TheDeepThingsOfGod
Відкрити в Telegram
Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!
Показати більше1 810
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
Архів дописів
1 810
....ፀጋ ማለት ምን ማለት ነዉ....
👉ፀጋ የቃሉ ትርጉም "በሰጪው ማንነት ላይ የተመሰረተ ነጻ ስጦታ" ማለት ነዉ። አንዳንድ ሰዎች ስለ ፀጋ ጠበብ ያለ አመለካከት አላቸው: "ደህንነት" ብቻ ፀጋ የሚመስላቸው ሰዎች አሉ: ነገር ግን ከእግዚአብሔር ለሰው ልጅ የሚሰጥ ነገር ሁሉ ፀጋ ነዉ! ምክንያቱም ፀጋ በእግዚአብሔር ማንነት ላይ የተመሰረተ ነጻ ስጦታ ማለት ስለሆነ። ፀጋ "ደህንነት" ብቻ ቢሆን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "ፀጋ ይብዛላችሁ" የሚል ሃረግ በተደጋጋሚ አናገኝም ነበር: አሁንም ማስተዋል ያለብን: እግዚአብሔር አድስ የሚሰጠን ነገር አለ ማለት አይደለም! ክርስቶስን ሲሰጠን ሁሉ በእርሱ ተሰጥቶናል! መጽሐፍ "ክርስቶስ ሁሉ ነዉ በሁሉ ነው!" እንደሚል አስተውሉ። ነገር ግን እግዚአብሔር በክርስቶስ ሁሉን ቢሰጠንም የተሰጠንን የምንቀበልበት ደረጃ: ክርስቶስን ከምናውቅበት ደረጃ ጋር እኩል ነዉ። ለዚህ ነዉ: ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ፀጋ ስለምበዛልን መንገድ ሲነግረን “... በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።” ያለው።
— 2ኛ ጴጥሮስ 1፥2-3....
አብ ክርስቶስን ስሰጠን ሁሉን ከእርሱ ጋር ሰጥቶናል! ነገር ግን የተሰጠንን የምንቀበልበት እግዚአብሔር የዘረጋው ስርዓት( SYSTEM) እግዚአብሔርን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ማወቅ ነዉ።
ፀጋ ይብዛላችሁ! የምለው ለዚህ ነዉ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️ወንድም ዮሴፍ ይባላል: አገልጋይ ነዉ: እግዚአብሔር በዚህ ቻናል ተጠቅሞ ሙሉ በሙሉ ሕይወቱን እንደለወጠው ስነግረኝ ስሰማ እጅግ በጣም ጌታን አመሰገንኩት: በinbox ብዙ ነገር ነግሮኛል: ምን ማለት እችላለሁ: ክብር ለንጉሡ ይሁን! እርሱ አገልጋይ እንደመሆኑ እዚህ በተከፋለው ፀጋና ቃል ስንቶች እንደሚለወጡ ሰስብ ደግሞ ሺዎች እየተለወጡ እንደሆነ አስተውላለሁ! ክብር ለመንፈስ ቅዱስ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
International ብለን....በአማሪኛ ብቻ የምንሰብክበት ዘመን ማብቃት አለበት😂😂🔥
U're blessed, friends!
1 810
Praying in unknown tongues!
the secret of Apostle Pauls success in life and ministry!!🔥🔥
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ኢያንዳንዱ ደቀመዝሙር ከመምህሩ ጋር ግላዊ የሆነ ሕብረት ሊኖረው የግድ ነዉ: ይህ ከልሆነ ግን በሁለቱ መካከል የመምህር እና የደቀመዝሙር ግንኙነት የለም ማለት ነዉ።
Every disciple must have a personal fellowship with his teacher. If not, it means the two doesn't have a teacher-disciple relationship.
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
...ንቃ.....ተነሣ.....ክርስቶስም... ያበራልሃል...
