cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

In Christ(በክርስቶስ)

We talk more about who we are in Christ

Більше
Рекламні дописи
477
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Фото недоступнеДивитись в Telegram
@whoweareinchrist አንድ መንፈሳዊ መፅሐፍ እያነበብኩ በጣም የገረመኝን ፅሁፍ ላጋራችሁ መልሳችሁን ከስር አስቀምጡልኝ። የትምህርት ቤት ማስታወቂያ ካንሰር፣ ኤች.አይቪ፣ እብደት፣ የነርቭ በሽታ፣ የአጥንት በሽታ፣ መካንነት፣ ሽባነት፣ እውርነት፣ ድንቁርና፣ የአእምሮ ዘገምተኝነት፣ የልብ በሽታ እና የተለያዩ በሽታዎችን ሁሉ ዘርዝርና እንዲህ የሚባሉ ትምህርት ቤቶች ስለከፈትን #ልጆቻችሁን #ላኩና #በእነዚህ #በሽታዎች #በነፃ #እናስተምርላችኋለን #የሚል #ማስታወቂያ #ቢለጥፉ #ማነው #ልጁን #የሚልክ? ማቴዎስ 7:11፤ እንኪያስ #እናንተ #ክፉዎች #ስትሆኑ #ለልጆቻችሁ #መልካም #ስጦታ #መስጠትን #ካወቃችሁ፥ #በሰማያት #ያለው #አባታችሁ ለሚለምኑት #እንዴት #አብልጦ #መልካም #ነገርን #ይሰጣቸው? አንተ ሞኝ ሰው አንተ እንኳን ልጅህ ላይ የማታደርገውን እግዚአብሔር ያደርጋል ብለህ እንዴት ታስባለህ? ያዕቆብ 1:16፤ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ #አትሳቱ። 17፤ በጎ ስጦታ ሁሉ ፍጹምም በረከት ሁሉ ከላይ ናቸው፥ #መለወጥም #በእርሱ #ዘንድ ከሌለ በመዞርም የተደረገ ጥላ በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ። Samuel Wondimu @whoweareinchrist
Показати все...
@whoweareinchrist ዛሬ ቸርች 💒 እንዴት ነበር? እግዚአብሄር አባታችንን በፀሎት ያወራንበት ያመሰገንበት መልካም የሆነ የልጅ እና አባት ግንኙነት ያደረግንበት ነበር በመዝሙር የቀጠለው የጌታ መገኘት በመንፈሱ አረሰረሰን በክርስቶስ የሆነውን እውቅና የሰጠን በመንፈስ ከፍ አልን ወደምንወደው የእግዚአብሄር ቃል ሄድን አዲስ ኪዳናዊ ፀሎት ክፍል 8 #አሳስበኝ የእግዚአብሄር ቃል ለየአንዳንዱ መልካም ነገሮች ይጠቅማል !!! ማቴዎስ 6:5-8 📌ፀሎት ዋጋ አለው ህብረት ብቻ ሳይሆን የምንቀበልበትም ነው። 📌ፀሎትን መደጋገም ችግር የለውም በመፅሃፍ ቅዱስም የደጋገሙ አሉ ፤ ችግሩ ግን በመደጋገምህ ወይም በፀሎትህ ርዝመት እንደምትሰማ ማሰብ ነው። (በዚህ አጋጣሚ የማይደገሙ ፀሎቶች አሉ) 📌እግዚአብሄር የሚያስፈልገንን ያውቃል፤ ይህ ማለት ግን ይሰጣል ማለት አይደለም ለዚህ ነው ፀሎት አስፈላጊ የሆነው። 🔔አማኝ በፀሎቱ ሳይሆን በእግዚአብሄር ነው ማመን ያለበት!!! #በፀሎት_ዙርያ_ምድር_ሰማይን_ይቀድማል! 