uk
Feedback
መሠረተ ግእዝ

መሠረተ ግእዝ

Відкрити в Telegram

ስለ ግእዝ ቋንቋ በቀላሉ መማር ፤ ማወቅ ፤ ማጥናት መናገር ፤ ይፈልጋሉ ? ይከታተሉ ፡፡ @learnGeez1 @learnGeez1 @learnGeez1

Показати більше
Ефіопія9 614Категорія не вказана
2 194
Підписники
-324 години
-107 днів
-130 днів
Архів дописів
ይሄንን ያየ ፍጡር ሁሉ Join ሳይል እንዳያልፍ #እኛ ጋር በመስራት ህይወቱን ይቀይር!!! # #ባሉበት ሁነው በመስራት በቀን እስከ 23,000 (ሃያ ሶስት ሺ ብር) ተከፋይ የሚሆኑብት ብቸኛው በአገ
ይሄንን ያየ ፍጡር ሁሉ Join ሳይል እንዳያልፍ #እኛ ጋር በመስራት ህይወቱን ይቀይር!!! # #ባሉበት ሁነው በመስራት በቀን እስከ 23,000 (ሃያ ሶስት ሺ ብር) ተከፋይ የሚሆኑብት ብቸኛው በአገራችን እውቅና የተሰጠው ድርጅት እንሆ!! Join us here @etcare_Ethiopian_Company @etcare_Ethiopian_Company @etcare_Ethiopian_Company #share አዲስ አበባ ዋና ቢሮ ባህር ዳር ቅርንጫፍ ቢሮ አዳማ ቅርንጫፍ ቢሮ ስራ ጀምረናል!!!!🤝 እና በቅረብ በተለያዮ ቦታዎች ቢሮዎችን እንከፍታለን

ይሄንን ያየ ፍጡር ሁሉ Join ሳይል እንዳያልፍ #እኛ ጋር በመስራት ህይወቱን ይቀይር!!! # #ባሉበት ሁነው በመስራት በቀን እስከ 23,000 (ሃያ ሶስት ሺ ብር) ተከፋይ የሚሆኑብት ብቸኛው በአገ
ይሄንን ያየ ፍጡር ሁሉ Join ሳይል እንዳያልፍ #እኛ ጋር በመስራት ህይወቱን ይቀይር!!! # #ባሉበት ሁነው በመስራት በቀን እስከ 23,000 (ሃያ ሶስት ሺ ብር) ተከፋይ የሚሆኑብት ብቸኛው በአገራችን እውቅና የተሰጠው ድርጅት እንሆ!! Join us here @etcare_Ethiopian_Company @etcare_Ethiopian_Company @etcare_Ethiopian_Company #share

ለልጅዎ የግእዝ ስም ማውጣት ከፈለጉ ክፍል ፪ ። ግእዝ__አማርኛ ፩) መዓርዒር__ጣፋጭ ፪) አሜር__ፀሐይ ፫) አርያም_ሰማይ ፬) አምኃ_እጅ መንሻ ፭) ብሥራት___የምስራች ፮) ሰሎሜ_ሰላም ፯) አሜን__እውነት/ይሁንልኝ ፰) ሠዊት__እሸት ፱) ጸገየ___አበበ ፲) አስካል____ፍሬ ፲፩) ልዑል____ከፍ ያለ ፲፪) ሣህሉ____ይቅርታው ፲፫) ቀጸላ_አክሊል ፲፬) ሐመልማል___የለመለመ ፲፭) ከሃሊ_የሚችል ቻይ ፲፮) ጸዳሉ_መብራቱ ፲፯) ፈትለ ወርቅ____የወርቅ ፈትል ፲፰) ፊደል_ፊደል ፲፱) ማኅተም____ማተሚያ ፳) ሥዩም__የተሾመ ሹም ፳፩) ስብሐት____ምስጋና ፳፪) ስቡሕ_ምስጉን ፳፫) ተቅዋም_መቅረዝ ፳፬) ንጹሕ_የነጻ ፳፭) ሰላማ__ሰላም ፳፮) አዳም__ያማረ ፳፯) ዳግም_የደገመ ፳፰) ግሩም_ተፈሪ ፳፱) ጥዑም____የሚጣፍጥ ፴) ፍጹም__የተቀባ ፴፩) ይኄይስ____ተሻለ ፴፪) ሐዳስ/ሐዲስ___አዲስ ፴፫) ሕዳሴ__መታደስ ፴፬) ሰንኮሪስ_መምህር ፴፭) መቅደስ_ማመስገኛ ፴፮) ሞገስ__ባለሟል የተወደደ ፴፯) ትዕግሥት_መቻል ፴፰) ንጉሥ__የነገሠ ፴፱) ወራሲ__ወራሽ ፵) ውዳሴ__ምስጋና ፵፩) ጌራወርቅ____የወርቅ ሥራ ፵፪) ማኅደር_ማደሪያ ፵፫) ምሕረት_ይቅርታ ፵፬) መሓሪ__ይቅር ባይ ፵፭) ሠምረ__ወደደ ፵፮) ሥሙር_ተወዳጅ ፵፯) ሥምረት____መወደድ ፵፰) ነጸረ__ተመለከተ ፵፱) ምሥጢሩ____ምሥጢሩ ፶) መራሒ____መሪ ፶፩) ፍሥሓ_ደስታ ፶፪) አእመረ____አወቀ ፶፫) አእምሮ____እውቀት ፶፬) ፍቅር__መውደድ ፶፭) ክቡር__የከበረ ፶፮) ደብሩ__ተራራው ፶፯) ተግባር_ሥራ ፶፰) ረቂቅ__ረቂቅ ፶፱) መብረቁ____መብረቁ ፷) ነጸብራቅ__ነጸብራቅ ። ፷፩) ይባቤ___እልልታ ፷፪) ጥበቡ___ብልሃቱ ፷፫) መሠረት__መሠረት ፷፬) ብሑት___ስልጡን ፷፭) ትሕትና___ትሕትና ፷፮) ተከሥተ__ተገለጠ ፷፯) ሃይማኖት_ሃይማኖት ፷፰) በየነ__ፈረደ ፷፱) መኰንን____ገዢ ፸) በጽሐ__ደረሰ ፸፩) መስፍን____የሚገዛ ፸፪) ምስፍና____ግዛት ፸፫) ክርስቲያን____ክርስቲያን ፸፬) ወሰን__ድንበር ፸፭) መዋዒ_አሸናፊ ፸፮) ትንሣኤ_መነሳት ፸፯) ነቅዐ ሕይወት_የሕይወት ምንጭ ፸፰) ገዛኢ__ገዢ ፸፱) ምሕርካ ክርስቶስ___የክርስቶስ ምርኮ ፹) ባራኪ____ባራክ ፹፩) መልአክ____አለቃ ፹፪) በረከት____በረከት ፹፫) ህላዌ_መኖር ፹፬) ኂሩት_ቸር የሆነች ፹፭) ልባዌ_ማስተዋል ፹፮) ቤዛዊት_ያዳነች የምታድን ፹፯) ስርጋዌ____ሽልማት ፹፰) ስርጉት____የተሸለመች ፹፱) ተስፋ_ተስፋ ፺) ኬንያ__ብልሃተኛ ፺፩) ኖላዊ__ጠባቂ ፺፪) መርዓዊ____ሙሽራ ፺፫) ማዕዶት____መሻገሪያ ፺፬) ወልታ____መከታ/ጋሻ ፺፭) ሐዋዝ____ያማረ ፺፮) ግእዛን____ነጻነት ፺፯) ሕሊና____ሕሊና ፺፰) ማኅሌት____ምስጋና ፺፱) ኅሩይ__ምርጥ ፻) ሲሳይ__ምግብ ፻፩) ሠናይ____ያማረ ፻፪) ፈታሒ____የሚፈርድ ፻፫) ሐሴት____ደስታ ፻፬) ትርሲት_ሽልማት ፻፭) ተዋናዪ_ተጫዋች ፻፮) ዐቢይ___ከፍ ያለ ፻፯) ትውፊት_ስጦታ ፻፰) ኃያል_የበረታ ፻፱) ጽጌ__አበባ ፻፲) ፍሬሕይወት____የሕይወት ፍሬ ፻፲፩) ምዕዳን_ምክር ፻፲፪) ንኡድ___ያማረ ፻፲፫) ነገደ___ሄደ ፻፲፬) ነጎድጓድ____ነጎድጓድ ፻፲፭) ጸዓዳ_ነጭ ፻፲፮) ሠረጸ_በቀለ ፻፲፯) ደምፀ____ተሰማ ፻፲፰) ሮሐ_ወለወለ/አራገበ/አናፈሰ ፻፲፱) ናርዶስ_ሽቱ ፻፳) እፀ ሕይወት___የሕይወት እንጨት ። ክፍል ፩ ከዚህ ቀደም በዚሁ በቴሌግራም ቻናሌ ተለቆ ስለነበር ወደኋላ ተመልክተው ያገኙታል።