“ስለዚህ፦ አንተ #የምትተኛ_ንቃ #ከሙታንም_ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል።”
— ኤፌሶን 5፥14
ሐዋሪያው #ከእንቅልፍ_ንቃ #ከሙታን_ተነሳ የሚለው #በክርስቶስ_አምኖ_ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለን ነገር ግን በጊዜ ሂደት በእምነቱ ደክሞ የተኛን ከዛም ስከፋ የሞተን ሰው ነዉ። አንዳንዱ ሰው እንቅልፍ ላይ ነዉ: ሕይወት በውስጡ ቢኖሪም መንፈሳዊ ተግባር ግን አቁሟል: ከዚህ የከፋው ደግሞ ጨርሶ በመንፈሳዊ ሕይወቱ ሞቷል: ከሕይወት ምንጫቸው ተለያይተዋል: ቢሆንም ሐዋሪያዉ መውጫ አለ ይላቸዋል: ይህም "ንቃ" "ተነስ" ነዉ። አንተ ራስህ በልብህ ፈቃድ ተነስ: የዛኔ ክርስቶስ ያበራልሃል: ይላል። ከእንቅልፍ መንቃት ያስፈልግህ/ያስፈልግሽ ይሆንን? ከሙታን መነሳትስ??? ያለማንቀላፋት እና ያለመሞት ምልክቱ እሁድና እሮብ ቤተክርስቲያን መሄድ አይደለም! አንድ ሰው: ቤተክርስቲያን እየተመላለሰ አስራት እየከፈለ: በማህበር እያገለገለ: ነገር ግን አሁንም የኃጢአት ባሪያ ከሆነ መንቃት/ መነሳት ያስፈልገዋል! የተለያየ የኃጢአት ልምምድ ውስጥ ሆኖ እኔ አላንቀላፋሁም! በእግዚአብሔር ሕይወት ነኝ! ካለ ራሱን እያሳተ ነዉ! መፍትሔ የሚሆነው ራስን ማታለል ሰይሆን: መንቃት እና መነሳት ነዉ! የክርስቶስን ፍጹም ብርሃን መፈለግ ነዉ።
እጅግ በጣም ብዙ ቀጥር ያላቸው የቤተክርስቲያን ልጆች: የኃጢአት ልምምዶች ባሪያ ሆነው: የዓለም እና የሰይጣን ተጠቂ መሆናቸውን ብዙ ጊዜ እሰማለሁ: መንፈስ ቅዱስ አይከሳቸውም! ነገር ግን ወዳጅ ወዳጁን እንደሚወቅስ ይወቅሳቸዋል! ምክንያቱም ከኃጢአት በላይ ለመሆን የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ ሰጥቶናል! ነገር ግን "አለማወቅ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይገድለዋል" ....በፍጹም ደግም የተወለደን ሰው ኃጢአት ባሪያው አድርጎ መግዛት አይችልም! የእግዚአብሔር ዘር በእርሱ ይኖራልና! ነገር ግን አሁንም አልረፈደም "ንቁ" "ተነሱ" ይላል የእግዚአብሔር መንፈስ! ይህንን ደግሞ ማድረግ እንችላለን: የማንችለውን ነገር አድርጉ አይለንምና!
ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ!!!
👇👇👇👇ተቀላቀሉን👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Time to wake up!
Time to get deeper into the word of God!
Time to pray and fast!
Time to fellowship with the holy Spirit!
Time to live above sin, the world and death!
Time to live in the consciousness of Christ In Us!
Time to live in holiness!
Time to walk in love!
Time to transfigure!
Time to move in the power of the spirit!
Time To prepare for the rapture!
Time to prepare to meet the bridegroom!
👇👇👇 join the chariot👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Revival የሚለው ቃል በአማርኛ መዝገበ ቃላት አቻ ቃል የሌለው የእንግሊዝኛ ቃል ነዉ። ነገር ግን ፍቺው "ወደ ሕይወት መመለስ" ነዉ።
Revival - means "bringing back to life."
ታድያ በክርስቶስ የመነ ሰው ወደ ሕይወት መመለስ የሚያስፈልገው ጊዜ አለ ወይ? አዎ በሚገባ!!
“ስለዚህ፦ አንተ የምትተኛ ንቃ #ከሙታንም_ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል።”
— ኤፌሶን 5፥14
ሐዋሪያው "ከሙታን ተነሣ" ያለው በክርስቶስ አምኖ ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለን ሰው ነዉ። የመልእክቱ መጀመሪያ ላይ "በኤፌሶን ላለች #ቤተክርስቲያን" የሚለውን አንብቡት። "ከሙታን ተነሳ" የሚለው በሕይወት ላለ ሰው እንዳልሆነ ግልጽ ነዉ። ይህ ስጋዊ ሞት አይደለም: መንፈሳዊ ሞት ነዉ: ከማንቀላፋትም በላይ ነዉ። ምክንያቱም ሐዋሪያው "የምትተኛ ንቃ" ብሎ አልጨረሰም "ከሙታንም ተነሳ" ይላል። ይሄ ነዉ "ወደ ሕይወት መመለስ" ማለት( Revival)
አሁን ባለንበት ወቅት ደግሞ እጅግ ብዙ ቁጥር ያለው የአካል ብልት ወደ ሕይወት መመለስ አለበት! ሕይወት ማነው? ክርስቶስ ነዉ። መንፈስ ቅዱስ ስመጣ "የመጀመሪያው የሚያደርገው ወደ ሕይወት ነዉ የሚመልሰው" ይህ ማለት አማኙን ወደ ክርስቶስ ነዉ የሚመልሰው!