👉እግዚአብሄር የሆነ ነገር ከማድረጉ በፊት በዛ ጉዳይ ላይ በቃሉ መሰረት የሚፀልዮ ሰዎችን ያስነሳል (ዘካርያስ 12:10) #ትንቢትህ_የጦርነት_ሜዳህ_ነው! 📌እግዚአብሄር ሰው እስካልጠየቀው ድረስ ምንም አያደርግም።(ዘካርያስ10:1) እግዚአብሄር ለምን ጠይቁኝ አለ ፣ለመቀበል እግዚአብሄር ጠይቁ ብልዋልን? ዘካርያስ 10:1 , መዝሙር 2:8, ማቴዎስ 21:22, 7:7-8 “አሳስበኝ፥ በአንድነትም ሆነን እንፋረድ፤ እንድትጸድቅ ነገርህን ተናገር።” — ኢሳይያስ 43፥26 📌አሳስበኝ ይልሃል እግዚአብሄር ፤ ለማሳሰብ በዚያ ዙርያ የተወራ ነገር ያስፈልግሃል። 📌በአንድነትም ሆነን እንፋረድ-ተስማምተን ያንን ነገር እናድርግ ፣አብረን ጉዳዮን እንየው፣ ትክክለኛ መሆንህን አስረዳ 👉ዘፍጥረት 15:13 (ለ400 አመት ትገዛላቹ) -ዘፀአት 12:29(ከ430 አመት በኋላ ወጡ) የአንተ 30 አመት ምንድነው? 📌ለምን ወጡ ዘፀአት 2:23(ጮሁ - አሰበላቸው) የምንወድህ መጋቢያችን ሳሙኤል ወንድሙ ተባርከሃል አንተ ውስጥ ያለውኝ ትልቅ የእጥዚአብሄር ፀጋ እንቀበላለን እናከብርሃለን! Blessed #Pastor_Samuel_Wondimu ቸርች አይቀርም !! 20-04-2015 @whoweareinchrist
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በህይወቴ ብዙ የእግዚአብሔር ሰዎችን አግኝቻለው ፀልየውልኝ ያውቃሉ ነገር ግን #ሁለት #ማግኘት #የምፈልጋቸው #ያላገኘዋቸው በውስጣቸው እግዚአብሔር ያስቀመጠውን ፀጋ የማከብርላቸው የእግዚአብሔር ሰዎች አሉ ከእነርሱ #መሃል #አንዱ_ቄስ_በሊና_ሳርካ #ናቸው። አዲሱን ትውልድ እና ወጣቱን እኔም በነበረኝ የድሮ አስተሳሰብ መቀበል በከበደኝ ሰዓት እንዴት #ትውልድን #መቀበል #እንደሚቻል #በግልፅ #የተማርኩባቸው #ድንቅ #አባት ናቸው። በእሳቸው አገልግሎት የተፈወሱ እኔ በግልፅ የሰማሁት አሁን በሚዲያ የምናውቀው አንድ የእግዚአብሔር ሰው በእሳቸው አገልግሎት የማይሰማ ጆሮው መስማት እንደጀመረ እና ብዙ በዙ ድንቆችን እግዚአብሔር በእሳቸው አልፎ ሰርቷል። ከምንም በላይ ግን የምገረመው #ማንም_የኢትዮጵያን_ከፍታ_አይደለም_ማውራት_ማሰብ_በማይደፍርበት_በዛ_ሰዓት_የከፍታ_ዘመን_ለኢትዮጵያ_ብለው ትልቅ ያዩ ጀግና የወንጌል አርበኛ። በእርሶ የጀመረው ወንጌል በእኛ ይቀጥላል። የትውልድ አባት ወዳገለገለው ጌታ ሄዷል መቼም በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ያደረጉት አስተዋጽኦ እና ተፅዕኖ ልንረሳ አንችልም። ኢትዮጵያም የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንም እርሶ እንዳዩት ወደ ከፍታ ትሄዳለች። ቄስ በሊና ሳርካ ወዳገለገሉት ጌታ ሄደዋል ዕብራውያን 12 (Hebrews) 1-2፤ እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን.... @whoweareinchrist
Показати все...
