cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

አዲስ ነገር መረጃ

አዲስ ነገር መረጃዎች መረጃዎች በትኩሱ ና ሳይዉሉ እንዲሁም ሳያድሩ በቻናሉ በኩል ይደርሳሉ ለአስተያየት እና ለማስታወቂያ ስራዎች 👇👇 @Addisnegermereja_bot

Більше
Рекламні дописи
76 191
Підписники
-1924 години
-1297 днів
-51430 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

ቻይና 60 አውሮፕላኖችን የሚይዝ የጦር መርከብን ስራ አስጀመረች፡፡ ላለፉት ሁለት ዓመታት ደግሞ በሚከራ ላይ ነበረች ተብሏል የዓለማችን ሁለተኛዋ ልዕለ ሀያል ሀገር ቻይና የባህር ሀይሏን የሚያዘምን ዘመናዊ የጦር መርከብ ይፋ አድርጋለች፡፡ ፉጂያን የሚል ስያሜ የተሰጣት ይህች የጦር መርከብ በአንድ ጊዜ 60 አውሮፕላኖችን የመያዝ አቅም እንዳለውም ተገልጿል፡፡ 80 ሺህ ቶን ክብደት ያላት ይህች መርከብ ላለፉት ስድስት ዓመታት በግንባታ ላይ የቆየች ሲሆን ከፈረንጆቹ 2022 ጀምሮ ደግሞ የባህር ላይ ሙከራ ስታደርግ እንደቆየች ሽንዋ ዘግቧል፡፡ ቻይና 66 ሺህ እና 60 ሺህ ቶን የመጫን አቅም ያላቸው ሻንዶንግ እና ሊያውኒንግ የተሰኙ ሁለት የጦር መርከቦች ያላት ሲሆን ሶስተኛውን እና ዘመናዊው ጦር መርከብ ባለቤት ሆናለች፡፡ አዲሷ ፉጂያን የጦር መርከብ ኤሌክትሮ ማግኔቲክ ሲስተም የተገጠመላት ሲሆን ከፍተኛ እና ክብደት ያላቸውን ጦር አውሮፕላኖች እንዲነሱ እና እንዲያርፉ ማድረግ ያስችላልም ተብሏል፡፡ የጦር መርከቧ በደቡባዊ ቻይና ባህር በኩል በአሜሪካ፣ ፊሊፒንስ እና ቬትናም በኩል ሊነሱ ለሚችሉ ተጽዕኖዎች እና ሌሎች ጥቃቶችን ለመከታተል እና ምላሽ ለመስጠት እንደሚያስችላት አል አይን በዘገባው አመልክቷል፡፡ @Addis_News
Показати все...
ሰበር የእስር ዜና ! በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24/2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸው ታውቋል። የሁለቱ አገልጋዮች መኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል። በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የሚገኙ ሲሆን የተያዙበት ምክንያት አልታወቀም። Via: ማህበረ ቅዱሳን @Addis_News
Показати все...
👍 15🤔 11
በትግራይ ክልል የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች የ17 ወር ውዝፍ ደሞዝ እስካሁን አልተከፈላቸውም ተባለ፡፡ በክልሉ የሚገኙ ሁሉም የጤና ባለሙያዎች የ17 ወር ደሞዝ ሳይከፈላቸው በመቆየቱ ከቤት ኪራይ ጀምሮ በተለያዮ ወጪዎች በእዳ ተይዘው እንደሚገኙ የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ አስታውቋል፡፡ የክልሉ ጤና ቢሮ የፈውስና ተሃድሶ ዋና የስራ ሂደት ተተኪ ዶክተር ስምኦን ገብረጻዲቅ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት ባለሙያዎቹ ለመኖር ሲሉ ለሚያስፈልጋቸው ወጪ በብድር ሲጠቀሙ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡ ይህም የጤና ባለሙያዎቹ አገልግሎት ለመስጠት ችግር እንደሆነባቸው ጠቅሰዋል፡፡ ሌላው ከጣቢያችን ጋር ቆይታ የነበራቸው የአይደር አጠቃላይ ሪፈራል ሆስፒታል ዳይሬክተር ዶ/ር አብርሃ ገ/እግዚአብሔር እንዳሉት ውዝፍ የ22 ወር የትርፍ ሰአት ክፍያም እስካሁን እንዳልተከፋላቸው አንስተዋል፡፡ ችግሩን የክልሉም ሆነ የፌደራሉ መንግስት ቢያቁም እስካሁን ምላሽ አልተሰጠንም ብለዋል፡፡ @Addis_News
Показати все...