በዚህ ዘመን መንፈስ ቅዱስ ወደ ሕይወት የመለሳቸው አማኞችም እንዳሉ ማወቅ አለብን! እነዚህ ለመንፈስ ቅዱስ ራሳቸውን የሰጡ ናቸዉ: ክርስቶስን እንደ ብዙሃኑ የሚያውቁት የስነ መለኮት መምህር የጻፈውን ትንተና አጥነተው ሳይሆን #በልምምድ ነዉ! በመንፈስ ቅዱስ #መገለጥ ነዉ! ክርስቶስን የሚያውቁት በሕይወት ነዉ! ራሱን በመንፈሱ ገልጦላቸው ነው! ማወቅ ያለብን ነገር ደግም የተወለደ የእግዚአብሔር ልጅ ሁሉ ክርስቶስን በሕይወት ለማወቅ ይችላል።
በሕይወት የመኖራችን መረጋገጫ ምንድነው? የመጀመሪያው በሕይወት ያለ ነገር ሁሉ #ያድጋል! #ይበዛል! #ይገዛል! #ድምፅ_አለው! #ሕይወቱንም_ይገልጣል!
ስለዚህ አሁን በምንነጋገረው አግባብ: ወደ ሕይወት የተመለሰ አማኝ ግልጽ የሆነ ምልክት አለው: ይህም #በእግዚአብሔር_ሕይወት ማደግ #መብዛት #መግዛት (ከኃጢአት ከዓለም እና ከሰይጣን በላይ መሆን) #የእግዚአብሔርን_ድምፅ_መስጠት #ክርስቶስን_መገለጥ ነዉ። አንድ አማኝ በእግዚአብሔር ሕይወት እያደገ ከልሆነ: እየበዛ እና እየገዛ ካልሆነ ...እግዚአብሔርን መስማት እና ላለበት ዓለም ድምፅ መስጠት የማይችል ከሆነ...ክርስቶስን የሚገለጥ ሕይወት እየኖረ ካልሆነ....የለምንም ጥያቄ #ተሃድሶ ሰይሆን "ከሙታን መነሳት እና ወደ ሕይወት መመለስ" ነዉ የሚገባው።
ስለዚህ እጅግ በጣም ብዙ ወደ ሕይወት መመለስ ያለባቸው አማኞች አሉ! ምንም ክርስቶስን የሚገልጥ ሕይወት የሌላቸው ነገር ግን አፋቸውን ከፍተው ወደ ሕይወት መመለስ አያስፈልገንም (Revival አያስፈልገንም) በይሉም: እንደዛ ለማለት የሚወዱ ብዙ ናቸው። እንደዚህ የምታስቡ ወንድሞች እና እህቶች: እባካችሁ አትሳቱ! ከአእምሮ ቀመር ውጡና በመንፈስ ቅዱስ ለመመራት የተዘጋጀ ልብ ይኑራችሁ: እምቢ የምትሉ ብሆን እንኳ እግዚአብሔር በተሰጡት ይሰራል! አንድነታችን ግን ደስ ያሰኘዋል!
👉ተሃድሶ እየተባለ ዘመናት ያልቁ ይሆናል እንጅ የሰው ልጅ መንፈስ ቅዱስ ከልሰራበት ማደስ በፍጹም አይችልም!
“...በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።”
— ዘካርያስ 4፥6....ተሃድሶን የሚያመጣው ሕይወትን የሚሰጠው መንፈስ ቅዱስ ብቻ ነዉ! ይሄ ስራ መጽሐፍ በመጻፍ ብቻ የሚሰራ ስራ አይደለም! በፍቅርና በአንድነት የእግዚአብሔር መንፈስ በእኛ እንድሰራ በመፍቀድ የሚመጣ ለውጥ ነዉ።
በሕይወታችሁ ሪቫይቫል እንድሆን የምትጸልዩ ወንድሞች: በየቀኑ መንፈስ ቅዱስ የክርስቶስን መልክ በእናንተ እንዲቀርጽ እየጸለያቹ: ወደፊት እና ወደ ላይ ብቻ! የእግዚአብሔር ብርሃን ስመጣላችሁ ተነስታችሁ አብሩ! አስተውሉ ሪቫይቫል በግል ሕይወት: በማህበር ደረጃ እና በሃገር ደረጃ ልሆን ይችላል! በግል ሕይወታችሁ ሪቫይቫል የሆነ እና በእግዚአብሔር ሕይወት እያደረጋችሁና እየበዛችሁ ከኃጢአት ከዓለም እና ከሰይጣን በላይ የሆነ ነሮ እየኖራችሁ ክርስቶስ በእናንተ እየተገለጠ ከሆነ: ሌሎችንም እርዱ! የእግዚአብሔርን እውነት አውሩ! ለሰዎች ሁሉ ወንጌልን ስበኩ! የተሰጣችሁን ተግባር ለመፈጸም ትጉ! በእናንተ የጀመረው: እየበዛ እና እየገዛ ብዙዎችን ወደ ሕይወት ይመልሳል!
ኢየሱስን የሚያከብረው: ቤተክርስቲያንን የሚያንጸው እና የማያምኑትን በመውቀስ ወደ እምነት የሚመልሳቸው መንፈስ ቅዱስ ብቻና ብቻ ነዉ!!
ይህ ደግሞ በዘመናችን ይሆናል! አሜን!
