928
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
- Підписники
- Перегляди допису
- ER - коефіцієнт залучення
Триває завантаження даних...
Приріст підписників
Триває завантаження даних...
በውቄ
አልወጣም ተራራ ደመናን ልዳብሰ
ቀስተ ደመናውን ቁልቁል ልቀለብስ
አልዋስም እኔ
ካቡነ ተክሌ ክንፍ
ከያዕቆብ መሰላል፤
እኔ መውጣት ሳስብ
ሰማዩ ዝቅ ይላል::
________________________________
ለወዳጅዎ ያጋሩ @thiolophy
በዕውቀቱ ስዩም
ህልም አለህ ይላሉ
ራዕይ ያዘለ
ኮከብ አለህ አሉ
ትንቢት የታደለ
ህልምህን ንገረኝ
ኮከብህን አሳየኝ
ተርጉሜው ልፅናና
መነሻዬን ልወቅ መድረሻዬን ላጥና
ባንተ ዕጣ ፈንታ ውስጥ ርስት አለኝና።
_______________________________
ለወዳጅዎ ያጋሩ @thiolophy
የኔታ ፍቄ(ግጥም እና ፍቅር)
፡
ምን ያህል ቢከፋ ምን ያህል ቢያሳምም፣
ለአላዘር መሞት
የክርስቶስ እንባ በጉንጩ ሚዘምም፣
፡
እንዴትስ ቢያንስ ነው እንዴትስ ቢጣጣል፣
በመግደል መሸነፍ
እስከመቼ ድረስ ኖሮ ያልጠገበ በሞቱ ይቀጣል፣
፡
ወረርሽኙ ሲነግስ ተጠንቀቁ ብለው የነተረኩኑ፣
ገዳይ ሲያሰፈስፍ
ሜንጫ ሲሳልብን ስለምን ጨከኑ፣
ወይንስ
ገዳይ መሸነፉ
እንዲገባው ብለው ሟች ላይ ተዋገኑ፣
፡
ምን ያህል ቢከፋ ምን ያህል ቢያሳምም፣
ለአላዘር መሞት
የክርስቶስ እንባ በጉንጩ ሚዘምም፣
፡
ሞትማ ህመም ነው
የአምላክን እንባ ቋት የደነቆለ፣
ልቡን ያሳዘነ
የወዳጁ በድን ስላቆለቆለ፣
አፈር ተምሶለት ባፈር ስለዋለ፣
፡
እሱ ከታመመ እኔንማ እሰቡኝ፣
ማች ስቆጥር የምውል
መግደል መሸነፍ ነው ብለው ከትበውኝ፡፡
________________________________
ለወዳጅዎ ያጋሩ
@thiolophy
የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች
68. ሚካኤል ተው ተብት በኩፍር ሳትቀጣ
ይበቃሃል የሚል ከአላህ አዋጅ መጣ
እንዴት ያለች ንፋስ የሆነች ባላንጣ
በጥፊ ብትመታው በአፍንጫው ደም መጣ
ጉዞው ተቃረበ እሩሁ ልትወጣ::
69. ጉግሣና ራስ ( ወ )ሎሌ፣ አጼ ዮሐንስ
ሚካኤል፣ ምኒልክና አጼ ቴዎድሮስ
ዘውዲቱና ፈረንጅ ተፈሪ ድረስ
በብልሃት ገዟት አልጋው እንዳይፈርስ
መጨረሻው ከፍቶ ጣሉት እንደርኩስ::
70. የአላህን ትተው በውሻ የሚመሩ
በሐበሻ መሬት ግፍን የሚሠሩ
ቁመታቸው አጭር መልካቸው የሚያምሩ
አይነግሡም ብላችሁ አትወዳደሩ
ሃምሳ ዓመት ይነግሣል እግረ ውትርትሩ::
7 1 .ባሕር ወዲያ ማዶ ዘር መጣ ሊጠቅም
ግድግዳው የሚያምር በሽንጥ የሚጠቅም
ቅጠሉ ለስላሳ ቁመቱ ረዣዥም
እሱን ያልተከለ እንዴት ይለጅም
ሸዋ በተለየ ያለሱ አይቆምም::
72. ሥራቸው ባለጌ አህያ የሚበሉ
ባሕር ወዲያ ማዶ ክፉ ሰዎች አሉ፣
ሐበሻን ለመውረር ሐሳብ ያስባሉ
የኋላ የኋላ መምጣት ይመጣሉ
አምስት ዓመት ገዝተው ወዲያው ይሄዳሉ::
73. ድንጋይ ዱቄት አርገው መንገድ የሚያበጁ
ገመድን ዘርግተው መብራት የሚያበጁ
አህያ የሚያርዱ አሞራ የሚፈጁ
መጡ እየተማሩ ሐበሻን ሊያበጁ
ማማሩን አማረች ግን ብዙ ሰው ፈጁ::
74. እግሩ እንደ ሙቀጫ የሚንከባለል
ቢሄድ አይታክተው አቀበት ቁልቁል
ጭቃ ካለው መንገድ መሄድ የማይችል
ገደል የሚያንሸራትተው የሚንከባለል
ይህንን የገዛ ካለፈው ምንም አይል::
75. በገዛ እጁ ነድፎ ፈትሎ የሚሠራ
ሰውን የሚያስገርም የሚሠራው ሥራ
ልብሱ ተፈላጊ ሰውን የሚያኮራ
ልብሱን ላይሸከሽክ አስተውሎ የሚሠራ
በዚህ አይግረምህ ሌላ አለ የሚሠራ::
________________________________
ለወዳጅዎ ያጋሩ @thiolophy
✍ መገንሽ
በስውር ስትወርጂ
ኖሮ ላፈር ገላሽ
ከጥፋትሽ:ገኖ፣ አንቺን ሚጠጥትሽ
ባል-ሰማ ነው አሉ፣ባል አወቀ ጭንቅሽ።
'ሰቢ ፯
________________________________
ለወዳጅዎ ያጋሩ ከአባል የተላከ
#yeneta #ሼር
ሚስት-- ላንተ ስል ከአለም እንደምጣላ ታውቃለሃ?
