uk
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Відкрити в Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Показати більше
1 810
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
Архів дописів
የእግዚአብሔር ቃል የእግዚአብሔር ቃል መልካም ነው የሰዎችን ሕይወት መልካም ያደርጋል 👉 ቃሉ እሳት ነው ከሕይወታችን መቀጠል ያለበትን ያቃጥላል። 👉 ቃሉ ሰይፍ ነው ከሕይወታችን መቆረጥ ያለበትን ይቆርጣል። 👉 ቃሉ መዶሻ ነው ከሕይወታችን ማድቀቅ ያለበትን ያደቃል። 👉 ቃሉ ወተት ነው ያሳድጋል። ✍ የእግዚአብሔር ቃል ሰባት ጊዜ ተፈትኖ እንዳለፈ ወርቅ ነው ሕይወታችንን ፍፁም ያደርጋል, ቃሉን አንብቡት አምሳ ጊዜ ቢተነቡት አምሳ አንደኛ መገለጥ አለው። 👉 ቃልህን እወደዋለሁ እግዚአብሔር ሆይ!!!!!!! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ታህሳስ 7/ 2013 #የእግዚአብሔር ልጆች ተዘጋጁ የመጨረሻው ዘመን: የመጨረሻው ዘመን ጥር ለአማኞች: እና የእግዚአብሔር መንግስት ምድር ለይ መጽናት በረከቶች..... #voice @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ዛሬ የተመለከትኩት ራዕይ አስገርሞኛል! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#የእግዚአብሔር_መንፈስ❤❤❤ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ ያለው: ትንቢት ልያናግረን እና ትልልቅ ተጽእኖ ፈጣሪ ሰዎች ልያደርገን ብቻ አይደለም: በዋናነት ዘላለማዊ የሆነውን እግዚአብሔራዊ ባሕርይ በመንፈሳችን እንደ ገና ለመስራት እና ክርስቶስን በእኛ ለመቅረጽ ነዉ። የእግዚአብሔር ልጆች መንፈስ ይህንን እንድያደርግ በእምነት ስትፈቅዱለት: ተዓምር ከውስጣችሁ ይወጣል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ስለዚህም በሚቻለኝ መጠን በሮሜ ላላችሁ ለእናንተ ደግሞ ወንጌልን ልሰብክ ተዘጋጅቼአለሁ።” — ሮሜ 1፥15 👉 አንዳንድ ሰው ሀገር ለቆ ለመውጣት ተዘጋጅቷል, እኛ ግን በመንፈስ ቅዱስ እሳት ምድርቱን ለመቆጣጠር ተዘጋጅተናል። 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ሰይጣን እየሰማ ይቃጠላል የሰው ልጅ ሰምቶት ይድናል ወንጌልም እንዳዘመርነው ምድርን ያሸንፋል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የመለኮቱ ባሕርይ ተካፋይ!???? ሃሌሉያ😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆😆 “ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ #ከመለኮት_ባሕርይ_ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን።” — 2ኛ ጴጥሮስ 1፥4 እኔ ይሄንን የመንፈስ ቅዱስ ቃል ባነበብኩ ቁጥር ሆዴን ህመም እስክሰማኝ ድረስ ነዉ: የምቃትተው! ሃሌሉያ! የእግዚአብሔር ልጆች ይህንን ከማር ይልቅ የሚጣፍጥ እና መንፈስና ነፍስን የሚያበራን ሰውነትን ደግሞ ፈጽሞ የሚለውጥን ቃል አሰላስሉ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በሕይወታችን ከለው ከእግዚአብሔር ዓላማ የሚበልጥ ነገር በምድር ለይ ምንም ያለም እርሱን ስታስቡ እረፍት ሊሰማቹ ይጋባል!!!! እግዚአብሔር ሆይ እወድሃለሁ!! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#Jesus_Noting_i_desire_compares_to_you! #You're blessed child of God. 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ᴊᴏʏ ɪs ʏᴏᴜʀ ᴘᴏƦᴛɪᴏɴ. ᴄʜɪʟᴅ ᴏғ ɢᴏᴅ ʏᴏᴜ ᴅᴇsᴇʀᴠᴇ ᴛᴏ ʙᴇ ᴊᴏʏғᴜʟʟ.

የደስታ ዘይት /the oil of Joy/ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯ “ጽድቅን ወደድህ ዓመፃንም ጠላህ፤ ስለዚህ ከባልንጀሮችህ ይልቅ እግዚአብሔር አምላክ የደስታ ዘይትን ቀባህ።” — መዝሙር 45:7 ምክንያት እና ውጤት ግልጽ በሆነ ቃል ተቀምጠዋል: "በደስታ ዘይት መቀባት" ውጤት ስሆን: "ጽድቅን መውደድ እና ዓመፃን መጥላት" ምክንያቱ ነዉ። 👉ጽድቅን መውደድ ማለት: በእግዚአብሔር ፊት ትክክል መሆንን እና ትክክል የሆነውን ነገር ሁሉ መውደድ ማለት ነዉ። ይህንን በእግዚአብሔር ፊት ትክክል መሆን ደግሞ: በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በለን እምነት አግኝተናል! ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን!!! ሃሌሉያ። ቃሉ በልባችን በቀጣይነት ስኖር: ደግሞ በእግዚአብሔር ፊት ትክክል የሆነውን ነገር እንወዳለን።ተወዳጆች ሆይ በእግዚአብሔር ፊት ትክክል በመሆናችን በሐሴት ዘይት ተቀብተናል! የማያቋርጥ ደስታ አለን: ዓለም የሌላት ሐሴት እኛ አለን። ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን: ከልባችን ስለማይናደው እና ስለማይሸረሸረው ሐሴት ሁልጊዜ እግዚአብሔርን ልናመሰግነው ይገባናል። የእግዚአብሔር ልጆች: በኢየሱስ ስም: የሚያገኛችሁ እና የምታገኙት የትኛውም ሰው: በዚህ የደስታ ዘይት ይበከላል!!! መኖር የሰለቸው ወንድማችሁ ቢሆን ወይም እህታችሁ እናንተን ካገኙ እና እጃችሁን ከጨበጡ በኃላ ከዚህ የደስታ ዘይት የተነሳ ተስፋ ውስጣቸው ይለመልማል! አሜን። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ከቤታችን ውጭ ላላችሁ ወንድሞቼ እና እህቶች ሁሉ የምጋብዘው: የመዝሙር ግብዣዬ ነዉ! አባታችን ይወደናል! ይወድሃል! ይወድሻል! #ና_ጌታ_ይወድሃል! -ሰላም ደስታ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።” — ማቴዎስ 5፥44-45 አባታችን ይህ ነዉ! "በክፎዎችና በበጎዎች ለይ ፀሐይን ያወጣልና: በጻድቃንና በኃጢአተኞች ለይ ዝናቡን ያዘንባል።" የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች: አሁን አንድ ነገር አድርጉ: የበደላችሁ ሰው ካለ: በእግዚአብሔር ርሕራሄ ይቅር በሉት! የበደላችሁትን ደግሞ ከልብ ይቅርታ ጠይቁ!* አሁኑን! እንዴት ካላችሁኝ: ስልካችሁ መልእክት መላኪያ ለይ "ይቅርታ" የሚል መልእክት በመጻፍ ላኩ! ይህንን ስታደርጉ: በሰማይ ያለ አባታችሁን ፈገግ ታሰኙታላችሁ! አሁኑኑ አድርጉት። ተባርካችኃል። @TheDeepThingsOfTheSpirit

ለሰዎች ሁሉ መልካም አድርጉ። እነሱ መልካምም ክፉም ቢሆኑ: የእነሱ ሁኔታ የእናንተን ማንነት እንዲቀይር አትፍቀዱ። ባላችሁበት መድረክ ሁሉ ለይ መልካሙን ገፀባህርይ በመምረጥ: በሰዎች ሁሉ ልብ መልካም ዘር ዝሩ። ይህንን የምታደርጉት መልካም ፍሬ ለመሰብሰብ በማሰብ ብቻ አይደለም! ዋናውና ትልቁ ምክንያት: በዳግም ልደት ከወለደን ከአምላክ የተካፈልነዉ ባሕርይ መሆኑ ነዉ። ማንነታችን ነዉ። ሰዎች ምንም ልያደርጉባችሁ ይችላሉ: እናንተ ግን የራሳችሁን ቦታ አትልቀቁ። መልካም ማድረጋችሁን ቀጥሉ: ይህ ማለት ግን እንዲጎዷችሁ ፍቀዱ ማለት አይደለም: በእግዚአብሔር ሰላም እና ደስታ ራሳችሁን የምትጠብቁበት ጥበብ ይኑራችሁ። ይህንን ስታደርጉ በሕይወት መንገድ እየሄዳችሁ እንደሆነ እርግጠኛ መሆን ትችላላችሁ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