👇👇👇👇👇ተቀላቀሉን👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ከተሃድሶ( Reformation) ወደ ሕይወት መመለስ( Revival ) አይቀድምም??
👉በመሰረቱ Revival ማለት "መነቃቃት" ማለት አይደለም! ይሄ የ Revival ጠላቶች የሆኑ አንዳንድ ቡድኖች የሰጡት ትርጉም ነዉ: ይህም Revivalን ለማቅለል ያለመ ነዉ። የሆነው ሆኖ Revival ማለት "Bringing back to life" በአማሪኛ "ወደ ሕይወት መመለስ" ማለት ነዉ። ተሃድሶ (Reformation) ደግሞ "ማደስ" ማለት ነዉ: እንዲያው ቃሉን በጣም ከለጠጥነው "እንደገና ማበጀት" ይሆናል: በተለያየ ምክንያት የቀደመ መልኩን የለቀቀን ነገር መልሶ ወደ ቀደመ መልኩ መመለስ ማለት ነዉ። ወደ ሕይወት ከመመለስ እና ወደ ቀደመው መልክ ከመመለስ የትኛው እንደሚቀድም ሕፃን እንኳ የሚያስተውለው ነዉ። ቤተክርስቲያን ከመታደሷ(Reformation) በፊት ወደ ሕይወት መመለስ(Revival) ያስፈልጋታል። በሕይወት መኖር ከመታደስ ይቀድማልና!
ወደ ሕይወት የሚመልሰን( revive የሚያደርገን) የሚያድሰንም(Reform) የእግዚአብሔር መንፈስ ብቻ ነዉ። በጣም ደስ የሚለው እኔ የማወራው የመሰለኝን አይደለም! መጽሐፍ ቅዱስ የሚለውን ነዉ: መጽሐፍ ቅዱስ ከተሃድሶ የሚቀድመው መፈጠር (ሕይወት ማግኘት) ነዉ ይላል!
“መንፈስህን ትልካለህ ይፈጠራሉም፥ የምድርንም ፊት ታድሳለህ።”
— መዝሙር 104፥30
መንፈስ ቅዱስ ስመጣ የሚያደርገው የመጀመሪያው ተግባር መፍጠር እና ሕይወትን መስጠት("Revive" ማድረግ) ነዉ:
“የእግዚአብሔር መንፈስ #ፈጠረኝ፥ ሁሉንም የሚችል የአምላክ እስትንፋስ #ሕይወት ሰጠኝ።”
— ኢዮብ 33፥4....በመቀጠልም በጊዜ ሕደት ነገሮች የቀደመ መልካቸውን የሚለቁ ከሆነ: ደግሞ "ያድሳቸዋል"( Reform ያደርጋል")።
ተሃድሶ ያስፈልጋል ወይ? ጥያቄ የለውም! ነገር ግን ከተሃድሶ ቀድሞ ወደ ሕይወት መመለስ( Revival) ያስፈልጋል!
ተሃድሶ ተሃድሶ እያሉ በራሳቸው ድምጽ የሚጮሁ ሰዎች: መረዳት ያለባቸው ነገር በፍጹም እነርሱ በራሳቸው ቤተክርስቲያንን ለማደስ ብቁ አለመሆናቸውን ነዉ! ይህንን መድረግ የሚችለው መንፈስ ቅዱስ ብቻ ነዉ: የእኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ትንተናዎች: በፍጹም ቤተክርስቲያንን ለማደስ የበቁ አይሆኑም! ይህንን ስራ መስራት የተገባው መንፈስ ቅዱስ ነዉ። በ ጴንጤቆስጤ ቀን በቅዱሳን ሐዋርያት ላይ የወረደው የእግዚአብሔር መንፈስ በዓለም ላይ ያሉ ሰዎች ሁሉ ቢጮሁ የማይፈጥሩት ድምጽ ይዞ ነበር የወረደው: ሐዋርያቱ ሰይጣሯቸው ሰዎች የተሰበሰቡት ለዚሁ ነበር! Revival ሰዎች የሚጮሁበት ሳይሆን መንፈስ ቅዱስ ድምፅ የሚፈጥርበት ነዉ። እራሳቸውን "ተሃድሶዊ" ነኝ ብለው የሚጠሩ የተለያዩ ወንድሞች አግኝቻለሁ: መጽሐፍ ቅዱስን ቃል በቃል ተንታኝ አድርገው ራሳቸውን ማቅረባቸው ስደንቀኝ: አብዛኞቹ ለይ ያስተዋልኩት መንፈሳዊ በሽታ አለ: አንድ ሰዓት እንኳ መጸለይ የማይወዱ: መጾም የማያውቁ: ከእነርሱ ቡድን ውጭ የሆነን ሰው የሚንቁ እና ፍቅር የሌላቸው እና አንድነትን የማይወዱ ናቸው! ሁሉም ማለቴ አይደለም! እኔ ያገኘኋቸው አብዛኞቹ። ይህ በግልጽ የሚያሳየው: በሕይወት እንደሌሉ ነዉ! ይህ የክርስቶስ መንፈስ አይደለም! አንድ የማልረሳውን ልንገራችሁ: "ተሃድሶዊ" ነኝ ብሎ እራሱን የሚጠሩ: ከአንድ ወንድሜ ጋር በመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዙሪያ ስንወያይ: እኔ እንደዚህ አልኩት "መጽሐፍ ቅዱስ መጠናት ያለበት በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ብቻ ነዉ"....እርሱ ግን እንደዚህ በማለት መለሰልኝ " መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ብቻ ነዉ የሚጠናው የምትለው ንግግርህ መጽሐፍ ቅዱስን በአእምሮ ለለማጥናት የሚቀርብ መከላከያ ነዉ" አለኝ። በጣም ነዉ: የሚያሳዝነው መጽሐፍ ቅዱስ "በአእምሮ ነዉ መጠናት ያለበት" ብሎ የሚያምን ነዉ እንግዲህ። ፀጋ ይብዛላቸው!
