cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

የብዕር ቀለሞች

በዚህ ቻናል 👉 ግጥሞች 👉 አጭር ልቦለዶች 👉 አስቂኝና አስገራሚ ወጎች 👉 ድርሰቶች 👉 join በሉት ይደሰቱበታል @amharic_poet join በሉት ይደሰቱበታል more connection

Більше
Рекламні дописи
784
Підписники
+424 години
+67 днів
+3930 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Repost from N/a
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ጊዜ እና ቀጠሮ """"""""""""""""""""" እሷ ጠብቀኝ ካልኩበት መጥቼ አጣሁት ብላ ታወራለች እኔ ግን የማውቀው እመጣለሁ ብላኝ ሄዳ እንደቀረች የእኔና'ሷ ጉዞ በዚህ ነው ያበቃው መጥታ እያጣችኝ ጠብቄያት እያጣው ግን እኮ ነበርኩኝ ጠብቀኝ ካለችኝ ቦታ ሳልል ንቅንቅ ሰዓት ከቀን ገጥሞ ወር ከዓመት ትንቅንቅ ክረምት እና በጋው በላዬ እያለፈ ልቤ እሷን ጥበቃ እንደተደገፈ ምናልባት ምናልባት በላብ በቆሻሻ መልኬ ካላደፈ በመሰንበት ብዛት ጠጉሬ ካልረገፈ ስጠብቃት ነበር በየሄደችበት እንዲቀናት በለስ ጉዳይዋን ፈፅማ ቶሎ እንድትመለስ የፀለይኩት ፀሎት ለሷ ብቻ ደርሶ ባለችበት ደልቷት ዕድሜዋ ገስግሶ በድሎቷ መሀል አንድ ጊዜ መጥታ ለመቅረብ ባትደፈር ከሩቅ አይኔን አይታ ንፁህ መጠበቄን ላለማጉደል ፈርታ እያዘነች ሄዳ እያነባች ሸሽታ ካልሆነ በስተቀር ቀጥራኝስ ካልቀረች አርፍዳ ነው ሚሆን ዘመን ቀይሮናል ብትመጣም አላውቃት እውን መጥታስ ቢሆን እሷ ጠብቀኝ ካልኩበት መጥቼ አጣሁት ብላ ታወራለች እኔ ግን የማውቀው እመጣለሁ ብላኝ ሄዳ እንደቀረች ልክ ናት በሷ ዓለም አርፍዳ ይሆናል ቀርታ ግን አይደለም ልክ ነኝ በኔ ዓለም ትመጣለች ሳልል ያለፈኝ ቀን የለም እድል ይሁን ዕጣ ወይ የአምላክ ውሳኔ አርቆ ያስቀረን ቀንሽ ወይስ ቀኔ የትኛው ይረገም የትኛው ይወንጀል አለሁ ስጠብቅሽ መጥተሽ ነው ያጣሽኝ የለብሽም በደል ሆነና ያንዳንዴ ያጋጣሚ ነገር እኔም አለኝ እውነት አንቺም አለሽ እውነት ለሀቅ የሚነገር ባድባር በሰፈሩ ለወጪ ወራጁ ለተራማጅ ቋሚው እስከምሆን ድረስ ምልክት ጠቋሚው ፀሀይ ከጨለማ ምሽት እና ቀኑ ለሚጠብቅ ገላ አንድ እንደሚሆኑ ያልገባቸው ሁሉ መሸ ነጋ ቢሉ በምስራቋ በኩል አንቺ እስከምትወጪ ከጨረቃዋ ጋ        አብረሽ ሳትመጪ ፅልመት ቢሆን ብርሀን ቀኑ ምን ትርፍ አለው ከትዝታ ውጪ እሷ ጠብቀኝ ካልኩበት መጥቼ አጣሁት ብላ ታወራለች እኔ ግን የማውቀው እመጣለሁ ብላኝ ሄዳ እንደቀረች ወይ በሄደችበት ከፀለይኩት ፀሎት አንዱም ሳይሳካ መንገዷ ተሞልቶ በእንቅፋት በሳንካ ብክንክን እንዳለች አንድ ነገር ሆና ወድቃ ቀርታስ ቢሆን ከአንዱ ጎዳና ቢሆንስ ቢሆንስ ቀጥራኝስ ካልቀረች አርፍዳ ነው ሚሆን ዘመን ቀይሮናል ብትመጣም አላውቃት እውን መጥታስ ቢሆን ። በረከት_ዘውዱ @yegtm_hywet @amharic_poet @poem_profile
Показати все...
