! ምንጣፌን ይዤ በአይኔ ክፍት ቦታ ስቃኝ ያየኝ አንድ አስተባባሪ "ና ቦታ ልስጥህ" ብሎ ወደ አንድ ቦታ መራኝና "እዚህ ጋ ተቀመጥ" ብሎ በእጁ ጠቆመኝ! ልጁን አመስግኜ ምንጣፌን አንጠፍሁና የአቅሜን ከሰገድሁ በኋላ ትንሽ ረፍት ለመውሰድ ተቀመጥሁ! ድንገት አንዲት ሴት አጠገቤ መጥታ ቆመች!ዕድሜዋ በሀያዎቹ አጋማሽ ላይ ነው!...በእጇ መስገጃ የሚሆናት ምንጣፍም ሆነ ምንም ነገር አልያዘችም!..ያደረገችውን ክፍት ጫማ አወለቀችና ጠጠሩ ላይ መስገድ ጀመረች!...የያዝኩት ምንጣፍ ሰፊ በመሆኑ ምንጣፉ ላይ ሆና እንድትሰግድ ነገርኳት!.."እሺ" ብላ አመስግናኝ ወደ ምንጣፉ ተጠጋች!...ፊቷን አየሁት!...ጉንጮቿ ደም መስለዋል..ሁለቱም አይኖቿ በዕንባ ብዛት በሚመስል መልኩ ቀልተዋል!...ደነገጥኩ!..."ምን ሆነሽ ነው?" ብዬ ልጠይቃት አልኩና "እኔ ማነኝ?" ብዬ መልሼ ተውኩት!...ተነሳሁና መስገድ ጀመርኩ!...ጎን ለጎን ሆነን መስገድ ጀመርን!...ብዙ ከሰገድኩ በኋላ ደከመኝና ተቀመጥሁ!...ልጅቷ ከገባች ጀምሮ አላረፈችም!...እየሰገደች ነው!...ድንገት ጎንበስ ስትል ዕንባዋ ምንጣፉ ላይ ጠብ ሲል ተመለከትሁ!...ድጋሚ ዝም ማለት አልቻልኩም!...እጇን ያዝ አደረኳትና "እህቴ እስቲ ትንሽ አረፍ በይ" አልኳት ዕንባዋን በነጠላዋ ጫፍ ጠራረገችና ተቀመጠች!..."ምን ሆነሽ ነው የኔ እህት...ምን ሆነሽ ነው ምታለቅሺው?" አልኳት!...ስጠይቃት ይበልጥ አለቀሰች!..."ማንም ምን ሆነሽ ነው ብሎ ጠይቆኝ አያውቅም እኮ" አለችኝ!..."እንዴት"? አልኳት...ረጅም አመት የምታውቀኝ ያህል አወራችልኝ!...ከእናቷ በቀር ምድር ላይ ማንም ዘመድ እንደ ሌላት አወራችልኝ!...እናቷ በጣም ሀብታም እንደ ነበረች አወራችልኝ!...እናቷ ከ 5 ወር በፊት እንደ ሞተች አወራችልኝ!...እናቷ ስትሞት የመኖር ትርጉም እንደ ጠፋትና ሱስ ውስጥ እንደ ተዘፈቀች አወራችልኝ!...በዕንባ ብዙ ብዙ ነገር አወራችልኝ!...ላቋርጣት አልፈለግሁም!...ዝም ብዬ ሰማኋት!...መጨረሻ ላይ ዕንባዋን ጠራረገችና ፈገግ ብላ..."ታውቃለህ" አለችኝ..."ታውቃለህ እናቴ ከሞተች በኋላ መጀመሪያ ግዜዬ ነው ቤተክርስቲያን ስመጣ!...በእርግጥ የመጨረሻዬም ነው!...የመጨረሻዬ ስግደትም ስለሆነ ነው ያለማቋረጥ ስሰግድ የነበረው ምን አልባት ቢምረኝ ብዬ!"...ብላ ትንሽ ዝም አለችና!..."ይቅርታ በማያገባህ ብዙ ጨቀጨኩህ!...አመሰግናለሁ ቻው በቃ" ብላኝ ተነስታ ሄደች!...ከሄደች በኋላ ስታወራቸው የነበረችው ነገሮች አይምሮዬ ላይ ማቃጨል ጀመሩ... "ታውቃለህ እናቴ ከሞተች በኋላ መጀመሪያ ግዜዬ ነው ቤተክርስቲያን ስመጣ!...በእርግጥ የመጨረሻዬም ነው" "የመጨረሻዬ ስግደትም ስለሆነ ነው ያለማቋረጥ ስሰግድ የነበረው.... ምን አልባት ቢምረኝ ብዬ!" በድንጋጤ ከተቀመጥሁበት ተነሳሁ!...ከህዝብ መሀል በአይኔ ፈለኳት...በሩ አከባቢ ስትወጣ ተመለከትኩ...ጫማዬን እንኳ ሳላደርግ በፍጥነት ሄድኩ! : : የመኪናዋን በር ከፍታ ልትገባ ስትል ደረስኩባት!...እጇን ይዤ አስቆምኳት...ወደ ኋላ ዞራ አየችኝ... "እራስሽን ልታጠፊ ነው አይደል?" አልኳት! ምንም ሳትናገር እጇን አስለቀቀችና መኪናዋ ውስጥ ገባች...ምንም ብናገር...ምንም ባወራ በዚህ ስሜት ሆና ማድረግ ከፈለገችው ነገር እንደማትመለስ አውቃለሁ...ብቻ ግን እግዚአብሔር አንደበቴ ላይ ቃላቶችን አስቀመጠ.. "እግዚአብሔር ከ እናትም ከ አባትም በላይ እንደ ሆነ አታውቂም?...