ተሃድሶ ሰዎች የሚሰሩት ስራ አይደለም! ተሃድሶ ሕይወትን የሚሰጥ (revive የሚያደርግ) መንፈስ የሚሰራው ስራ ነዉ። አትሳቱ: የእግዚአብሔር መንፈስ ነዉ የሚያስፈልገን እንጅ ምንም መንፈስ የሌለው እና መጽሐፍ ቅዱስን በ አመክንዮ የሚተረጉሙ መደዴ አይደለም! እንደዛ ካሉ ወንድሞች አንድ ጓደኛ ያዙና ለአንድ ስምንት ተመልከቱት! የክርስቶስ መንፈስ እንደሚያስፈልገው በግልጽ ይታያችኋል!
Revival እንድሆን የምትጸልዩ የምታለቅሱ: የእግዚአብሔር ልጆች ትጋታችሁን ቀጥሉ! የእግዚአብሔርን ቃል ከዋቢ መጽሐፍት ሰይሆን ከመንፈስ ቅዱስ ተማሩ! እንደዚህ እያደረጋችሁ መሰደብ ክብር ነዉ! መናቅ ሞገስ ነዉ! ብቻ ልባችሁም እጃችሁም ንጹሕ ይሁን እግዚአብሔር በእናንተ የሚሰራውን ፍጥረት ሁሉ ይመለከተዋል! በምድር ላይ ያለ ሰው ሁሉ ወደ እውነት እና ወደ ሃይል ይመለሳል ብላችሁ አታስቡ! እግዚአብሔር ግን ለእናንተ የሰጣችሁን ተግባር ፈጽሙ! በመንፈስ ቅዱስ እየተመራችሁ እና የጽድቅን ፍሬ እያፈራችሁ በክርስቶስ ፍቅር ኑሩ! ያየነውን እና የሰማነውን እንናገራለን!!! እግዚአብሔር በዚህ በዘመን መጨረሻ የሚሰራው ትልቅ ስራ አለ!
የየትኛውም ቡድን ነኝ ከሚል ነገር ግን የክርስቶስ መንፈስ ከሌለው ሰው ራቁ: የክርስቶስ መንፈስ ትሁት! እውነተኛ! ፍቅር! በወንድሞች መካከል አንድነትን የሚያመጣ ነዉ!
Revival ይሆናል! ይህ ስሆን ነገሮች ሁሉ ውብ ይሆናሉ! ምክንያቱም ሰሪው እግዚአብሔር ከሆነ የሚሰራውን ሁሉ ውብ አድርጎ ነዉ የሚሰራው!
#ፀጋ_ይብዛልን!
👇👇👇👇ተቀላቀሉን👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ከተሃድሶ( Reformation) ወደ ሕይወት መመለስ( Revival ) አይቀድምም??
👉በመሰረቱ Revival ማለት "መነቃቃት" ማለት አይደለም! ይሄ የ Revival ድብቅ ጠላቶች የሆኑ አንዳንድ ቡድኖች የሰጡት ትርጉም ነዉ: ይህም Revivalን ለማቅለል ያለመ ነዉ። የሆነው ሆኖ Revival ማለት "Bringing back to life" በአማሪኛ "ወደ ሕይወት መመለስ" ማለት ነዉ። ተሃድሶ (Reformation) ደግሞ "ማደስ" ማለት ነዉ: እንዲያው ቃሉን በጣም ከለጠጥነው "እንደገና ማበጀት" ይሆናል: በተለያየ ምክንያት የቀደመ መልኩን የለቀቀን ነገር መልሶ ወደ ቀደመ መልኩ መመለስ ማለት ነዉ። ወደ ሕይወት ከመመለስ እና ወደ ቀደመው መልክ ከመመለስ የትኛው እንደሚቀድም ሕፃን እንኳ የሚያስተውለው ነዉ። ቤተክርስቲያን ከመታደሷ(Reformation) በፊት ወደ ሕይወት መመለስ(Revival) ያስፈልጋታል። በሕይወት መኖር ከመታደስ ይቀድማልና!