5
እሷ ጠብቀኝ ካልኩበት መጥቼ አጣሁት ብላ ታወራለች እኔ ግን የማውቀው እመጣለሁ ብላኝ ሄዳ እንደቀረች የእኔና'ሷ ጉዞ በዚህ ነው ያበቃው መጥታ እያጣችኝ ጠብቄያት እያጣው ግን እኮ ነበርኩኝ ጠብቀኝ ካለችኝ ቦታ ሳልል ንቅንቅ ሰዓት ከቀን ገጥሞ ወር ከዓመት ትንቅንቅ ክረምት እና በጋው በላዬ እያለፈ ልቤ እሷን ጥበቃ እንደተደገፈ ምናልባት ምናልባት በላብ በቆሻሻ መልኬ ካላደፈ በመሰንበት ብዛት ጠጉሬ ካልረገፈ ስጠብቃት ነበር በየሄደችበት እንዲቀናት በለስ ጉዳይዋን ፈፅማ ቶሎ እንድትመለስ የፀለይኩት ፀሎት ለሷ ብቻ ደርሶ ባለችበት ደልቷት ዕድሜዋ ገስግሶ በድሎቷ መሀል አንድ ጊዜ መጥታ ለመቅረብ ባትደፈር ከሩቅ አይኔን አይታ ንፁህ መጠበቄን ላለማጉደል ፈርታ እያዘነች ሄዳ እያነባች ሸሽታ ካልሆነ በስተቀር ቀጥራኝስ ካልቀረች አርፍዳ ነው ሚሆን ዘመን ቀይሮናል ብትመጣም አላውቃት እውን መጥታስ ቢሆን እሷ ጠብቀኝ ካልኩበት መጥቼ አጣሁት ብላ ታወራለች እኔ ግን የማውቀው እመጣለሁ ብላኝ ሄዳ እንደቀረች ልክ ናት በሷ ዓለም አርፍዳ ይሆናል ቀርታ ግን አይደለም ልክ ነኝ በኔ ዓለም ትመጣለች ሳልል ያለፈኝ ቀን የለም እድል ይሁን ዕጣ ወይ የአምላክ ውሳኔ አርቆ ያስቀረን ቀንሽ ወይስ ቀኔ የትኛው ይረገም የትኛው ይወንጀል አለሁ ስጠብቅሽ መጥተሽ ነው ያጣሽኝ የለብሽም በደል ሆነና ያንዳንዴ ያጋጣሚ ነገር እኔም አለኝ እውነት አንቺም አለሽ እውነት ለሀቅ የሚነገር ባድባር በሰፈሩ ለወጪ ወራጁ ለተራማጅ ቋሚው እስከምሆን ድረስ ምልክት ጠቋሚው ፀሀይ ከጨለማ ምሽት እና ቀኑ ለሚጠብቅ ገላ አንድ እንደሚሆኑ ያልገባቸው ሁሉ መሸ ነጋ ቢሉ በምስራቋ በኩል አንቺ እስከምትወጪ ከጨረቃዋ ጋ        አብረሽ ሳትመጪ ፅልመት ቢሆን ብርሀን ቀኑ ምን ትርፍ አለው ከትዝታ ውጪ እሷ ጠብቀኝ ካልኩበት መጥቼ አጣሁት ብላ ታወራለች እኔ ግን የማውቀው እመጣለሁ ብላኝ ሄዳ እንደቀረች ወይ በሄደችበት ከፀለይኩት ፀሎት አንዱም ሳይሳካ መንገዷ ተሞልቶ በእንቅፋት በሳንካ ብክንክን እንዳለች አንድ ነገር ሆና ወድቃ ቀርታስ ቢሆን ከአንዱ ጎዳና ቢሆንስ ቢሆንስ ቀጥራኝስ ካልቀረች አርፍዳ ነው ሚሆን ዘመን ቀይሮናል ብትመጣም አላውቃት እውን መጥታስ ቢሆን ። በረከት_ዘውዱ @yegtm_hywet @amharic_poet @poem_profile
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
እኔ በቆሎ """""" """"""" ከገላው ጠጉር ከላዩ ልስልስ በነኩት ቀጥር ወደ ብዙነት የሚፈራርስ ማንነት አለኝ እንደ በቆሎ በአንድ አካሌ ዕልፍ ማንነት በውስጤ በቅሎ ተጫዋች ሲሉኝ የማልናገር ጀግና ነው ሲሉኝ የምደናበር አማኝ ነው ሲሉኝ የማውደለድል ደካማ ሲሉኝ የምነሳ ድል ጠጉር ገላዬን ሸፍኖት ጨርቄ ከታች ነው ሲሉኝ መሬት ርቄ ከላይ ነው ሲሉኝ ከስር ወድቄ እየተምታታ ሀጥያት ከፅድቄ አብሮ የሚወርድ እንባና ሳቄ እኔ በቆሎ ዕልፍ ማንነት በውስጤ በቅሎ ለነፍሴ መብል ቢያለብሰኝ ስጋ ነፍሴን በላሁት ምንም ሳልሰጋ ። #በረከት_ዘውዱ @amharic_poet @yegtm_hywet @poem_profile
Показати все...