ዛሬ ከሰዓት አንድ ቦታ ሰው ታሞ ለፀሎት ሄድኩኝ .....እና መንፈሳዊ ቲቪ ቻናል ያላቸው ትልልቅ ሰዎች እየጠራችልኝ እንደ ፀለዩላት ነገረችኝ ግን .... የምትፈልገውን ውጤት ባለማየቷ ትንሽ ጥያቄ ቢፈጠርባትም ጠንካራ የምትባል አይነት ሴት ነች.... ትንሽ እያወራን ፈውሷ ያልተገለጠበትን መንገድ ገባኝ...ረጅም አመት ጌታን አገልግላለች ስለዚህም ጌታ ሊፈውሳት እንደሚገባ ታስባለች እንደዛ አታስቡ .... ረጅም ጊዜ ስለፆማችሁ ፣ ስለ ፀለያችሁ፣ ደግ ሰው ስለሆናችሁ ፣ ጌታን ስላገለገላችሁ፣ መልካም ስራ ስለሰራችሁ...ጌታ ቆጥሮላችሁ አላዳናችሁም። የዳናችሁት በፀጋ ነው የዘለዓለም ሕይወት ያገኛቹትን በነፃ ነው ምንም አልተባበራችሁም ፈውስንም የምትቀበሉት በዚያው መንገድ በነፃ ነው በፀጋ ነው ...እናንተ በእምነት ውሰዱት ይሄው ነው። ስንትም አመት በጌታ ሁኑ ጌታ ለእናንተ የሚቆመው በራሱ ባህሪ ላይ ተደግፎ እንጂ በእናንተ መልካም ነገር ተመስርቶ አይደለም !!! በተለያየ በሽታ ውስጥ ያላችሁ ፈውሳችሁን ለመቀበል ብዙ አትውጡ አትውረዱ ፣ አባት ሆይ ቸር ነህና በልጅህ በኢየሱስ የሰጠኸኝ ፀጋ ላይ አንዳች አልጨመረም ብላችሁ ፈውሳችሁን አረጋግጡ 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ተፈፀመ ዮሐ 19:30 @whoweareinchrist
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
አንድ ጊዜ በአንድ ሀገር ላይ እጅግ በጣም የታወቀ ታላቅ ንጉሥ ነበር። እና ይህም ንጉሥ በግዛቱ ከሚገኙ ከተሞች በአንዷ ትንሽ ከተማ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች "ንጉሥ ምን ቢያደርግላቸው ደስ እንደሚላቸው ተጠየቁ" በዚህ መሠረት አንዳንዶቹ በሕይወት ከኖርኩ ይበቃል ካልገደለኝም በቂዬ ነው ድንበሬን ካልነካብኝ ይበቃል ጠላቶቼን ይጨርሳቸው ሌሎችም መሬት ይሸልሙኝ ቤት ይስጡኝ ወ.ዘ.ተ እያሉ የፈለጉትን ተናገሩ። በስተመጨረሻ ወደአንድ አሮጊት ጋር በመሄድ ሕዝቡ ሁሉ የተጠየቁትን ይጠይቋቸዋል። ከዚያም እኚህ አሮጊት በጣም ተደስተው ጨፈሩ ፣ ዘለሉ ፣ እንደህጻን ፈነደቁ ፣ . . . ከዚያ ከቡረቃቸው ሲመለሱ መልዕክተኞቹ እማማ እባኮትን በፍጥነት ተመልሰን የየሰዉን ምላሽ ለጌታችን ስለምናደርስ ገስግሰን ዛሬ ማደር አለብንና አያያዙን አሉ። ከዚያ አሮጊቷ በእርጋታ " #ንጉሥ_ቤቴ_ይምጡ" አሉ ኸኸኸ !!!!! መልዕክተኞቹ በድንጋጤ ከመቀመጫቸው ብድግ አሉና:- እማማ አይቀልዱ ይህ እንዲህ ሊሆን አይገባም ንጉስ ጋር መግባት ከባድ እንደሆነ እያወቁ ጭራሽ . . . ሴትየዋም ፊታቸውን ቅጭም አድርገው " #አዎ_ንጉሥ_ቤቴ_ይምጡ" አሉ ። ሰዎቹ ሊያሳምኗቸው ባልቻሉ ጊዜ ጥለዋቸው ወጡ። ከዚያ በኋላ ንጉሥ እያንዳንዱን እንደጥያቄው እያስተናገደ ሲያበቃ የአሮጊቷ ጥያቄ ላይ ደረሰ፦ ትንሽ አሰበና እቤታቸው እሄዳለሁ ሲል ባሮች ደነገጡ። ንጉሱ ቀጠለ:- ==ፈጥናችሁ የምገባበት የአሮጊቷን ቤት አስውቡት ለኔ እንደሚመጥን ተደርጎ አዲስ ቤት ይሰራ። ==የቤት እቃዎች በንጉስ ቤት አይነት ዕቃዎች ይተኩ። ==ሁሉ ተስተካክሎ ካለቀ በኋላ የአሮጊቷ ከተማ ውብ ተደርጎ ይሰራ ከዚያ እኔ እመጣለሁ ። ወዳጄ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መኖሪያ ነህ መለኮት አድሮብሀል ታዲያ መለኮት ሲያድርብህ አንተን አስውቦ ፣ ውስጥህን ሰርቶ ፣ ውጪህንም ለራሱ ቀድሶ ባንተ ምክንያት ለዙሪያህ ጭምር በረከት ለመሆን ነውና ይህን እወቅ። ቤተመቅደሱ ሲሰራ መለኮት በራሱ ዲዛይን ለራሱ እንደሰራው እወቅ። መለኮት እያደረብህ ከርካሳ ጣሳ ቱቦ ነኝ ምናምን ትላለህ እንዴ???? ኧረ የመለኮት መኖሪያ ነህ። መኖሪያው ትሆን ዘንድ የተቀደስህ ፣ የተባረክህ ፣ የተመረጥህ ። 1 ቆሮንቶስ 3 16፤ #የእግዚአብሔር_ቤተ_መቅደስ_እንደ ሆናችሁ_የእግዚአብሔርም_መንፈስ_እንዲኖርባችሁ_አታውቁምን? ይግረምህና ንጉስ ስለመጣ ሁሉ መልካም ነገር ውጤት ሆኖ አግኝቶሃል። የክርስቶስ የመሆንህ መዘዝ መልካም ነገሮችን ወደአንተ ይስባል። አሸናፊነት ገዢነት ድል . . . የአንተ ናቸው። ሮሜ 8 32፤ ለገዛ ልጁ ያልራራለት ነገር ግን ስለ ሁላችን አሳልፎ የሰጠው ያው ከእርሱ ጋር ደግሞ ሁሉን ነገር እንዲያው እንዴት አይሰጠንም? @shalomgracegospel @shalomgracegospel https://t.me/shalomgracegospel
Показати все...
Grace Gospel

ትውልድ የእግዚአብሔርን ፍቅር በመማር በእግዚአብሔር ፍቅር ህይወቱ እንዲቀየር ለማድረግ የጸጋውን ወንጌል እናስተምራለን። Comment @EsseyShalom @Metu_boy

ዋጋ! የዮሐንስ ራእይ 22 12፤ እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ #ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ። Revelation 22 12 'Behold, I am coming quickly, and My #reward is with Me, to render to every man according to what he has done. ብዙዎች ከላይ ያስቀመጥኩትን ቃል ጂምናስቲክ እያሰሩ ቃሉ የማይለውን እንዲልላቸው ሲሞክሩ ይታያል! ይህ ቃል፣ ብዙ ሰው የጌታን ዳግም መምጣት ሲያስብ እንዲፈራ የሚያደርግ ቃል ሳይሆን ቤተክርስትያን የተባረከ ተስፋዋን በሀሤት እንድትጠብቅ የሚያደርግ ድንቅ ቃል ነው! በዚህ ቃል ውስጥ ልብ ልንለው የሚገባን ጉዳይ፣ ይህ ቃል ሙሽራው ክርስቶስ፣ ሙሽሪት ለሆነችው ለቤተክርስትያን የላከላት መልዕክት መሆኑን ነው! አንድ ሙሽራ ሙሽሪትን ሊወስድ ሲሄድ፣ በትልቅ ደስታና ፍቅር እንጂ በብዙ ቁጣና በቀል እንዳልሆነ ሁሉ ፣ ሙሽሪትም ሙሽራዋን ስትጠብቅ በብዙ ሳቅና ናፍቆት ነው! በዚህም ክርስቶስ፣ ''ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ'' ብሎ ሲል ለቤተክርስትያን ይዞ ስለሚመጣው ሽልማትና አክሊል እንጂ ስለ ቁጣና ፍርድ አለማውራቱን እንረዳለን! ለዚህም በአማርኛው ትርጉም ላይ ''ዋጋ'' ተብሎ የተጠቀሰው ቃል በእንግሊዘኛው ''reward'' ወይም ''ሽልማት'' የሚል ትርጉም መያዙን ማየት ከበቂ በላይ ነው። የምንጠብቀው ሙሽራችን ሽልማትና አክሊል ይዞልን የሚመጣ አፍቃሪ እንጂ ቁጣና ፍርድ ይዞብን የሚመጣ ክፉ አይደለምና ደስ ይበለን! ወንድም ቢንያም ተስፋዬ @ye_adis_kidan_hiwot
Показати все...