ወደ ሕይወት የሚመልሰን( revive የሚያደርገን) የሚያድሰንም(Reform) የእግዚአብሔር መንፈስ ብቻ ነዉ። በጣም ደስ የሚለው እኔ የማወራው የመሰለኝን አይደለም! መጽሐፍ ቅዱስ የሚለውን ነዉ: መጽሐፍ ቅዱስ ከተሃድሶ የሚቀድመው መፈጠር (ሕይወት ማግኘት) ነዉ ይላል!
“መንፈስህን ትልካለህ ይፈጠራሉም፥ የምድርንም ፊት ታድሳለህ።”
— መዝሙር 104፥30
መንፈስ ቅዱስ ስመጣ የሚያደርገው የመጀመሪያው ተግባር መፍጠር እና ሕይወትን መስጠት("Revive" ማድረግ) ነዉ:
“የእግዚአብሔር መንፈስ #ፈጠረኝ፥ ሁሉንም የሚችል የአምላክ እስትንፋስ #ሕይወት ሰጠኝ።”
— ኢዮብ 33፥4....በመቀጠልም በጊዜ ሕደት ነገሮች የቀደመ መልካቸውን የሚለቁ ከሆነ: ደግሞ "ያድሳቸዋል"( Reform ያደርጋል")።
ተሃድሶ ያስፈልጋል ወይ? ጥያቄ የለውም! ነገር ግን ከተሃድሶ ቀድሞ ወደ ሕይወት መመለስ( Revival) ያስፈልጋል!
ተሃድሶ ተሃድሶ እያሉ በራሳቸው ድምጽ የሚጮሁ ሰዎች: መረዳት ያለባቸው ነገር በፍጹም እነርሱ በራሳቸው ቤተክርስቲያንን ለማደስ ብቁ አለመሆናቸውን ነዉ! ይህንን መድረግ የሚችለው መንፈስ ቅዱስ ብቻ ነዉ: የእኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ትንተናዎች: በፍጹም ቤተክርስቲያንን ለማደስ የበቁ አይሆኑም! ይህንን ስራ መስራት የተገባው መንፈስ ቅዱስ ነዉ። በ ጴንጤቆስጤ ቀን በቅዱሳን ሐዋርያት ላይ የወረደው የእግዚአብሔር መንፈስ በዓለም ላይ ያሉ ሰዎች ሁሉ ቢጮሁ የማይፈጥሩት ድምጽ ይዞ ነበር የወረደው: ሐዋርያቱ ሰይጣሯቸው ሰዎች የተሰበሰቡት ለዚሁ ነበር! Revival ሰዎች የሚጮሁበት ሳይሆን መንፈስ ቅዱስ ድምፅ የሚፈጥርበት ነዉ። እራሳቸውን "ተሃድሶዊ" ነኝ ብለው የሚጠሩ የተለያዩ ወንድሞች አግኝቻለሁ አባቶቻቸው እንደእነርሱ እንዳልነበሩ አምናለሁ! በተሃድሶዊያን ትምህርት እየተወለዱ ያሉ ልጆችን ሳይ በትምህርቶቹ ላይ ያለኝ ጥያቄ ከፍ ብሏል! እነኝህ ልጆች መንፈስ የሌላቸው ሆነው: መጽሐፍ ቅዱስን ቃል በቃል ተንታኝ አድርገው ራሳቸውን መቅረባቸው ስደንቀኝ: አብዛኞቹ ለይ ያስተዋልኩት መንፈሳዊ በሽታ አለ: አንድ ሰዓት እንኳ መጸለይ የማይወዱ: መጾም የማያውቁ: ከእነርሱ ቡድን ውጭ የሆነን ሰው የሚንቁ እና ፍቅር የሌላቸው እና አንድነትን የማይወዱ ናቸው! ሁሉም ማለቴ አይደለም! እኔ ያገኘኋቸው አብዛኞቹ። ይህ በግልጽ የሚያሳየው: በሕይወት እንደሌሉ ነዉ! ይህ የክርስቶስ መንፈስ አይደለም! አንድ የማልረሳውን ልንገራችሁ: "ተሃድሶዊ" ነኝ ብሎ እራሱን የሚጠሩ: ከአንድ ወንድሜ ጋር በመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዙሪያ ስንወያይ: እኔ እንደዚህ አልኩት "መጽሐፍ ቅዱስ መጠናት ያለበት በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ብቻ ነዉ"....እርሱ ግን እንደዚህ በማለት መለሰልኝ " መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ብቻ ነዉ የሚጠናው የምትለው ንግግርህ መጽሐፍ ቅዱስን በአእምሮ ለለማጥናት የሚቀርብ መከላከያ ነዉ" አለኝ። በጣም ነዉ: የሚያሳዝነው መጽሐፍ ቅዱስ "በአእምሮ ነዉ መጠናት ያለበት" ብሎ የሚያምን ነዉ እንግዲህ። ፀጋ ይብዛላቸው!