-ከሰማይ የመጣ የውዴ ቃል -Azeb hailu 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#በማያቋርጥ_ሐሴት_ውስጥ_መኖር! 👉የማያቋርጥ እና በምንም አይነት መልኩ ሰይጣንም ሆነ ሰው ልነጥቃችሁ የማይችል: የደስታ አይነት እንዳለ ታውቃላችሁ? ከደስታ ጋር በተያያዘ ሦስት ቃላትን ጠቅሰን ምን አይነት እንደሆነ ልንመለከት እንችላለን። መጽሐፍ ቅዱስ ለይ አብዛኞቹ የአማርኛ ቅጂዎች እንዚህን ሦስት የመለየት ስር በይሰሩም በዋናው ጽሑፍ ግን የተለያዩ ናቸዉ። ሦሶቱንም እንመልከታቸው። 1-ተድላ : ይህ ቃል በእንግሊዝኛው ቅጂ /Pleasure/ ተብሎ ተተርጉሟል። ይህ #በስጋችሁ ለይ ያለ እና በቀጥታ ከስጋችሁ ጋር የተገናኘ የደስታ አይነት ነዉ። ለምሳሌ ጥሩ መብል ስትባሉ ወይም ስትጠጡ ወይም ስትለብሱ...ወዘተ የሚመጣ ነዉ። በውጫዊ ነገር ለይ የተደገፈ በመሆኑ ከነገሮች ጋር የሚሄድ እና የሚመጣ ነዉ። ይህ ድብን ያሉ ፍጥረታዊ ሰዎች ያሉበት የደስታ ክልል ነዉ። አንዳንድ ፍጥረታዊ ክርስቲያኖችም በዚህ ደረጃ ለይ ሊሆኑ ይችላሉ: ግን #እንዲያድጉ ያስፈልጋል። 2- ደስታ: ይህ ቃል በእንግሊዝኛ /Happiness/ ተብሎ ሊተሮገም ይችላል። ይህ የደስታ አይነት በሰዎች ነፍስ(ኔፌሽ) ለይ ያሚፈጠር ነዉ። የሚፈጠር ነዉ የሚለው ቃል እራሱ ስለዚህ የደስታ አይነት ብዙ ይላል! ይህ ደስታ የሚፈጠረው: አንድ ደስ የሚያሰኝ ነገር ስሆን ነዉ። Happiness comes when something good happens to your soul. Happiness ከሚለው ቃል አንድ ነገር happen ስያደርግ የሚፈጠር የደስታ አይነት ነዉ። ክርስቲያኖች በዚህ የደስታ ደረጃ ለይ አይደሉም! በዚህ የደስታ አይነት የሚኖር ሰው: ከጠዋት ደስተኛ ከሰዓት ደግሞ በሐዘን የተመታ ልሆን ይችላል: ምክንያቱም ደስታው የተደገፈው በነገሮች መሆን እና አለመሆን ለይ ነዉ። ለዚህ ነዉ አንዳንድ ብዙ የምታውቋቸው ሰዎች: በየሰዓቱ ስሜታቸው የሚቀያየረው። የእግዚአብሔርን እውነት አለማወቅ ይገድላል። 3-ሐሴት: የመጨረሻው እና ፍጹም የሆነው የደስታ አይነት ሐሴት /JOY / ይባላል። ይህ ደግም በተወለዱ: ክርስትያኖች ሁሉ መንፈስ ውስጥ: ከመንፈስ ቅዱስ መሰጠት ጋር ለአማኙ መንፈስ የተሰጠ እና በአማኙ መንፈስ ውስጥ #ሁልጊዜ የሚኖር ነዉ። ሁልጊዜ ማለት ሁልጊዜ ነዉ!😁 በቀንም በማታም በሸለቆም በተራራም: ብንከበብም ብቻችንን ስንሆንም: ስንወደድም ስንጠላም: ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡ ! 