👍 6
የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፈተና መቼ ይሰጣል ? እንደ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ፤ የ2016 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል። ፈተናው ለ15 ቀናት በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ለመስጠት እየተሠራ ነው። ከ70 በመቶ የሚዘጋጀው ፈተና በኦንላይንና በወረቀት ወይም በጥብቅ ቁጥጥር በወረቀት ይሰጣል ተብሏል። ባለፈው ዓመት የተፈጠረውን ችግር ለመቅረፍ የሪሚዲያል ፈተናውን በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራበት ነው። ዘንድሮ 32,500 ተማሪዎች 50 በመቶ በላይ ውጤት በማምጣት በቀጥታ ዩኒቨርሲቲ ገብተው መደበኛ ትምህርት እየተከታተሉ ሲሆን ከ78 ሺህ በላይ ተማሪዎች ደግሞ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ሪሚዲያል ትምህርት እየወሰዱ እንደሚገኙ ሚኒስቴሩ ለኢፕድ ከሰጠው መረጃ ተመልክተናል። በሌላ በኩል ፤ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደቡ የሬሜዲያ ተማሪዎች ከታህሳስ ወር ጀምሮ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ቢሆንም በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የተመደቡ ተማሪዎች እስካሁን ጥሪ አልተደረገላቸውም። @Addis_News
Показати все...
በጃፓን ሰው የማይኖርባቸው ቤቶች ብዛት ዘጠኝ ሚሊዮን ደርሷል የጃፓን መንግሥት ያወጣው የቅርብ ጊዜ አኃዛዊ መረጃዎች፣ በሀገሪቱ ሰው የማይኖርባቸው የባዶ ቤቶች ብዛት ዘጠኝ ሚሊዮን መድረሱ አለምን ጉድ እያሰኘ ነው። በጃፓን ሰው የማይኖርባቸው ወና ቤቶች ብዛት በሀገሪቱ ውስጥ ካሉት ቤቶች ውስጥ 13.8 ከመቶ ድርሻ እንዳላቸው ለማወቅ ተችሏል። በሀገሪቱ ለባዶ ቤቶች መብዛት ዋነኛ ምክንያት ተብለው ከተቀመጡት መካከል የወሊድ መጠን መቀነስና በገጠር የሚኖረው ህዝብ መመናመን ናቸው። ከሁሉም በላይ፣ ሰው ከማይኖርባቸው ዘጠኝ ሚሊዮን ቤቶች ውስጥ ከአንድ ሦስተኛ በላይ ወይም 3.85 ሚሊዮን የሚሆኑት ቤቶች በቀጥታ የተተዉ ናቸው ሲል የሀገር ውስጥ ጉዳይ እና ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስቴር ያወጣው የዳሰሳ ጥናት ውጤት ያሳያል። የህዝብ ቁጥር እየቀነሰ የሚሄድባቸው የገጠር ቀበሌዎች ባዶ ወይም የተተዉ ቤቶችን ብዛትን መገኛ በመሆን ይመራሉ። ዋካያማ እና ቶኩሺማ አውራጃዎች በ21.2 በመቶ በላይ ባዶ ቤቶች የሚገኙባቸው ቦታዎች ናቸው። ሌላው ደግሞ የጃፓን የግብር ህግ ለባዶ ቤቶች መስፋፋት አስተዋጽኦ አድርጓል በማለት ወቀሳ እየቀረበበት ነው። ምክንያቱም በጃፓን ህንፃዎች ካረፉበት መሬት ይልቅ ቤት ያላረፈበት ባዶ መሬት የበለጠ ቀረጥ ይስባል ይባላል፣ ይህም ሰዎች ያረጁ ቤቶችን ከማፍረስ እንዲቆጠቡ አድርጓል በሚል ይጠቀሳል። Via:Infraethiopia @Addis_News
Показати все...
👍 12🔥 2
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የጸሎተ ሐሙስ ሥነ ስርዓት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል። @Addis_News
Показати все...
ደንበኞች ከትንሳኤ በዓል ዋዜማ ጀምሮ ኃይል ቆጣቢ አጠቃቀምን ተግባራዊ እንዲያደርጉ አገልግሎቱ ጠየቀ በትንሳኤ በዓል ዋዜማና ዕለት የኃይል መዋዥቅና መቆራረጥ ለመቀነስ፤ ከተከሰተም አፋጣኝ ምላሽ ለመሰጠት የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያጠናቀቀ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። እንዲያም ሆኖ ሊያጋጥም የሚችለውን የኃይል መዋዠቅና መቋረጥ ለመቀነስ በውጭ ንግድ ላይ ከተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች በስተቀር ሌሎች ሁሉም የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ከዋዜማው ከቀን 7 ሰዓት ጀምሮ እስከ በዓሉ ዕለት ድረስ ከዋናው ግሪድ የሚጠቀሙትን ኤሌክትሪክ እንዲያቋርጡ አገልግሎቱ ጥሪ አቅርቧል። ደንበኞች በቤት ውስጥ የሚገለገሉባቸው የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶች ኃይል ቆጣቢና ለአደጋ የማያጋልጡ መሆናቸውን እንዲያረጋግጡ እና የኤሌክትሪክ ኃይል ጭነት በማይበዛበት ሰዓት በተለይ ከምሽቱ 4፡00 እስከ ንጋቱ 11፡00 ባሉት ጊዜያት እንዲጠቀሙ ጠይቋል። የቅድመ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ደግሞ በዓሉ ሲደርስ የሚኖረውን አላስፈላጊ ወረፋ ለማስቀረት እንዲችሉ ከወዲሁ የሚበቃቸውን ያህል የኤሌክትሪክ ኃይል አስቀድመው እንዲገዙ (ካርድ እንዲሞሉ) አገልግሎቱ መክሯል። @Addis_News
Показати все...