ተሃድሶ ሰዎች የሚሰሩት ስራ አይደለም! ተሃድሶ ሕይወትን የሚሰጥ (revive የሚያደርግ) መንፈስ የሚሰራው ስራ ነዉ። አትሳቱ: የእግዚአብሔር መንፈስ ነዉ የሚያስፈልገን እንጅ ምንም መንፈስ የሌለው እና መጽሐፍ ቅዱስን በ አመክንዮ የሚተረጉሙ መደዴ አይደለም! እንደዛ ካሉ ወንድሞች አንድ ጓደኛ ያዙና ለአንድ ስምንት ተመልከቱት! የክርስቶስ መንፈስ እንደሚያስፈልገው በግልጽ ይታያችኋል!
Revival እንድሆን የምትጸልዩ የምታለቅሱ: የእግዚአብሔር ልጆች ትጋታችሁን ቀጥሉ! የእግዚአብሔርን ቃል ከዋቢ መጽሐፍት ሰይሆን ከመንፈስ ቅዱስ ተማሩ! እንደዚህ እያደረጋችሁ መሰደብ ክብር ነዉ! መናቅ ሞገስ ነዉ! ብቻ ልባችሁም እጃችሁም ንጹሕ ይሁን እግዚአብሔር በእናንተ የሚሰራውን ፍጥረት ሁሉ ይመለከተዋል! በምድር ላይ ያለ ሰው ሁሉ ወደ እውነት እና ወደ ሃይል ይመለሳል ብላችሁ አታስቡ! እግዚአብሔር ግን ለእናንተ የሰጣችሁን ተግባር ፈጽሙ! በመንፈስ ቅዱስ እየተመራችሁ እና የጽድቅን ፍሬ እያፈራችሁ በክርስቶስ ፍቅር ኑሩ! ያየነውን እና የሰማነውን እንናገራለን!!! እግዚአብሔር በዚህ በዘመን መጨረሻ የሚሰራው ትልቅ ስራ አለ!
የየትኛውም ቡድን ነኝ ከሚል ነገር ግን የክርስቶስ መንፈስ ከሌለው ሰው ራቁ: የክርስቶስ መንፈስ ትሁት! እውነተኛ! ፍቅር! በወንድሞች መካከል አንድነትን የሚያመጣ ነዉ!
Revival ይሆናል! ይህ ስሆን ነገሮች ሁሉ ውብ ይሆናሉ! ምክንያቱም ሰሪው እግዚአብሔር ከሆነ የሚሰራውን ሁሉ ውብ አድርጎ ነዉ የሚሰራው!
#ፀጋ_ይብዛልን!
👇👇👇👇ተቀላቀሉን👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
አጋፔ!
....ያለ ልክ በእግዚአብሔር ተወዳችኋል....
“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።”
— ዮሐንስ 3፥16
በመጀመሪያ መረዳት ያለብን ነገር ፍቅር የሚገለጸው በመስጠት መሆኑን ነዉ: ለሰዎች ያለንን ፍቅር ለመግለጽ ወድ ነገሮቻችንን አንዳንዴ ደግሞ እራሳችንን እንሰጣለን: ከላይ ያለው ቃል እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ያለውን ፍቅር የገለጠበት መንገድ ነዉ። "አንድያ ልጁን መስጠት!"። ይህ በጣም የተለየ ፍቅር ነዉ። ምክንያቱም በሰው ልጅ መልካምነት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን በእግዚአብሔር በራሱ ማንነት ላይ የተመሰረተ እና "አንድ ልጅን በመስጠት" የተገለጠ ፍጹም ፍቅር ነዉ። ስለዚህ የእግዚአብሔር ልጆች እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር ገልጧል! አሁን አይደለም የሚገልጠው ኢየሱስ ክርስቶስን ቤዛችን እንድሆን ስሰጥ ፍጹም ፍቅሩ ታይቷል! እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር ለመግለጥ ከዚህ የተሻለ የሚያደርገው ነገር የለም: ትልቁን ስጦታ ሰጥቶናል! አስቀድሞ ወዶናል እና እኛም እንወደዋለን! በፍቅሩ እንኖራለን: የእግዚአብሔር ልጆች በዚህ መንፈሳዊ እውቀት በቀጣይነት መመላለስ ይኖርብናል! ሰይጣን አልተወደዳችሁም የሚል ውሸቱን በእኛ ጆሮ እንድያሰማ መፍቀድ የለብንም! ምክንያቱም ያለልክ ተወደናል!
👇👇👇👇ተቀላቀሉን👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
አስቸኳይ የመንፈስ ቅዱስ መልእክት!!!!