👍 5 1
እኔና በቆሎ """""" """"""" ከገላው ጠጉር ከላዩ ልስልስ በነኩት ቀጥር ወደ ብዙነት የሚፈራርስ ማንነት አለኝ እንደ በቆሎ በአንድ አካሌ ዕልፍ ማንነት በውስጤ በቅሎ ተጫዋች ሲሉኝ የማልናገር ጀግና ነው ሲሉኝ የምደናበር አማኝ ነው ሲሉኝ የማውደለድል ደካማ ሲሉኝ የምነሳ ድል ጠጉር ገላዬን ሸፍኖት ጨርቄ ከታች ነው ሲሉኝ መሬት ርቄ ከላይ ነው ሲሉኝ ከስር ወድቄ እየተምታታ ሀጥያት ከፅድቄ አብሮ የሚወርድ እንባና ሳቄ እኔ በቆሎ ዕልፍ ማንነት በውስጤ በቅሎ ለነፍሴ መብል ቢያለብሰኝ ስጋ ነፍሴን በላሁት ምንም ሳልሰጋ ። #በረከት_ዘውዱ @amharic_poet @yegtm_hywet @poem_profile
Показати все...
ብቻ ስትስቅ ልያት ""'''''''' """""""" """"""" የደስታዋ ምክንያት ለመሆን ስሞክር ጭንቀቷ ላይ ቆሜ እምቢኝ ስል ልፎክር ዱካኳን ገርፌ ልሰደው እርቃኑን ሀዘኗን ደብድቤ ላሳጣው እርባኑን ስፈልግ አመሹሁ የደስታዋን ዓለም ሳቋን ለመመለስ ያልሞከርኩት የለም ጥርሷን ባየው ብዬ የጉንጮቿን ስርጉድ ከንጋት እስኪመሽ እያልኩኝ ሽር ጉድ ኧረ ጉድ ኧረ ጉድ ምን ያልሆንኩት አለ ያልዋልኩበት ቦታ የሷን ሳቅ ልሸምት ሸጥኩኝ የኔን ደስታ ብቻ ትሳቅልኝ ሲከፋት እንዳላይ የነጥብ ደመና እንደሌለው ሰማይ ፍክትክት እንዳለች ይቆጠር ዘመኑ ከአድማስ ይራቃት እንባና ሀዘኑ እንባዎቿን ስጠኝ ሀዘኗን ልጋራት መደሰቴ አይቀርም ፈገግ ብላ ሳያት #በረከት_ዘውዱ @Amharic_poet @Yegtm_hywet @Poem_profile
Показати все...
👍 4 3😢 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
🥰 3👍 1
ለመላው እስልምና እምነት ተከታይ እህት ወንድሞቻችን እናት አባቶቻችን እንኳን ለ 1445ኛው የ ኢድ አል አድሃ ( አረፋ ) በአል በሰላም አደረሳችሁ !!!! በዓሉን የፍቅር የደስታ የጤና የሰላም ያድርግልን መልካም በዓል !!!!! 💦💦💦Eid Mubarak 💦💦💦 @amharic_poet @amharic_poet @amharic_poet
Показати все...
👍 1
ለመላው እስልምና እምነት ተከታይ እህት ወንድሞቻችን እናት አባቶቻችን እንኳን ለ 1445ኛው የ ኢድ አል አድሃ ( አረፋ ) በአል በሰላም አደረሳችሁ !!!! በዓሉ የፍቅር የደስታ የጤና የሰላም ያድርግልን መልካም በዓል !!!!! 💦💦💦Eid Mubarak 💦💦💦 @amharic_poet @amharic_poet @amharic_poet
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.