#ምግብና #መጠጥ ነክ ነገሮች ግእዝ_አማርኛ ገይላ____አሞሌ ጨው ተብሲል___ንፍሮ ጼተሎ____ጉሽ ጠጅ ጳኵሲማ____ዳቦ/አንባሻ ልሔም_ዳቦ ፕፕሬ____በርበሬ መዓር_ማር ሶከር_ስኳር ሐሊብ____ወተት ኅብስት____እንጀራ አረቦናት____ፍትግ ክክ አያያት_የማር ወለላ ግብነት_አይብ ሆሳዕና_መድኃኒት መና_እንጀራ ጸደና____የጣዝማ ማር ዕቋን____ወገሚት አክራጦን___የወይን ጠጅ ወይን____ወይን ጤጉን_ዳቦ ቆሎ ሐምለ ብሒእ____ስልጆ ፀቃውዕ_የማር ወለላ ኮቤዝ_ዳቦ/አንባሻ ማዕድ____ማዕድ/መሶብ ቴሮጋ_እርጎ ወተት ሱራጌ_መረቅ አንቆቅሖ____እንቁላል ። #የአካል ክፍሎች እራኅ_መሐል እጅ ድማኅ____መሐል ራስ ዳሌ__የጀርባ አጥንት ሰይል_ሽል/ጽንስ ዐፅም____አጥንት ተኬሳ_ትክሻ ሕዋስ_ሰውነት ሐቌ_ወገብ ቅርንብ____ቅንድብ ዘነብ_ጅራት ደርፍዑ____ሻኛ ቀርን_ቀንድ ተላዕ____ፍሪንባ ጸኵ_ሹልዳ መስቴካ____ጨጓራ ገቦ__ጎን መልታሕት___ፊት/ጉንጭ ማዑት____አንጀት መዝራዕት___ክንድ ሥዕርት____ጸጉር ኵሊት_ኩላሊት ሰኮና_ተረከዝ ሥን_ደም ግባት እዝን____ጆሮ ዓይን____ዓይን ዘባን_ጀርባ ጕርዔ____ጉረሮ ሰንቡዕ____ሳንባ ኵርናዕ_ክንድ ሐልገዝ____የደም ሥር መንኮብያ____አውራ ጣት ክሳድ__አንገት ከብድ__ሆድ ቍይጽ__ጭን መትከፍ_ትከሻ ። #የቤት ዕቃዎች & አልባሳት ቀርጠፋሉ____ቶፋ ገብላ___ገንዳ/ገበታ ቤረሌ___ብርሌ/ብርጭቆ መሐፒል_ሳሙና መንዲል_ሸማ ልብስ ሰይቀል_እንዝርት ጻሕል__ወጪት ጽንጉል_ፍግ ፍያል__ፍንጃል ማዕሎ_አዷማ ለንጳስ__ግምጃ ኬጥሮጋውሎስ___የብረት ጋን ፊላስ_የአልጋ ልብስ ጌልዳቦሩ____ቡሃቃ ምዕራ/መታግር_ጉልቻ ቃሩራ____ጠርሙስ/ብርጭቆ ንብቲራ_ኩስኩስት ኮራ____ጋን/ጽዋ ፓፒራ____ክብሪት ጶደሬ____ግምጃ ቢሶስ___አረንጓዴ ዓይነት ልብስ ከፈር_ቅርጫት/እንቅብ ጎሞር/ሜላቃ_ቁና ጻሕር____ብረት ምጣድ ፀምር____ግምጃ መባሮ____መቆፈሪያ መጕድዕ____መዶሻ መሥነቅ____ስልቻ መቀቅ_ሙገጫ ቴውናቅ/ሱጣብ/ሱጣ__ወስከንበያ ጸርቅ__ድሪቶ ሶርቃቡ_እርሾ/ሊጥ ድልጋቡ_አቅማዳ መኩረቢ_መጥረቢያ መሶብ_መሶብ መዝረብ/ሰፌልያ____መዶሻ መዝገብ_ሳጥን ግራብ__ገንቦ ጻሕብ__ማድጋ/ወጭት ከረቦ__አገልግል ክእቦ/ክቦ__ኩበት ልሕኵት__ገንቦ ሜላት_ሐር ግምጃ መስብክት____ጋን መሥነቅት____አቅማዳ መቅጹት____ድስት/ምንቸት መንኮክት____እንዝርት ራግናት__ብቅል ቀሡት_እንስራ ዐራት_አልጋ ወዲፈት____ዳውጃ/ግምጃ ጨርቅ ጽህርት____ጋን ጽፍነት____ስልቻ ቴግኑ_ጉልቻ ፓና____መብራት ልጕን____ማሰሮ ቆጶን____ጫማ ጤገን____ብረት ምጣድ ጵርዩን____መጋዝ ግምዔ____ማሰሮ ገልዕ____ገል ፀፍዕ____አዛባ/ፋንድያ መንካ____ማንኪያ ማዕከክ_ማሰሮ/ቶፋ/ገንቦ ማህው__ብርጭቆ/ብርሌ ጠረጴዛ____ወንበር ሰፌልያ____ድጅኖ/መዶሻ አስፈሬዳ____እንቅብ/ቅርጫት ወሳይድ_ትራስ ሰንጎጕ_የብረት ዘንግ #መልክዐ ምድር & ነገረ ሀገር ሄላ_ምንጭ ዔላ_የውሃ ጉድጓድ ቀልቀል___ገደል አፋፍ ደወል_አውራጃ/ቀበሌ ዐምዓም___ረግረግ ገዳም/ሊሳ_ዱር/በረሓ መጽአሞ____ዋሻ/ግምጃ ቆሮስ_መስፈሪያ ላዳን ቀርሜሎስ____ለምለም ዱር ቃዴስ____በረሓ አርዮጳጌጤስ____መዝናኛ ቦታ ባሕር____ባሕር ወግር_ኮረብታ ደብር_ተራራ ሰንሰሪቁ/ኬርቃ____ስርጥ መንገድ መርቄ____ቆላ ሐይቅ____ወደብ/ዳር መርሕብ____ሜዳ ዐቀብ_ተራራ/ገደል ግብ__ጉድጓድ ምኔት_ገዳም ሰኮት_አውራ መንገድ ዐዘቅት____ጉድጓድ ደሴት_የባሕር ጥጋጥግ ገነት_ጓሮ/የተክል ቦታ ጾማዕት/ጾላዕት___ዋሻ ፂዖት____የከብት መሰማሪያ ክልክል ፍኖት___ጎዳና መዲና____ከተማ/አደባባይ ፍና_መንገድ ጕርን____አውድማ ደደክ_ደጋ ሐዝሐዝ____ረግረግ ። #የእርሻ እቃዎች ላሕሎ_ወገል ሰይራ_ወገል ሞሰርት_ማረሻ አርዑት_ቀንበር አግልዕት____ማነቂያ ገራህት____እርሻ ጸጕራፍ____ጅራፍ ። #ነገረ #ቤት ትሄ_____መስኮት ጽርሕ_አዳራሽ ኰኵሕ_አለት ደንጊያ መርኆ_መክፈቻ ሶልላ__ኩረት፣ አሸዋ፣ አፈር ጺላ___ጭቃ ሶቶፍሌ_ምንቸት መርጡል____አዳራሽ ሩካም___ዕብነ በረድ ተንከተም_ድልድይ/መሰላል ናሕስ___የግንብ ቤት ኤስኬዴሬ_እልፍኝ ኆር____መስኮት ጠፈር____ባጥ ፍንዱቅ____ሆቴል ኆኅት_ደጃፍ ሐይመት____ድንኳን ልገት_ጎጆ መሬት_አፈር ብርት__ብረት ቤት_ቤት ኀጺን_ብረት ሜላንትሮን____ጉልላት ዕብን_ድንጋይ ጽንጕን____ጭቃ ታዕካ____አዳራሽ ሐኒክ____አፈር ሰዋስው___መሰላል/ድልድይ ዴዴ____ደጃፍ በር ሐመድ____አመድ/ክሰል ድድ_መሰረት መምሠጥ____ቁልፍ አንቀጽ_ደጃፍ/በር ዕፅ___እንጨት ። ለአንድ ቃል ብዙ ተመሳሳይ ትርጉሞች አሉት። ስለዚህ የተደጋገሙ ቃላትን ስናይ በዚህ መልኩ እንደሆነ እናስተውል።