"በመጨረሻው ዘመን የሰይጣን Strategy ስጋለጥ!! ይሄንን እንድትሰሙት አጋንንቶች አይፈልጉም!" 😱😱🔥🔥
👇👇👇ተቀላቀሉ👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
....አትሳቱ....
“የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ አትሳቱ።”
— ያዕቆብ 1፥16
👉የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች: ዛሬ አንድ ነገር እንድላችሁ ተዝዣለሁ: "አትሳቱ" "Don't be deceived"! እንድላችሁ መንፈስ ቅዱስ ተናግሮኛል!
"አትሳቱ" ከተባልን ግልጽ ነዉ የሚያስት አለ ማለት ነዉ። ያለንበት ዓለም ላይ ያለነው እኛ(ደቀመዛሙርት) ብቻ እንዳልሆንን ታውቃላችሁ: የሰይጣን ደቀመዛሙርትም አሉ: ሰይጣን በብዙ መሰጠት የሚሰሩለት አገልጋዮች አሉት: ጌታ ኢየሱስ ሰይጣንን "የዚህ ዓለም ገዥ" እንዳለው አስታውሱ። ስለዚህ "አሳች" የለም ብሎ ማሰብ ስህተት ነዉ የሚሆነው! እንደውም ከዚህ መልእክት እንድታውቁ የምፈልገው አንድ ነገር "የመጨረሻው ዘመን የሰይጣን ውጥን #ማሳት" እንደሆነ ነዉ። ሰይጣን ከመጀመሪያው አሳች ነበር! ይሄንን እውነት ገነት ውስጥ ሄዋንን እንዴት እንዳሳታት በማስተዋል መመልከት ይቻላል።
“ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ለክርስቶስ ከሚሆን ቅንነትና ንጽሕና ምናልባት እንዳይለወጥ ብዬ እፈራለሁ።”
— 2ኛ ቆሮ 11፥3
ይህ ከመጀመሪያው የሚጠቀመው: የተበከለ ጥበቡ ነበር። አሁን እኛ ባለንበት በመጨረሻው ዘመን መንፈስ ቅዱስ በግልጽ እንደሚናገረው "ማሳት" የሰይጣን መሳርያ ነዉ የሆነው። ይህንንም ለማድረግ በገነት እባብን እንደተጠቀመ አሁን ደግሞ: ተንኮለኛ ልጆቹን (የእፉኝት ልጆች) ይጠቀማል። እነዚህ ሰራተኞቹ በሁሉም ዘርፎች ውስጥ አሉ: በሃይማኖት ውስጥ አሉ!... በፖሎቲካ! ... በፊልም እንዱስትሪ ውስጥ:... በትምህርት ዘርፍ: በኢኮኖሚው ዘርፍ ...በ ሙዝቃ እና በመዝናኛው እንዱስትሪ ውስጥ አሉ....በማሕበራዊ ሚድያው ዘርፍ አሉ....እነዚህ ተራሮች የተቆጣጠረ የትኛውም ብድን ለዓለም ሁሉ ይታያል! ....ለዚህም ነዉ ቢልዮኖችን ለማሳት ቀላል የሆነላቸው። አሁን ግን የእነርሱን ጥበብ ከንቱ የሚያደርግ ልዪ ልዪ የእግዚአብሔር ጥበብ በቤተክርስቲያን በኩል የሚገለጥበት ዘመን ነዉ! ቤተክርስቲያን ትንቃ! ከተሳሳተ የድህነት አስተሳሰብ ወጥተን: በሁሉም እረገድ በመበልጸግ ተራሮችን የምንይዝበት ዘመን ነዉ። ሰይጣን "እንድያስተን" መፍቀድ የለብንም! ይህ ግን አያስተኝም! አልስትም! ብሎ በመፎከር ብቻ የሚሆን አይደለም! ሄዋን የሳተችበት ምክንያት የእግዚአብሔርን ቃል አለማግኘቷ ነዉ! እባቡ በጠየቃት ጊዜ እግዚአብሔር ያላለውን ነገር ስትል ተሰምታለች! ይህ በግልጽ የእግዚአብሔርን ቃል ፈጽማ እንዳላገኘችው የሚያሳይ ነዉ። ኢየሱስ ከሰይጣን በተፈተነበት ወቅት የሰይጣንን አሳችነት ያሸነፈው በእግዚአብሔር ቃል ነበር! ስለዚህ "የማይስቱ" ሰዎች የተማሩ ወይም ገንዘብ ያላቸው ሰዎች አይደሉም በእግዚአብሔር እውነት የበለጸጉ እንጂ! መሳት እንደማትፈልጉ አውቃለሁ! የእግዚአብሔርን ቃል አግኙ! ስተገኙት አጥብቃችሁ ያዙት! አትልቀቁት! ትዝታችሁ ይሁን! ሃሌሉያ! ይህንን ከደረጋችሁ የሰይጣንን ስሁት ንግግር ሁሉ በቀላሉ ታውቃላችሁ! ታሸንፉታላችሁ!!!
👇👇👇👇ተቀላቀሉን👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