ባል-- ግንኮ ሁሌ ከኔ ጋር ነው ምትጣዪው
ሚስት-- ምክያቱም የኔ ዓለም አንተ ነሃ፡፡
😂❤️😂❤️😂❤️😂❤️😂❤️😂
________________________________
ለወዳጅዎ ያጋሩ @thiolophy
🔰Online ስራ መስራት እንፈልጋለን ላላችሁ ይሄን⬇️ ቦት ተጠቀሙ፤ ሞክሬው ሰርቷል።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://telegram.me/ask_anything_ethiopia_bot?start=i392939044
1⃣. ቦቱን Start በሉት።
2⃣. Join Channel የሚል ይመጣል #Join በሉት። 👉 @askAnythingEthiopia 👈
🔆ለተለያዩ ሰዎች በላካችሁ ቁጥር፤ በየአንዳንዱ ሰው 1ብር ይከፍላችኋል።✅
❗️ቦት ውስጥ ከገባችሁ ብኋላ join channel የሚል አለ እሱን join ማለት አለባችሁ እንጂ ቦቱን ብቻ ስለተቀላቀላችሁ አይቆጥርላችሁም
አንድ ነገር ላስቸግርህ? 🙏
❇️ Online ስራ መስራት እንፈልጋለን🤔 ላላችሁ ይሄን⬇️ ቦት ተጠቀሙ፤ ሞክሬው ሰርቷል።
💡ስለ ቦቱ ቀለል አርጌ ለመንገር ያህል:-
ከታች ያለውን ሊንክ ነህተሽ ሁለታችንም ትርፋማ እንሁን🤷♂️🤷♂️
የሚሰራው በመጀመሪያ ሊንኩን start ብለህ Ask Any Things bot ውስጥ ተቀላቀይ በመቀጠል invite ሚለወን በመንካት share ሚለወን እየነካህ በ 1 ሰው 50 ሳንቲም የከፈልሀል ጊዜው አሁን ነው::💁🏿♂
መርሳት የሌለብህ ነገር ግን👇
#bot_start_ብለህ_join_channel_ሚለውን_መንካት_ይኖርብሀል
Start
Join channel
"እነሱ፤ እነሱ የምትሉት እነማን ናቸው? እኛስ እነማን ነን? እነሱ እነሱ ከማለት ራሳችንን ዞር ብለን እንመልከት። ወደኛ ዞር ብንል የምናየው ምንድን ነው? ወኔ ቢስ፤ የምቾት አታሞዎች ሆነን እንገኛለን። ከካስቴሊ ወይም ከኢትዮጵያ ሆቴል ስንወጣ ፤ ለማኞች ላይ እያገሳን የምናልፈው እኛው ነን። ወገኖቻችን መሬት ቆፍረው፤ ከመሬት ላይ ያገኙትን በልተው፤ እጦት ካፍንጫቸው ስር ላንድ ቀን ሳትርቅ እዚያው መሬት ላይ ሞተው እንደሚቀበሩ እያወቅን፤ በስምንትና በዘጠኝ መቶ ብር (በአሁኑ 8 እና 9 ሺ ማለት ነው) ላይ ደመወዝ ይጨመርልን በማለት ጧት ማታ ማመልከቻ የምናንጋጋው እኛው ነን…
"ለሀገር ልማት ይህን ያህል ከደሞዛችሁ ስጡ ብንባል መጀመሪያ የምናለቅሰው እኛው ነን። መንግስት ጀርባ ላይ እንደቱሀን ተጣብቀን የምንኖረው እኛው ነን። ከሞግዚት ጉያ ወጥተን፤ በሁለት እግራችን መቆም ያስፈራናል። በራሳችን ላይ እምነት የለንም። ማንነታችንን አናውቅም…
"እንደኛ ያሉት ሰዎች በየትኛውም መንግስት ስር ያው ናቸው፤ ከማማረር አያልፉም። ታዲያ ይህ ሁሉ የጓዳ ወሬ፣ ይህ ሁሉ አሉባልታ፣ ይህ ሁሉ የትችት መአት የራሳችንን ጉድለት ለመደበቅ፤ ወኔ ቢስነታችንን ለመሸፈንና ያደፈውን ህሊናችንን ለመደለል ነው እንጂ ለሌላ አይደለም። ግን እስከመቼ ድረስ? እስከመቼ ድረስ?"
፧
፧
📚📚📚
ምንጭ:- 👉"ከአድማስ ባሻገር" ከበዓሉ ግርማ
ገጽ 71-72
✍ ንባብ ለሕይወት
@thiolophy
@thiolophy
@thiolophy
#ማንበብ_ምናልባት_ምናልባት_የተሻለ_ሰው_ሊያረግ_ይቻላል
ፍልስፍና ምንድን ነው?
፨፨፨
ፍልስፍና ምንድን ነዉ? ተፈጥሮዉ ወይም ባህሪዉ ምንድነዉ? መልስ ከምናገኝባቸዉ መንገዶች አንዱ የቃሉን ማለትም የ"ፍልስፍና" ሥርወት (etymology) በመዳሰስ ነዉ። ፍልስፍና ከጽርእ ቋንቋ የተገኘ ነዉ፣ ፊሎሶፊያ የሁለት ቃላት ሕብረት ሲሆን፤ ፊልያ ማለት #ፍቅር፣ ሶፊያ ማለት ደግሞ #ጥበብ ነዉ፣ ስለዚህ ፍልስፍና ማለት የጥበብ ፍቅር ማለት ነዉ። ይሁን እንጂ ፍቅር ማለት ምንድነዉ? ጥበብስ? ፍቅር ማለት አካላዊ ያልሆነና በማንም ሠዉ ልትጭነዉ(impose) እና ልትማረዉ የማትችል ነገር ነዉ። ማፍቀር የእኔነት(ራስ) አንድ ገፅታ ነዉ። በራስ ብቻ ነዉ ሊኮተኮት፣ ሊጎለብትና ሊጠነክር የሚችለዉ። ፍቅር መሠረታዊ ዝንባሌ ነዉ፣ ወይም እኔነት ወደ ህልዉ የሆነዉ ነገር የሚያነጣጥርበት ነዉ። እንዲሁም እኔነትን እዉን በማድረግ ፕሮጀክት ላይ በጣም መሠረታዊ ጥንተ ነገር (element)ነዉ።
፧
ጥበብም አካላዊ ያልሆነ እንደ ፍቅር ከራስ ወይም ከእኔነት ጋር የተያያዘ ነዉ። ልክ እንደ ሣንቲም ሁለት መሠረታዊ ገጽታዎች አሉት። በአንደኛዉ ገጽታ በሁሉም የሕይወት አቅጣጫዎች ምክንያታዊ ባሕሪ ሲሆን፤ ለሰዉ ልጅ በትክክል ጥሩ የሆነና በትክክል መጥፎ የመግለጽ ወይም የመወሰን አቅም ነው።
ፍልስፍና እና መፈላሰፍ የሃይማኖትና ባህል ፀጋዎችን የሚፈታተን አለፍ ሲልም የሚቃረን ነው የሚል እምነት ቀኖናዊ ጭፍንነት አሊያም ገራገርነት(naivete) ከመሆን አልፎ በሙግታዊ አመክንዮ ሲደገፍ አልታየምም።
አግባብ ባለው መንገድ እስከተከናወነ ድረስ የፍልስፍና ጥናት ከመንፈሳዊ እድገታችን ጎን ለጎን "የራስን" እዉቀታችን፣ ዉስንነታችንና አቅማችንን በማወቅ ሂደት ላይ አጋዥ ነው። ይህን እዉቀት ከራሳችን ከ"ዉስጥ" የሚፈልቅ እንጂ ከእኛ "ዉጭ" የሚገኝ አይደለም።
፧
እኛ የምናድግ ፍጡሮች ነን። በቀጣይ የመሆን ሂደት ላይ ያለን - ቢያንስ ለማርጀት! ግን ደግሞ በተስፈኝነት ወደተሻለ በመሆን ሂደት ላይ ነን፣ የበለጠ ለመማር፣ የበለጠ ክህሎት ለመደለብ፣ የበለጠ ለመብሰል ብልህ ለመሆን።
፨፨፨
ምንጭ ፦
(የፍልስፍና መግቢያ ከሚለው መፅሀፍ የተወሰደ)
Credit to ፦ ፈቲያ
@thiolophy
@thiolophy
@thiolophy
#ማንበብ_ምናልባት_ምናልባት_የተሻለ_ሰው_ሊያረግ_ይቻላል