እንስሳት፣ አራዊት፣ አዕዋፋት በግእዝ ግእዝ_አማርኛ ቶራ_አጋዘ ሐንዘር___አነር ነር____ነብር ድግ____አህያ ካሂ_ጥገት (አራ ላም) ካሂ__ጊደር ተክሉ____የበግ አውራ ናጦሊ__የግመል ጊደር ጠ____ፍየል ዳቤላ___የፍየል አውራ ቅል___በቅሎ ዕዋል___የአህያ ውርንጭ ዕጕል__ግልገል ገመል__መል ላሕም__ላ/በሬ ሰቄዘሩ__አራስ ውሻ ሦር____በሬ/ወይፈን ልብ___ውሻ ሔሴሜት____ድመት ቴፈን__ወይፈን መሐስዕ_ቦት በግዕ___በ በሐኵ__ጠት/አውራ ጣዕ__ጥጃ ሐርጌ__ጊደ/ሙክት ሐርፅ__አዞ ተስጴዳ_ጥንል ቀርዱ__ዝጀሮ ከማንዮ__ግስላ ከራግልዮ_ሳማ ሐለስትዮ__ጣ ሆባይ _ዝንጀሮ አርዌ___አውሬ ግሔ____እሽኮኮ ቢሕ____ጉማሬ ዔሊ___ድንጋይ ልብሱ ኵላ__ተኵላ መንተሌ_ጥቸል ሐራድል_ጅ ኀየል____ዋያ ቀይዘል_ሚዳቋ ቍንጽል_ቀበ ወይጠል____ፌቆ አንበሳ____አንበሳ ሐሪስ_አውራሪስ ዋኖስ___ዋሊያ ገሙስ__ሽ ጋስ____የዳ አህያ ቃንስ__ጉሬዛ ራኩብ____የግመል ወሳብሬ ዝእብ_ጅብ ላጽቂት____ንጣ/እንሽላሊት ሥርዐት____ድርጪት ብሄሞት____ጉማሬ/ጎሽ ተረቅት/ጽግነት_የሌት ወፍ ጼዴነት____ድንጋይ ልብሱ/ዔሊ ጻጹት___ጫጭት ጽርኒ____አይጥ ኦርና____ሚዳቋ ማዖን____ድኩላ ሰርኖን____ሰገኖ ሰራግልዮን___ዐሳማ ቅጥራቅጥሬን____ድንቢጥ ተመን_ዘንዶ ደስከን_ጎሽ ደራጎን_ዘንዶ ቀቀኖ_ርኩም ደስከኖ_ጎሽ እልልድኩ_አነ ድመት ሐርማ_ጎሽ ቅንፉዝ_ጃርት ነጌ__ዝሆን ። ጸያጴ____እንሽላሊት መንጢጥ____ድምቢጥ ወፍ አዲማ/ቶብኒ____ትኋን ቃሕም____ገብረ ጉንዳን ቆጶሮጢስ___የንብ አውራ ንብሌስ_ፌንጣ አክሳስ____ሺህ እግር/ቅንቡርስ/የእበት ትል ዘንቢር____ተቆናጣጭ ዝንብ ሐንቄ/ቆብኒ_ቅማል ንህብ____ብ አቅራብ_ንጥ ሣሬት__ሸረት ሰኳዕት____ጉንዳን ጸንጾላዕት___የእሳት ራት ጽንጽንት____ነቀዝ/ብል ቁንቁኔ___ነቀዝ ሐሴን____አሸን ቀርነናዕ____ትል ቈርነናዕ____እንቁራሪት ኮራኪ_ምስጥ/ጉንዳን አንዋ____አይጥ ከመዝ____የውሃ እናት ትንንያ____ትንኝ ጽንጽንያ____ዝንብ ጕጋ__ቁንጫ ዕፄ_ትል ፄ__ብል/ነዝ አንባ____አንበጣ ኤርጌት____አውራ ዶሮ ፍኅርት_ጫጭት ዖፍ__ወፍ ርሆ_ዶሮ ርቤዶ_ዥግራ ቆቅሕ___ቆ ገምሉ___ለቅት ኔስታሊ__የመስክ እባብ ኤሊ__የእሳት ራት ከይ_እባብ ዓሣ__ዓሣ ርሣ_አንባ ሬክትም/ፊትም_የውሃ እናት ሰጳላስስ/ገላሜዎስ____እስስት አንበሪ/ዐንበር__ታላቅ ዓሣ ጳልቃ_ርኩም ሰገኖ_ሰጎን ንስር_አሞራ ዐንቄ____ጭላት ርግብ___ርግብ ማዕነቅ____ሽመላ ቋዕ____ቁራ ሶቤቃካ____ጅግራ ኬሌሜዎን____እስስት ዙዝዮን_አለቅት ። ማስታዎሻ:-ለአንዱ የአማርኛ ቃል ብዙ የተለያዩ የግእዝ ቃላት ሊኖሩት ይችላሉ። ለምሳሌ ርኩም ለሚለው የአማርኛ ቃል በግእዝ "ጳልቃን" ወይም "ቀቀኖ" ይሆናሉ። ስለዚህ ከጽሑፉ የተደጋገመ ነገር ብታዩ ተሳስቶ ሳይሆን ለአንዱ ቃል ብዙ አቻ ትርጓሜ ስላለው መሆኑን እንድትገነዘቡ። ።