😆😆 ሃሌሉያያያያያያያያያያ! በጽሑፍ መጮህ ከተቻለ ብዬ ነዉ🤔 ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን። ሐሴት የእግዚአብሔር የደስታ አይነት ነዉ! እግዚአብሔር በሐሴት የሚኖር አምላክ ነዉ: እኛም ልጆች በዚህ ሐሴት እንድንኖር መንፈሱን ሰጥቶናል! ሐሴት ግን መንፈሳችን ለይ ነዉ ያለው: ስለዚህ ነፍሳችንን ለመንፈሳችን እንድትገዛ በማድረግ: ወደ ነፍሳችን ከዛም ወደ ስጋችን እንዲፈስ ማድረግ ይኖርብናል! ይህ እውነት ነዉ! አንድ አማኝ ሰው በማያቋርጥ ሐሴት ውስጥ መኖር ይችላል! መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ውስጥ እስካለ ድረስ ሐሴት በመንፈሳችሁ አለ! ሃሌሉያ! በመጨረሻ: ታድያ ክርስቲያኖች ለምንድነው በዚህ ሐሴት የማይኖሩት? ብላችሁ ከጠየቃችሁኝ: መልሴ የሚሆነው "አለማወቅ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይገድለዋል" ነዉ። #የማን እና #ማን እንደሆናችሁ እወቁ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ስለ ወጀብ እግዚአብሔርን ላማስግን!🤔 በሚወዛወዝ ባህር ውስጥ የተደላደለ አለት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለይ ብቻ ጸንቼ እንድቆም የበለጠ ስላበቁኝ ወጀቦች አምላኬን አመሰግናለሁ!😁 👉የእግዚአብሔር ልጆች እውነትን ስታውቁ እና በእውነት ስትኖሩ የሚያሰጋችሁ የለም! #በእግዚአብሔር ቃል ለይ ተተከሉ! @TheDeepThingsOfTheSpirit

#የእግዚአብሔርን_ቃል_በልባችን_እንያዝ! ኤርምያስ 8 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁸ እናንተስ፦ ጥበበኞች ነን የእግዚአብሔርም ሕግ ከእኛ ጋር ነው እንዴት ትላላችሁ? እነሆ፥ የጸሐፊ ብርዕ ሐሰተኛ ነው በሐሰትም አድርጎአል። ⁹ ጥበበኞች አፍረዋል ደንግጠውማል ተማርከውማል፤ እነሆ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ጥለዋል፤ ምን ዓይነት ጥበብ አላቸው? ¹⁰ ከታናሹ ጀምሮ እስከ ታላቁ ድረስ ሁሉ ስስትን ያስባሉና፥ ከነቢዩም ጀምሮ እስከ ካህኑ ድረስ ሁሉ በተንኰል ያደርጋሉና.. 👉የጸሐፊ ብዕር ሐሰተኛ ነዉ: በሐሰትም አድርጓል። 👉ጥበበኞች አፍረዋል ደንግጠውማል: ተማርከውማል። 👉ከታናሹ ጀምሮ እስከ ታላቁ ሁሉም ስስትን ወይም ያልተገባ ጥቅምን ያስባሉ። 👉ከነብዩ ጀምሮ እስከ ካህኑ በተንኮል ያደርጋሉ። #ለምን? ምክንያቱም የእግዚአብሔርን ቃል ጥለዋልና። ጥበባቸውስ ምን አይነት ነዉ!? 👉የእግዚአብሔር ቃል የሌለው: አገልጋይም ቢሆን አማኝ: እግዚአብሔርን ይበድላል! ሆኖም የእግዚአብሔር ህግ አለኝ እያለ ራሱንም የሚሰሙትንም ያስታል። #አገልጋይ ለመሆን የምትወዱ: በትጋት #ቃሉን_አግኙ! ሌሎች ነገሮች ሁለ የሚከተሉ እና የቃሉ ወጤቶች ናቸዉ። “የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ..” — ቆላስይስ 3፥16 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#በራስ_ለይ_ማዋል! ተስፋ አትቁረጡ። ዛሬ ያላችሁበት ነገ የምትኖሩበት አይደለም: ነገር ግን ነገ የምትሆኑት ዛሬ በምታደርጉት ለይ የተደገፈ እንደሆነ አትርሱ። (🐛.......................................🦋) 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit