cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

✞ማሕበረ ናታኒም✞

ጎልማሳ መንገዱን በምን ያነፃል? ቃልህን በመጠበቅ ነው።(መዝ 119፥9) ናታኒም፦ ማለት የእግዚአብሔር ቤት ጠራጊዎች ወይም የእግዚአብሔር ቤት አገልጋይ ማለት ነው። ✝በቻናላችን 👇👇 ❖ ስብከት ❖መዝሙር ❖ ስንክሳር ❖መንፈሳዊ PDF ❖ ስዕለ አድኖ ❖ ብሒላተ አበው እና ሌሎችም ❖ መንፈሳዊ ይዘት ያላቸው ነገሮች ይለቀቁበታል። 🙏ሊንኩን ለወዳጅ ዘመድዎ ሼር ያድርጉ🙏

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
174
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

የእራሔል እንባ ተመልክተ ህዝበ እስራኤል ከግብፅ ባርነት ነፃ እንዳወጣሃቸው እኛም በእነዚህ እንባ ከጎሳ ፓለቲካ ነፃ አውጣን
Показати все...
✝💚💛❤✝💚💛❤✝💚💛❤✝💚💛❤✝ ከእናንተው በዲ.ን ዘልዑል ምናሉ የቀረበ። #ጧፍ_በቅዳሴ_ሰአት_ለምን_እናበራለን? ጧፍ ምሳሌነቱ ፦ ጣፍ የሚሰራው ከሁለት ነገር ነው እሱም ከፈትልና ከሰም ይሰራል ። ሰሙ የሃይማኖት ፣ ፈትሉ ደግሞ የምግባር ምሳሌ ነው ። ሰሙ ብቻውን ይብራ ቢባል ይቀልጣል እንጂ አይበራም ። ፈትሉ ብቻውን ይብራ ቢባል ብቻውን ቶሎ ነዶ ያልቃል ። ምግባር ብቻውን ረጅም ጉዞ አይጓዝም ፣ ሐይማኖትም ብቻውን ምግባር ከሌለው የሞተ ነው ። ፈትሉ ከሰሙ ጋር ሰሙ ከፈትሉ ጋር አንድ ሆነው እንደሚያበሩ ሁሉ፡ ሐይማኖት ከምግባር ምግባር ከሐይማኖት ጋር አንድ ከሆነ ያበራል ፡፡ በዚህ ምክንያት በቤተክርስትያናችን የመብራት መስዋት ይቀርባል፡ ካህኑ ወንጌል ሲያነብ ጧፍ ይይዛል ፡፡ አልጨለመ ብርሃን አለ? ቢሉ ክቡር ዳዊት ህግ ለእግሬ መብራት ለመንገዴም ብርሃን ነው (መዝ 118 ፥ 105) ብሏል ። ወንጌል ነውና የሚነበበው፡ ወንጌሉም ለእግራችን መብራት ለመንገዳችንም ብርሃን ስለሆነ ነው በቤተ ክርስትያን ውስጥ በብዛት ሻማ አለ ይህም እግዚአብሔር በባህሪው ብርሃን ስለሆነ ነው ሻማው እየቀለጠ ብርሃን ይሰጣል ። ይህም ቅዱሳኑ ስለ ቤተክርስትያን እነደ ሻማ እየቀለጡ ለአለም ብርሃን የመሆናቸው ምሳሌ ነው ፡፡ + የዲያቆናት ምሳሌነታቸው ፦ ከካህኑ ፊት መብራት የያዘው ዲያቆን የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ነው ። ብርሃን እሱ እንጂ እኔ አይደለውም የአለም አጥያት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ እንዳለ መስቀል ተሸክሞ ከካህኑ በኋላ የሚከተለው ዲያቆን ደግሞ የቀዳሜ ሰማዕት የዲያቆን እስጢፋኖስ ምሳሌ ነው ። ሌላው፡ ካህኑ ዲያቆኑ መብራት የሚያበራው የክርስቶስ ወንጌል የቅዱሳኑ ህይወት መብራት ስለሆነ.ነው። ሌላኛው የክርስትያን ህይወት በራሱ ብርሃን ነው ። ብርሃናቹ በሰዎች ሁሉ ፊት ይብራ ማቴ 5 ላይ ብሏል ። መብራት የበጎ ነገር ምሳሌ ነው ። እግዚአብሔር በራሱ ብርሃን ነው ፣ እግዚአብሔር ብርሃንና መዳኒቴ ነው ፣ የሚያስደነግጠኝ የሚያስፈራኝ ማነው ፣ ቤተክርስትያን በጸሎት ሰአት መብራት ስናበራ እግዚአብሔር ከኛ ጋር ነው ማለታችን ነው ። ኢየሱስ ክርስቶስም.ብርሃን ነው ። ዮሐ 1 ፥ 9 ለሰው ሁሉ የሚያበራ እውነተኛ ብርሃንስ ወደ አለም የመጣው ነው ይላል ። ዮሐ 5 ፥ 35 እሱ የሚነድና የሚያበራ መብራት ነው ይላል ። አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው እንዳለ ቤተክርስትያን ከጣራዋ እስከመሬቷ ሀሉም ሥርአቷን ያስተምራል ባህረ ጥበብ ቤተክርስትያን ፡፡ እየተናገረች ታስተምራለች ሳትናገርም ዝም.ብላም ታስተምራለች ። ክብር ለድንግል ማርያም ልጅ ለኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን ። አማላከ ቅዱሷን ቅድስት ቤተክርስትያንን ይጠብቅልን ። አሜን ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✝💚💛❤✝💚💛❤✝💚💛❤✝💚💛❤✝
Показати все...
✝የራማው ቅ/ገብርኤል አንተ ጠብቀኝ✝
✝መስቀል ሀይልነ✝
✝ለእናንተ ፕሮፋይል ፒክቸርስ✝
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.