#ዕፀዋት #በግእዝ #ቋንቋ ግእዝ__አማርኛ ሰናፔ__ሰናፍጭ ሐረፍ__ጎመንዘር/ቅባኑግ መናሂ__ነጭ ጤፍ ዳሂ____ጓያ ሡራሕ_ድንች ቤዴላህ____እንጉዳይ በጢሕ_ዱባ ሄላ____የወይን ዘለላ ደንጎላ__ሱፍ ስንዳሌ_ስንዴ ሐምል__ጎመን በድል/ፋል___ባቄላ በጸል/ቱማ___ነጭ ሽንኩርት እክል___እህል ዚፋል___ሽንብራ ቢጸልቱማ___ቀይ ሽንኩርት ሕጥሜ_ጎመንዘር ኅጥጥሜ___ጥጥ ሐምሐም____ቅል ሰገም___ገብስ ሊጦስ/አስፈሊጦስ__ሰሊጥ መለንስ_ኑግ ሲላስ__አብሽ ቆንደራጢስ/ዱሓን__ዳጉሳ ተርሙስ____አተር አለንስ__አጃ ሕምር/ጥምዐት____እንሶስላ ትለቤ/ከሙን__ተልባ ሶመት_ነጭ ሽንኩርት እንጎት_ትርንጎ መርሳኒ_ቀጋ መልጰጶን____ጎመን ከሜን__ፌጦ ከርካዕ_ሎሚ ፔርካ__ሽንብራ ጓልኬ_ሰናፍጭ ሴዋ__ጌሾ ቃሕዋ_ቡና ሥርናይ___ስንዴ ተቅዳ_ድንብላል ስጕርንድ___ሽንኩርት ሑስጱ_አሽክት ክርዳድ_እንክርዳድ ኵሓ____ከያ ዛፍ ኤርጋሄ__አክርማ ሰግላ___ሾላ አሜከላ_እሾህ ኩላ___ሙጫ ሕንጽዋል___አረማሞ(የእፅዋት በሽታ) ከርሜል__ችፍርግ ቢሶም___ምሳና በርሴም__ጽድ በራቄኒም_ኮሸሽላ ዖም_____ዛፍ ተቢሳ___ሸንበቆ ሜርሴንስ____ቀጋ ቄድሮስ__ዋንዛ ባሕሩስ_መቃ ሸንበቆ ብሕውስ____መጭ/አብሾ/አስተናግር ኤልያስ__ወይራ ጠርቤንቶስ____ዋርካ መዓረግራ_ሙጫ/አዶሮማር ፐፒራ/አዛብ____እንዶድ መምሬ_ወይራ ተምር__ተምር ዕጕስታር_ሬት አጽፋር__አደይ አበባ ሳቤቅ_ያረግ ሬሳ ዘግባ_ዝግባ ቀረብ_እንቧይ ዐቃብ____ኮሸሽላ ሾኽ ስት___ቄጤማ አርቦት_ችባሓ አቃኒ_ችፍርግ ጳውቄና____ጽድ ልብኔ_ልምጭ ሰቂኖን_ኮክ ሰኪኖን_እንዶድ ሰውሳን_ሱፍ ሰጥረጲሎን____ዋንዛ/ሽነት ራምኖን_ዶግ ቄድሮን__ዋንዛ ተርሜን_ድድሆ/ክትክታ ከርሜን_ድድሆ ጢጤን_ዶቅማ ጎሜዕ__ሸንበቆ/ቅርቅሀ ሮዛ____ጽጌረዳ አርዝ___ዛፍ ፒርልዩ__ቀንጠፋ ምግራይ____ግራር መጽርይ_ቀጋ ፐፒረለይ____እንዶድ መድዮ___ጨፌ ቀለምጤዳ____ቅንጭብ ቀለምጼዳ_ቁልቋል ተሐግ_____ሰርዶ ።

የግእዝ ቋንቋ ትምህርት1.pdf1.65 MB

2.76 MB

1.66 MB

#እንኳን #ለቅድስት #ሥላሴ #ዓመታዊ #በዓል #በሰላም #አደረሳችሁ። ዓለምን ካለመኖር የፈጠሩ፣ ፈጥረውም የሚያስተዳድሩ ሥላሴ በአካል ሦስት ሲሆኑ በባሕርይ አንድ ናቸው። ። √ በአካላዊ ግብር ሦስት ናቸው። በአካላዊ ግብር ሥምም ሦስት ናቸው። ይህም ወላዲ አሥራጺ፣ ተወላዲ፣ ሠራጺ መባል ነው። ። √ በሥልጣናዊ (በባሕርያዊ) ግብር አንድ ናቸው። በባሕርያዊ ግብር ሥምም አንድ ናቸው። ይህም አምላክ፣ ፈጣሪ፣ እግዚአብሔር ወዘተ የመሳሰለው ነው። ። √ በከዊን ሦስት ናቸው። እኒህም ቃል መሆን፣ ልብ መሆን፣ እስትንፋስ መሆን ናቸው። በዚህም ሥላሴ ነባብያን፣ ሕያዋን፣ ለባውያን መሆናቸውን እናውቃለን ። √ በባሕርይ አንድ ናቸው። ይህም ማለት የሦስቱ ኩነታት ተገናዝቦ አንድ ሕይወተ አንድ ባሕርይ ይባላል። ። √ በአካል ሦስት ናቸው። በአካል ሥምም ሦስት ናቸው። ይህም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ መባል ነው። +++++++++ +++++++++ እንኳን አደረሳችሁ።አብርሃም ወሰዶ ለይስሐቅ ወልዱ ከመ ይሡዖ። አውረደ ሎቱ ቤዛሁ በግዐ። ዛሬ በማኅሌት የሚባሉ ወረቦችን የባሕርዳር ብዙኃን ማርያም የአቋቋም መምህር የሆኑት መምህር ልሳነ ወርቅ በዩቲይብ ቻናላቸው ለቀውልናል። #ልሳኑ #ዘያሬድ በሚለው የዩቲይብ ቻናል ገብተው ይመልከቱ። ። ከዚህ ቀጥሎ ከዛሬ ወረቦች የተወሰኑትን ስሟቸው ። እነሆ

ምርጡ ጓደኛየ መምህር ልሳነወርቅ ናቸው። ጥዑም ዜማ ያድምጡ።

#የቅኔ #ጉባኤ #ቤት ባህር ዳር የሚገኘው ታላቁ የቅኔ ጉባኤ ቤት ሊሠራ የሚከተለውን ዓይነት ዲዛይን ወጥቶለታል፡፡ የጉባኤ ቤት ቤት አሠራር ትውፊትን የያዘ ድንቅ ዲዛይን ነው፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ለ
+2
#የቅኔ #ጉባኤ #ቤት ባህር ዳር የሚገኘው ታላቁ የቅኔ ጉባኤ ቤት ሊሠራ የሚከተለውን ዓይነት ዲዛይን ወጥቶለታል፡፡ የጉባኤ ቤት ቤት አሠራር ትውፊትን የያዘ ድንቅ ዲዛይን ነው፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ለትርጓሜም ለሌሎች ትምህርቶችም ዋናው ቁልፍ ቅኔ ነው፡፡ የግእዝ ትምህርት በጥልቀት የሚሰጠው ቅኔ ቤት ነው፡፡ ግእዝ ደግሞ ብዙ ጥንታውያን መጻሕፍት የተጻፉበት ቋንቋ ነው፡፡ ሊቃውንቱ በቅኔያቸው የእግዚአብሔርን ቸርነቱን፣ መግቦቱን፣ ሁሉን ቻይነቱን፣ ፈታሒነቱን፣ ይቅር ባይነቱን፣ አንድነቱን፣ ሦስትነቱን፣ ጌትነቱን፣ ዘለዓለማዊነቱን በአማረ የቋንቋ አሰካክ በሰምና ወርቅ ይገልጡበታል፡፡ የቅዱሳንን አማላጅነት የሰማዕታትን መንፈሳዊ ቆራጥነት የመላእክትን ተራዳኢነት በቅኔያቸው ይገልጹታል፡፡ በቅኔያቸው ክፉዎችን ይገሥጹበታል፡፡ ምእመናንን ይመክሩበታል፡፡ ፡፡ በአጭሩ ለመግለጽ ቅኔ መንፈሳዊ ፍልስፍና ነው፡፡ ቀድሞማ መሳፍንቱ መኳንንቱ ወይዛዝርቱ ሁሉ ባለቅኔ ነበሩ፡፡ የዚችን ዓለም ከንቱነት በቅኔያቸው ይገልጡት ነበር፡፡ የእነ ተዋነይ መንፈሳዊ ፍልስፍናኮ ቅኔ ነው፡፡ የቅኔ ትምህርት በአሁኑ ሰዓት በስፋት የሚሰጥበት ጉባኤ ደግሞ የሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው ልጅ የሆኑት የየኔታ ቅዱስ ያሬድ ጉባኤ ቤት ነው፡፡ ይህን ጉባኤ ቤት ለመሠራት ወደ 200 ሚልየን ብር ይፈጃል ተብሏል፡፡ ስለዚህ ሁሉም በችሎታው ማገዝ አለበት፡፡ ለማገዝ የምትፈልጉ ከስር በተገለጡት የአካውንት ቁጥሮች መርዳት ትችላላችሁ፡፡ ፡፡ አምላከ ሊቃውንት እግዚአብሔር ቤተጉባኤን ይጠብቅልን፡፡

Share 'attachment.pdf'

photo content

​✝️ እንቋዕ አብጽሐክሙ ለእግዚእነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ በሰላም በፍቅር ወበጥዒና። ሠናይ በዓል ይኩን ለኲልክሙ ሕዝበ ክርስቲያን! "ኢሀሎ ፡ ዝየ ፡ ተንሥአ ፡ በከመ ፡ ይቤ ፤ እንደተናገረ ተነስቷልና በዚህ የለም" ማቴ ፳፰ ፥ ፮ "እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም በፍቅርና በጤና አደረሳችሁ።" ✝️ ለሁሉም የክርስቲያን ሕዝብ መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁን ○▭▭▭▭▭▭▭▭▭▭▭▭○ 🔆 የቃሎች ትክክለኛ አጻጻፍ ✅በዓል - የሚከበር ቀን ❌በአል - የጣዖት ስም ✅ዓመት - ዘመን ❌አመት - አገልጋይ ✅ትንሣኤ - መነሣት ❌ ትንሳኤ ✅ሰላም - ሰላም ❌ሠላም ✅ ዓመተ ምሕረት - የይቅርታ ዘመን ❌መሀረ - አስተማረ መሐረ - (ምሕረት) ➜ ይቅር አለ (ይቅርታ) 🌸 መ ሠ ረ ተ ግ እ ዝ

አቤቱ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበን
አቤቱ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበን

ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም አረፉ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቀድሞ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የሕክምና ክትትል ሲደረግላቸው ቆይቶ ዛሬ እሁድ
+1
ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም አረፉ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቀድሞ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የሕክምና ክትትል ሲደረግላቸው ቆይቶ ዛሬ እሁድ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን የኢኦተቤ መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት አሳውቋል።

