cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

Рекламні дописи
1 983
Підписники
+1824 години
+997 днів
+34230 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Фото недоступнеДивитись в Telegram
በዶናልድ ትራምፕ ላይ የተኮሰው ግለሰብ ማንነት ታወቀ የአሜሪካ የፌደራል ምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) በቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ላይ የተኮሰው ግለሰብ ቶማስ ማቲው ክሩክስ የተባለ የ20 ዓመት ወጣት መሆኑን አስታውቋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፔንስልቬንያ የምርጫ ቅስቀሳ ሲያካሂዱ የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸው በጆሯቸው አካባቢ መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ጥቃት ፈጻሚው ወደ ዶናልድ ትራምፕ ከመተኮሱ በፊት የሕዝብ መጨናነቅ በነበረት ቅስቀሳው ላይ ሌላ ሰው መግደሉም ተሰምቷል። ግለሰቡ ወዲያውኑ በደህንነት ሰዎች የተገደለ ሲሆን ሕግ አስከባሪዎች ይህ ክስተት እንዲፈጠር ያሳዩት ክፍተት ጥያቄ እያስነሳ ነው።
Показати все...
የአውሮፓ ዋንጫና ኮፓ አሜሪካ ዛሬ ፍፃሜያቸውን ያገኛሉ🔥 ዛሬ የሚደረግ የአውሮፓ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ            ⏰ ማታ 04:00      🇪🇸 ስፔን ከ እንግሊዝ 🏴󐁧󐁢󐁥󐁮󐁧󐁿 🏟️ ስታድየም - በርሊን ኦሎምፒክ 🌎 ዛሬ ለሊት የሚደረግ የኮፓ አሜሪካ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ          ⏰ ለሊት 09:00 🇦🇷 አርጀንቲና ከ ኮሎምቢያ 🇨🇴 🏟️ ስታድየም - ሀርድ ሮክ ስታድየም
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
አማራ ክልል በ17 ከተሞች ኢንተርኔት ተለቀቀ አማራ ክልል ኢንተርኔት የተለቀቀላቸው ከተሞች ቁጥር ወደ 17 ከፍ ማለታቸው ተሰምቷል።እንጅባራ:ፍኖተ ሰላም እና ቡሬ ተጨምረዋል። ከሰሞኑ 👇 👉ባህር ዳር 👉ደብረ ማርቆስ 👉ደጀን 👉 ጎንደር 👉ደብረ ታቦር 👉ሁመራ 👉ገንደውሃ 👉ደብረ ብርሃን 👉ወልዲያ 👉ደሴ 👉ኮምቦልቻ 👉ከሚሴ 👉ባቲ 👉ሰቆጣ ተለቆ ነበር። በ3G አስጀምሩት።በክልሉ ባጋጠመ ግጭት ኢንተርኔት ከተቋረጠ አመት ማለፉ ይታወሳል።(wasu)
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
Breaking news, ትረምፕ ምርጫ ቅሰቀሳ ላይ እያለ ከደቂቃዎች በፊት በመድረኩ ላይ የጥይት ድምጽ በመሰማቱ በፍጥነት በጠባቂዎቻቸው ከመድረኩ እንዲወርዱ ተደርገዋል:: የተተኮሰው ጥይቅት ይሁን ተቀጣጣይ ነገር ጆሯቸው አካባቢ እንደመታቸውና እንደደማ ተንቀሳቃሽ ምስሉ ያሳያል:: በትራምፕ ላይ የተኮሰ ሰው ህይወቱ አልፏል:: ግለሰቡን ፖሊስ ተኩሶ ይምታው እራሱን ያጥፋ ግን እስካሁን መረጃዎች አልወጡም:: BBC ግለሰቡ መሞቱን ብቻ ዘግቧል:: ከደቂቃዎች በፊት ዶናልድ ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳ ላይ እያሉ  ሲተኮስባቸው የሚታይበትን ቪዲዮ ላይ ፡ ትራምፕ ጆሯቸው  አካባቢ በመጠኑ የደማ ነገር ይታያል ።  እና የሚገርመው ምንድነው  ? የፀጥታ ሀይሎች ትራንፕን ከበው ሲወስዷቸው ፡ በእናሸንፋለን ምልክት እጃቸውን ጨብጠው ለደጋፊዎቻቸው ያሳዩ ነበር ። .... እንደውም. . በቀጥታ ታርጌት ከሆኑት ከሳቸው ይልቅ  በአካባቢው የነበረው ሰው ደንግጧል ። .......... በዚህ በዛሬው የፔንስልቫንያ ጥቃት ፡ የግድያ ሙከራውን ያደረገው ሰውና ፡ የሌላ የአንድ ሰላማዊ ሰው ህይወት እንዳለፈ  እየተነገረ ነው ። .....
Показати все...
👍 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
የወርቅ ኮንትሮባንድ .... በትግራይ የታጠቁ ኃይሎችና የውጭ ዜጎች ከሚሳተፉበት የወርቅ ሕገወጥ ቁፋሮና ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ከሚያዝያ ወዲህ ብቻ ከ20 በላይ ሰዎች እንደተገደሉ በምርመራ ማረጋገጡን ሪፖርተር ዘግቧል። በተለይ እንዳባጉና ወረዳ የሚገኘው የትግራይ ጀኔራሎች የሚቆጣጠሩት "ራህዋ" የወርቅ ማውጫ ከፍተኛ ሕገወጥ የወርቅ ቁፋሮና ኮንትሮባንድ እንደሚካሄድበትና ተዋናዮቹ የቀድሞ የሕወሃት ተዋጊዎች፣ ወጣቶች፣ ስደተኞችና ቻይናዊያን እንደኾኑ ዘገባው ጠቅሷል። ዘገባው፣ በሰሜን ምዕራብ ትግራይ በ"ሒንጻት" የወርቅ ማውጫ ከኹለት ወራት በፊት በቀድሞ የሕወሃት ታጣቂዎችና በጥበቃዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት 22 ሰዎች እንደሞቱ መስማቱን ገልጧል። ሕገወጡ ወርቅ ወደ አዲስ አበባ፣ አሥመራ፣ ሐርጌሳ፣ ናይሮቢ እና ካምፓላ እንደሚሸጥና ከዚያም መዳረሻው ዱባይ እንደኾነ ምንጮች ስለመናገራቸው በዘገባው ላይ ተጠቅሷል።(ሪፖርተር)
Показати все...
👍 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ሜታ ኩባንያ በዶናልድ ትራምፕ ፌስቡክ እና ኢንስታግራም ገጾች ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ አነሳ ሜታ ኩባንያ ከሶስት ዓመት በፊት ነበር ገጾቹን የዘጋው። ዶናልድ ትራምፕ አሁንም የሜታ ኩባንያ ህግን ካላከበረ እገዳው ሊቀጥል እንደሚችል አስጠንቅቋል። Alain
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
አርቲስት መቅደስ ፀጋዬ የቱሪዝም የክብር አምባሳደር ሆና ተሾመች!! የአዲስ አበባ የባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ በዛሬው እለት በአካኼደው የኪነጥበብ እና የቱሪዝም የትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት የምስረታ ጉባኤ ላይ አርቲስት መቅደስ ፀጋዬን የአዲስ አበባ ከተማን በሀገር አቀፍና በአለምአቀፍ መድረኮች ላይ እንድታስተዋውቅ የክብር አምባሳደር አድርጎ ሾሟታል። አርቲስት መቅደስ ፀጋዬ ከኪነጥበብ ስራዎቿ ባሻገር የሀገሯን መልካም ገፅታ በማስተዋወቅና የተቸገሩ ዜጎችን በተለያየ መንገድ በመርዳት የምትታወቅ ተወዳጅ አርቲስት ነች። መልካም የስራ ዘመን ይሁንልሽ።
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ስትከፍቱት እንደዚ የሚመጣላቹ ከሆነ የቴሌግራም አካውንታቹ ላይ Telegram setting ላይ በመሄድ Username የሚለው ቦታ ላይ የፈለጋችሁትን ስም ካስገባችሁ ይሰራላቹሃል 
Показати все...
New Project እስካሁን ካሉት ውስጥ ቢያንስ አንዱ list ሳይደረግ አዲስ Airdrop recommend አላደርግም ብየ ለራሴ ቃል ገብቼ ነበር።🙈 ነገር ግን Dogs የተባለዉን Airdrop የnotcoin official channel Share ሲያደርገው አልቻልኩም። Btw I love #notcoin project!!ምክንያቱም ሳላስበው አንበሽብሾኛል ኮይን የሚሰጥተው 3 ነገሮችን አይቶ ነው። ⚫ቴሌግራም አካውንታችሁ የተከፈተበትን እድሜ ⚫Premium ተጠቃሚ መሆናችሁን ⚫ለጊዜው Tap/Tap የለውም። እሱም አንድ እፎይታ ነው። pre market ላይ10ሺ የሰራ ሰው እስከ 100$ ያገኛል  እየተባለ ነው 😳 አሁን ጀምሩ!👇👇👇 https://t.me/dogshouse_bot/join?startapp=tBSzCnvdQcOcHn4MnXIcrA https://t.me/dogshouse_bot/join?startapp=tBSzCnvdQcOcHn4MnXIcrA
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በእንግሊዝ እስር ቤቶች በመጨናነቃቸው በሺዎች የሚቆጠሩ እስረኞች ሊለቀቁ ነው እስር ቤቶች በመጨናነቃቸው ምክንያት በእንግሊዝ እና በዌልስ በሺዎች የሚቆጠሩ እስረኞች እንደሚለቀቁ የአገሪቱ የፍትሕ መሥሪያ ቤት ባለሥልጣን አስታወቁ። ባለሥልጣኗ ሻባና ማህሙድ በእስረኞች የተጨናነቁ እስር ቤቶችን ጫና በአስቸኳይ ማቃለል ካልተቻለ የአገሪቱ “ሕግ እና ሥርዓት ሙሉ ለሙሉ የመፍረስ አደጋ ሊገጥመው ይችላል” በማለት የእርምጃውን አስፈላጊነት አሳስበዋል። በእንግሊዝ እና በዌልስ ውስጥ በሚገኙ እስር ቤቶች ያለውን የታሳሪዎች ብዛት ለማቅለል የፍትሕ መሥሪያ ቤቱ ባቀረበው ዕቅድ መሠረት ከተፈረደባቸው የእስር ጊዜ 40 በመቶውን ያጠናቀቁ የተወሰኑ እስረኞች የሚለቀቁ ይሆናል። በዚህም መሠረት በመጪው መስከረም ወር በሺዎች የሚቆጠሩ እስረኞች በመጀመሪያው ዙር የሚፈቱ ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ ባሉ 18 ወራት ውስጥ ደግሞ ተጨማሪ እስረኞች ደረጃ በደረጃ የሚለቀቁ እንደሚሆን ባለሥልጣኗ አሳውቀዋል።
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.