👍 5
በገበታ ለሀገር የተገነቡ ሎጆችን የማስተዳደር ኃላፊነቱ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ተሠጠ። በገበታ ለሀገር የተገነቡ ሎጆችን ስራ የማስኬድ ተግባርን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በስካይ ላይት ሆቴል ተቋሙ በኩል እንዲወጣ ዛሬ የስምምነት ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል። ስምምነቱ በቅርቡ የተመረቁትን ሃላላ ኬላ ሎጅ፣ ጨበራ ጩርጩራ የዝሆን ዳና ሎጅ እና ወንጪ ኢኮ ሎጅ እና በመጠናቀቅ ላይ ያለውን የጎርጎራ ፕሮጀክትንም ያካትታል። "ቀጣይ የስራ ማስኬድ እና ማስተዳደር ተግባሩ ለብሔራዊ ሰንደቅ ተሸካሚው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሃላፊነት መሰጠቱም የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ ከማስቻሉም ባለፈ ለአለምአቀፍ የቱሪዝም መዳረሻነት ትውውቅ ከፍ ያለ ዕድል ይፈጥራል።" ሲል የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት አስታውቋል። @Addis_News
Показати все...
በቴክሳስ ዩኒቨርሲቲ ዳላስ ቢያንስ 20 የፍልስጥኤም ደጋፊዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ ቢያንስ 20 የፍልስጤም ድምፅ በማሰማት የሚቃወሙ ሰዎች በቴክሳስ ዩኒቨርስቲ በዳላስ ካምፓስ የጋዛ ህብረት ካምፕ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአካባቢው ፖሊስ ገልጿል።  ረቡዕ ጠዋት ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ድንኳኖችን በመትከል እንኳን ወደ ጋዛ ነፃነት ስፍራ በሰላም መጡ ሲሉ መልዕክት አጋርተዋል። ረቡዕ ከሰአት በኋላ ፖሊስ ካምፑን ሲያፈርስና ተቃዋሚዎችን በቁጥጥር ስር ሲያውል ታይቷል። ከሰልፈኞቹ መካከል ምን ያህሉ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች እንደሆኑ ግልጽ አይደለም። ፍልስጤምን የሚደግፉ ዋና ዋና ሰልፎች በአሜሪካ የኮሌጅ ካምፓሶች ተሰራጭተዋል፣ በኦስቲን የሚገኘው የቴክሳስ ዩኒቨርሲቲ በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች በተመሳሳይ በቁጥጥር ስር አውሏል።ፍልስጤማውያን በዩናይትድ ስቴትስ በሚገኙ የዩንቨርስቲው ካምፓሶች ፀረ-ጦርነት ሰልፎችን ላደረጉ ተቃዋሚዎች ምስጋናቸውን ለመግለጽ በጋዛ ጎዳናዎች ላይ ወጥተዋል። በማዕከላዊ ጋዛ ዲየር ኤል ባላህ በስደተኛ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ሰዎች በአሜሪካ ኮሌጆች ተቃዋሚዎችን የሚያመሰግኑ ምልክቶችን ይዘው ወጥተዋል። ሰልፎቹ ጦርነቱ እንዲቆም በዩንቨርስቲው አስተዳደሮች፣በ አሜሪካ መንግስት እና በአለም አቀፉ ማህበረሰብ ላይ ጫና እንደሚፈጥር ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል። በሌላ በኩል በዮርዳኖስ መንግስት ስር የሚተዳደረው ፔትራ የዜና ወኪል እንደዘገበው ሁለት የዮርዳኖስ የእርዳታ ልዑካን ምግብ፣ ዱቄት እና ሰብአዊ ርዳታዎችን የያዙ ምርቶችን ሲያጓጉዙ በእስራኤል ሰፋሪዎች ጥቃት እንደደረሰባቸው ዘግቧል። @Addis_News
Показати все...
👍 5
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ አየር መንገዱ ካለፈው ዓመት አንጻር በተያዘው ዓመት የመንገደኞቹ ብዛት በ30 በመቶ ይጨምራል ብለው እንደሚጠብቁ መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል። ባለፈው ዓመት የአየር መንገዱ መንገደኞች ብዛት 13 ነጥብ 9 ሚሊዮን ነበር። የአየር መንገዱ መንገደኞች ብዛት ዘንድሮ የሚጨምረው፣ አየር መንገዱ መዳረሻዎቹን በማስፋቱና በዓለም ላይ የአየር ትራንስፖርት በማንሠራራቱ እንደኾነ ተገልጧል። ኾኖም አየር መንገዱ ያዘዛቸው አዳዲስ አውሮፕላኖች መዘግየታቸውና በሞተር እጥረት የቆሙ አውሮፕላኖች መኖራቸው ችግር እንደኾኑበት መስፍን መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። አየር መንገዱ በዓመቱ በ20 በመቶ ጭማሪ 7 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን መስፍን ገልጸዋል ተብሏል። @Addis_News
Показати все...
👍 6