ሀ/ በጋይንት አውራጃ በታች ጋይንት ወረዳ በምትገኘው በታላቋ ደብር ቤተ ልሔም ከአንድ በጎ አድራጊ ርዳታ በመጠየቅ በናፍጣ የሚሠራ አንድ የሞተር ወፍጮ አቋቁመው ለካህናቱና ድጓ ለሚያደርሱ ተማሪዎች ደመወዛቸውን እንዲችሉ ጥረዋል፡፡ ለ/ በደብረ ታቦር አውራጃ በእስቴ ወረዳ ሊጋባ ቅዱስ ሚካኤል በተባለው ቤተ ክርስቲያን አካባቢ አንድ የሞተር ወፍጮ በጎ አድራጊዎችን በመጠየቅ እንዲቋቋም አድርገዋል፡፡ አገልጋይ ካህናትም የወር ደመወዝተኛ እንዲኾኑ አድርገዋል፡፡ ሐ/ ጥንታውያን መጻሕፍት ለትውልድ እንዲተላለፉ ለማድረግ ባደረጉት ጥረት፡- ጠቢበ ጠቢባን፣ ሙሉ ሲኖዶስ፣ የቅዳሴ አንድምታ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰናቸውን ውሳኔዎች በሙሉ በብራና እንዲጻፉ አድርገዋል፡፡ በጭልጋ፣ በሊቦ፣ በደብረ ታቦር፣ በጋይንት አውራጃዎችና በእስቴ ወረዳ የችግኝ ጣቢያዎች አቋቁመው በየዓመቱ በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ችግኞች በየአብያተ ክርስቲያናቱ ሰበካና ለሕዝባውያን ድርጅቶች እንዲከፋፈሉ በማድረጋቸው የተራቆቱ መሬቶች በዛፎች እንዲዋቡ ጥረዋል፡፡ መ/ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በማስፈቀድ በማኅደረ ማርያም የሐዲሳት፣ የድጓና የቅዳሴ ት/ቤት አሠርተው ለመምህራኑ ከ50 እስከ 200 ብር ደመወዝ እንዲከፈላቸው፣ ለደቀ መዛሙርቱ ድጎማ እንዲሰጣቸው አድርገዋል፡፡ ሠ/ ጥንታዊውንና ታሪካዊውን የጣና ቂርቆስ ገዳም በብር 8ሺሕ835 እንዲታደስ አድርገዋል፡፡ በጣና ለሬማ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ብር 4ሺሕ ረድተዋል፡፡ የደረሞ ቅዱስ ሚካኤልን ቤተ ክርስቲያን ብር 21ሺሕ 114 በማውጣት አሳድሰዋል፡፡ እንዲሁም ጥንታዊውን የግርቢ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በብር 8ሺሕ860 ብር እንዲታደስ አድርገዋል፡፡ በአዘዞ በሰሚ ቅዱስ ሚካኤል ወደ ካህናቱ ማሠልጠኛ የሚወስደው መንገድ በምግብ ለሥራ መርሐ ግብር እንዲሠራ አድርገዋል፡፡ በጎንደር መንበረ መንግሥት ጥበበ እድና የአዳሪ ቤቱ ዙሪያ ርዳታ በመጠየቅ ከ9ሺሕ በላይ በማወጣት እንዲሠራ አድርገዋል፡፡ በጎንደር ጉባኤ ቤትና የዶክተር አየለ ዓለሙ የመቃብር ቤት የአራቱ ጉባኤያት ሥዕል እንዲሠራበት አድርገዋል፡፡ በሊቦ አውራጃ በቆላ እብናት ለአምራቾች የኅብረት ሥራ ማኅበር ብር 15 ሺሕ ረድተዋል፡፡ በጎንደር ከተማ በአዘዞ አባ ሳሙኤል በመጠለያ ለሚረዱ ከልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ መምሪያ ጋራ በመተባበር የኤልክትሪክ ምጣድ ርዳታ አድርገዋል፡፡ በዳባት ወረዳ የሚገኘውን የደፍቂ ቅዱስ ሚካኤልን በብር 5ሺሕ፣ ቆማ ፋሲለደስን በብር 5ሺሕ አሳድሰዋል፡፡ ለአምስትያ ገዳም ብር 4ሺሕ፣ ለጣርክ ማርያም ብር 7ሺሕ ረድተዋል፡፡ ዐደባባይ ኢየሱስም በብር 40ሺሕ እንዲታደስ አድርገዋል፤ የድምፅ ማጉያም አስገብተውለታል፡፡ በጎንደር ዙሪያ አውራጃ ለቸንከር ተክለ ሃይማኖት ርዳታ በመጠየቅ ብር 764ሺሕ አበርክተዋል፡፡ በዚያው በጎንደር ዙሪያ ከማክሰኝት እስከ አርባያ ለመንገድ ሥራ ብር 30ሺሕ ርዳታ እንዲገኝ አድርገዋል፡፡ ከእብናት እስከ ጎሐላ ለመንገድ ሥራ የብር 6ሺሕ ርዳታ እንዲገኝ አድርገዋል፡፡ በስሜን አውራጃ ለሚገኙ ጥንታውያን ገዳማት፤ ለቤተ ሚናስ ዋልድባ ከብር 10ሺሕ በላይ፤ ለጣዕመ ክርስቶስ ብር 10ሺሕ፣ ለሰቋር ዋልድባ ብር 4ሺሕ ግምት ያላቸው የቁሳቁስ(የዓይነት) ርዳታ አድርገዋል፡፡ በጎርጎራ ገዳም በደሴተ ጣና ለሚገኙ ገዳማት፤ ለማን እንዳባ ገዳም ብር 1ሺሕ880፤ ለብርጊዳ ማርያም ገዳም ብር 1ሺሕ ለበሬ መግዣ እንዲሰጥ አድርገዋል፡፡ ከልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ መምሪያ ርዳታ ሰጪ ድርጀቶች በመጠየቅ አቅም በፈቀደ መጠን በተወሰኑ አብያተ ክርስቲያናት የቆዳ፣ የሽመና፣ የሹራብ ሥራ፣ የልብስ ስፌት፣ የወፍጮ ቤትና የዳቦ ቤት እንዲቋቋምና አገልግሎት እንዲሰጡ አድርገዋል፡፡ በተጨማሪም ለስብከተ ወንጌል፣ ለሰንበት ት/ቤትና ለሕዝብም መሰብሰቢያ የሚያገለግሉ አዳራሾች በየአብያተ ክርስቲያናቱ አካባቢ አሠርተዋል፡፡ ሕዝቡ ንጹሕ ውኃ ማግኘት እንዲችል የውኃ ጉድጓድ በማስቆፈር ለዚሁ የሚያገለግል ሞተርና ቧምቧ እንዲያገኙ የበኩላቸውን ጥረዋል፡፡ ለሀገረ ስብከቱ ያስገኟቸው ሽልማቶች፤ የሰበካ ጉባኤ ቃለ ዐዋዲ ደንብ በትክክል እንዲፈጸም በማድረጋቸውና ሰበካ ጉባኤን በሚገባ በማደራጀታቸው፣በየዓመቱ በሚደረገው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባ የሥራ ግምገማ በተደረሰበት ውጤት የጎንደር ሀገረ ስብከት ቅድሚያ ቦታ እንዲይዝ አድርገዋል፡፡ በዚህም መሠረት፡- ከ16ቱ አህጉረ ስብከት፣ ከ1975 እስከ 1977 ዓ.ም. በተከታታይ እንዲሁም በ1979 ዓ.ም. አንደኛ፤ በ1978 ዓ.ም. ኹለተኛ በመኾን በውጤታማነት እንዲሸለም አድርገዋል፡፡ ብፁዕነታቸው፣ ከዚህ በላይ ጠቅለል ባለ መልክ በተዘረዘረው ዓይነት ተልእኳቸውን በትክክል የተወጡ አባት ከመኾናቸውም በላይ በ1979 ዓ.ም. በተደረገው የብሔራዊ ሸንጎ አባላት ምርጫ በጎንደር ዙሪያ አውራጃ ምርጫ ጣቢያ ደንቢያ ከመረጠው 26ሺሕ127 ሕዝብ መካከል 17ሺሕ249 ድምፅ በማግኘት ተመርጠው ሕዝብን አገልግለዋል፡፡ ብፁዕ አቡነ መርቆሬዎስ፣ የበላዮቻቸውን መካሪ፣ የበታቾቻቸውን አክባሪ፣ በሥራ ታታሪ፣ መንፈሳዊ አባትነታቸውና ትሑት ሰብእናቸው አርኣያነት ያለው ቁጥብ አባት ናቸው፡፡