ተስፋን የሰጠን የታመነ እንደሆነ አታውቂም?....ክርስቶስ ተሰቅሎ አለምን ባዳነበት ዕለት አንቺ ትሞቻለሽ?"...አልኳት!....ተንሰቅስቃ አለቀሰች! : : መርሀ ግብሩ ካለቀ በኋላ ከማውቃቸው ደግ እማሆይ ጋ አገናኘኋት!...ፀለዩላት!...አረጋጓት!...እንደ እናት አቀፏት!...አባበሏት!..አይዞሽ አሏት!... ዲያቢሎስ አስቦባት የነበረውን የሞትን ደብዳቤ ክርስቶስ ኢየሱስ በስቅለቱ ዕለት ሰቀለው!....ስሟን ጠየኳት!...ሩት አለችኝ.... : ሩት!....በእግዚአብሔር ምህረት ከሞት እና ከዘላለማዊ እሳት ያመለጠች ነፍስ! [እዮብ ዘ ማርያም] Join @poeteyobzmariam @poeteyobzmariam @poeteyobzmariam
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ሰላም facebook የምትጠቀሙ ወዳጆቼ! ከስር የማስቀምጥላችሁ link የስነፅሁፍ ውድድር እየተካሄደበት ያለበት page ነው!...comment ላይ እየገባችሁ eyob z mariam በሚል pofile የተፃፈውን "ናተይ" የሚል አጭር ልቦለድ like እንድታደርጉ ጠይቃለሁ...አመሰግናለሁ🙏 link 👇 https://www.facebook.com/share/p/VX6SuiXZcyYYBnmY/?mibextid=oFDknk link አልሰራ ካላችሁ @ሙስተጃብ ነኝ በሚል የፌስቡክ ስም ታገኙታላችሁ!
Показати все...
አይመስለኝም ነበር የምንረሳሳ አይመስለኝም ነበር... ልብሽና ልቤ በወረት ሚበሳ ሁሉም ከንቱ ቀረ ተረሳሳን በቃ የዘመናት ፍቅር ጠፋ በደቂቃ እኔም ዘነጋሁሽ አንቺም ዘነጋሺኝ በሌላ ተካሁሽ በሌላ ተካሺኝ ያ ሁሉ መገዘት ያ ሁሉ መሀላ ያ ሁሉ ቃል ማብዛት ሁሉ ሽንገላ በቃ ለዚሁ ነበር? ልብሽ ሊኮበልል እኔም ላቅፍ ሌላ? የሚያስቀናው ፍቅር... ሲታይ የሚመስለው ማይገኝለት አቻ እዚህ ጋ ተቋጨ ሳይደርስ ዳርቻ የኔና አንቺ ነገር ያሳዝናል ብቻ! [Eyob  Z Mariam] @poeteyobzmariam @poeteyobzmariam @poeteyobzmariam
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
እንኳንም ኖርሺኝ🖤 join @poeteyobzmariam @poeteyobzmariam @poeteyobzmariam
Показати все...
(እንዲህ ናት የኔ ሴት) ጾሜን አስገድፋ፣ አንጀቴን ስትበላ እሮብ አርብ የማትል ሆዴን ምታላውስ ገብታ ልክ እንደ ትል ቀጥ የምታደርገኝ... ጉንጩን ዳበስ አርጋ "ወድሀለሁ" ስትል! እንዲህ ናት የኔ ሴት... ሀዘን ቅስሜን ሰብሮ ለፀፀት ሲሰጠኝ መሰንበት ጠልቼ ትካዜ ሲንጠኝ ፀጉሬን ደባብሳ... የመኖርን ተስፋ ዳግም ምትሰጠኝ! እንዲህ ናት የኔ ሴት... በጠመመ ግዜ ጨርቄን ጥዬ ባብድም የማደርገው ጠፍቶኝ በራሴ ላይ ባድም መሰልቸት ደባብሷት፣ ትታኝ የማትሄድ አብራኝ ምትወድም! እንዲህ ናት የኔ ሴት... በማላቀው ጥፋት በስሜ ቢነገድ ሊያጠፋኝ ቢነሳ አንድ ሙሉ ነገድ ፈፅሞ ማትከዳኝ... በሄድኩበት ሁሉ አብራኝ ምትሰደድ! እንዲህ ናት የኔ ሴት..!! እቴ የኔ አበባ፣ ዘመድ አዝማዶቼ መኖሬን ሳይሰሙት ጠላቶቼ ሁሉ... የኔን ደስታ ማግኘት ጭራሽ ሳይተልሙት ፍቀጂልኝና፣ ካንቺ ጋራ ኖሬ ካንቺ ጋራ ልሙት! (እዮብ ዘ ማርያም) join @poeteyobzmariam @poeteyobzmariam
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.