ደዌ/በሽታ የእግዚአብሔር ፈቃድ ቢሆን ኖሮ መንግስተ ሰማይ በደዌና በበሽታ በተሞላ ነበር። E.W.Kenyon ❤️❤️ @whoweareinchrist ❤️❤️
Показати все...
2 ቆሮንቶስ 5 17፤ ስለዚህ #ማንም_በክርስቶስ_ቢሆን_አዲስ_ፍጥረት_ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። ይህ ክፍል በጣም አስደናቂ መንፈሳዊ እውነታን ይዟል። #ማንም - ይህ ማለት ማንኛውም ሰው ፥ ማንም በአዳም የነበረ ፥ ከየትኛውም ዘር የሆነ ሰው በሙሉ ማለት ነው ስለዚህ ከክርስቶስ መስዋዕትነት በኋላ ለአዲስ ፍጥረትነት ዕድል የሌለው ሰው የለም ማለት ነው ። #በክርስቶስ - ይህ ማለት ሰው ሁሉ አስቀድሞ በአዳም የነበረ በመሆኑ ከአዳም የተነሳ ኃጢአተኛ እንደሆነ ከአዳም የተነሳ ኃጢአት የተቆጠረበት እንዲሁም ከአዳም በመወለዱ በመካፈል ኃጢአተኛ ለሆነ ሰው እግዚአብሔር ታላቅ እድል አዘጋጀ ይህም በክርስቶስ መሆን ሲሆን በዚህም በክርስቶስ ውስጥ ያሉ በጎ ነገሮች ሁሉ ተካፋይ መሆን ማለት ነው። ምክንያቱም በክርስቶስ መሆን ማለት በክርስቶስ ውስጥ መጨመር ማለት ነው። #አዲስ - የዚህ ቃል ትክክለኛ ትርጓሜ ከዚህ በፊት ያልነበረ እንደማለት ነው። የታደሰ ሳይሆን አዲስ ነው። የታደሰ ማለት አሮጌ ተሻሽሎ ነው። እግዚአብሔር የተሻሻለ ፍጥረት አይደለም ያደረገን ነ.ግን ፈጽሞ አዲስ ፍጥረት ተደርገናል። #ፍጥረት - ይህ ቃል የዚህ ስራ ባለቤት እግዚአብሔር ራሱ መሆኑን ያሳያል ምክንያቱም ፈጣሪ እግዚአብሔር ነውና ፍጥረት ከተወራ አድራጊው ፈጣሪ ነው። ስለዚህ ክርስትና በክርስቶስ መሆን እና በእርሱ በመሆን ምክንያት በእርሱ ያለውን የሕይወት አይነት መካፈል ነው። ይህ አዲሱ ፍጥረት የእግዚአብሔር ልጅነትን የተቀበለ የእግዚአብሔር ቤተሰብ ነው። አዲስ ፍጥረት ይሆናል የሚል ተስፋ ሳይሆን በክርስቶስ ከሆነ አዲስ ፍጥረት ነው። አሁን ነው። ወዳጄ ኃይማኖት አያድንም መጠመቅ ሆነ መገረዝ ሆነ ሌላ ኃይማኖታዊ ስርዓት ለድነት ረብ የለውም ነ.ግን በአዳም የሆነ ሁሉ በሞት እንዳለ በክርስቶስ የሆነ ሁሉ የዘላለም ሕይወት አለው። አዲስ ፍጥረት ሆኖ የእግዚአብሔር ቤተሰብ መሆን ቀላል ነው። በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን ብቻ። ይህን የፍቅር ግብዣ ለሚያውቋቸው ሁሉ ይጋብዙ። ብሩካን ናችሁ። @shalomgracegospel @shalomgracegospel https://t.me/shalomgracegospel
Показати все...
Grace Gospel

ትውልድ የእግዚአብሔርን ፍቅር በመማር በእግዚአብሔር ፍቅር ህይወቱ እንዲቀየር ለማድረግ የጸጋውን ወንጌል እናስተምራለን። Comment @EsseyShalom @Metu_boy

Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.