በመርቆርዮስ ቀን መርቆርዮስ ሄዱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አራተኛ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። በረከታቸው ይደርብን:: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ፣ 4ኛ ፓትርያርክ ኾነው የተሾሙት፣ ነሐሴ 29 ቀን 1980 ዓ.ም. ሲኾን፣ በፖሊቲካዊ ግፊትና ጫና መንበራቸውን ለቀው ከሀገር ከመውጣታቸው በፊት እስከ ነሐሴ 28 ቀን 1983 ዓ.ም. ድረስ ለቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ አመራር ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ ከ26 ዓመታት ስደት በኋላ፣ ሐምሌ 25 ቀን 2010 ዓ.ም.፣ በስሙ በተሠየሙበት በሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ክብረ በዓል ወደ ቅድስት ሀገራቸው ኢትዮጵያ መመለሳቸውን፣ ይታወቃል፡፡ ልደት በፊት ስማቸው አባ ዘሊባኖስ ፈንታ የሚባሉት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ፣ በጎንደር ክፍለ ሀገር በደብረ ታቦር አውራጃ በአለታ ወረዳ አረጊት ኪዳነ ምሕረት በተባለችው ገዳም ሰበካ፣ ልዩ ስሙ ማር ምድር በ1930 ዓ.ም.፣ ከብላታ ፈንታ ተሰማና ከወ/ሮ ለምለም ገሰሰ ተወለዱ፡፡ መንፈሳዊ ትምህርት ዕድሜያቸው ለትምህርት በደረሰ ጊዜ፣ በተወለዱበት ገዳም መሪጌታ ላቀው ከሚባሉ መምህር፣ ንባብና ዳዊት ተማሩ፡፡ ከዚያም በኋላ አጭታን ኪዳነ ምሕረት በምትባለው ደብር ምዕራፍና ጾመ ድጓ ተምረዋል፡፡ ትምህርታቸውን ለመቀጠል ወደ ጎጃም ክፍለ ሀገር ሔደው ጎንጅ ቴዎድሮስ በተባለው ገዳም ለኹለት ዓመት ከመሪጌታ ወርቁ፣ ወደ ዋሸራ በመዛወር በቅኔ ዝነኛ ከነበሩት ከመሪጌታ ማዕበል ፈንቴ ለኹለት ዓመት በጠቅላላ በአራት ዓመት የቅኔ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡ ከዚያም በኋላ ወደ ትውልድ ሀገራቸው ተመልሰው፣ በደብረ ታቦር አውራጃ እስቴ ወረዳ አጋጥ ደብረ ጽዮን፥ የምዕራፍ፣ ጾመ ድጓና ድጓ ትምህርታቸውን ከመሪጌታ ሙጩ አጠናቀዋል፡፡ ወደ አቋቋም ቤት በመግባት፣ መነጒዘር በሚባለው ደብር፣ ከመሪጌታ ሚናስ ለኹለት ዓመት የአቋቋም ትምህርት ተምረዋል፡፡ ከዚያም ቁት አቡነ አረጋዊ ደብር፣ ከመሪጌታ ውብ አገኝ ለአንድ ዓመት ዝማሬ መዋሥዕት ተምረዋል፡፡ ወደ ደብረ ታቦር አውራጃ ተመልሰው፣ ከጥንቱ መምህራቸው ከመሪጌታ ሙጩ ላቀ ዘንድ የድጓ ትምህርታቸውን በመቀጠል ጽፈውና አመልክተው ከጨረሱ በኋላ፣ በነፋስ መውጫ አውራጃ በታች ጋይንት ወረዳ በምትገኘው በስመ ጥሩዋ በቤተ ልሔም አራት ዓመት ቆይተው ድጓ አስመስክረው በመምህርነት ተመርቀዋል፡፡ የድጓ ትምህርታቸውን ካስመሰከሩ በኋላ ወደተወለዱበት ገዳም ሔደው፣ በአረጊት ኪዳነ ምሕረት ገዳም ለሰባት ዓመታት ያህል ድጓ አስተምረዋል፡፡ ሥርዐተ ምንኵስናና መንፈሳዊ አገልግሎት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ፣ ሥርዐተ ምንኵስናን ከመምህርነት ጋራ አጣምሮ ለመያዝ ያላቸው ፍላጎት ከፍ ያለ ስለኾነ በጣና ገዳም ዳጋ እስጢፋኖስ በመግባት ማዕርገ ምንኵስናን ከመምህር ኃይለ ማርያም(በኋላ የባሕር ዳር ቅዱስ ጊዮርጊስ መልአከ ገነት) በ1961 ዓ.ም. ከተቀበሉ በኋላ፣ በዚሁ ዓመት ማዕርገ ቅስናን፣ ከጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ ተቀብለዋል፡፡ የገዳምን ሥነ ሥርዐት ይበልጥ ማጥናት ስለፈለጉ፣ በባሕር ዳር አውራጃ ልዩ ስሙ ጋሾላ በተባለ ገዳም ገብተው የገዳሙን ሥነ ሥርዐት እያጠኑና ለገዳማውያን እየታዘዙ ለኹለት ዓመት ገዳሙን ረድተዋል፡፡ በገዳሙ በነበሩበት ጊዜ፣ በጸሎተ ማኅበር፣ የልማት ሥራ በመሥራትና አቅመ ደካሞችን በመርዳት ገዳሙን አገልግለዋል፡፡ ከዚያ በኋላ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት፣ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል፣ በቅዳሴና በማሕሌት እያገለገሉ ትርጓሜ ሐዲሳትንና አቡሻኽርን ተምረዋል፡፡ ዘመናዊ ትምህርታቸውንም በቅድስት ሥላሴ ትምህርት ቤት እስከ ኹለተኛ ደረጃ ተከታትለዋል፡፡ በተጨማሪም ለመምህራን፣ የተደረገውን የስብከት ዘዴ ኮርስ ለኹለት ዓመታት ተምረው የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል፡፡ በቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪነት የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ኾነው በመሾም በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የነበረውን ችግር ተገንዝበው ለአገልጋዮች መኖሪያ ቤት አሠርተውላቸዋል፡፡ የእሑድ(የሰንበት) ት/ቤት ወጣቶችም የመሰብሰቢያ አዳራሽ ስላልነበራቸው አንድ አዳራሽ ከነሙሉ ድርጅቱ አሠርተው በመስጠት ችግራቸውን አቃለውላቸዋል፡፡ ተጀምሮ የነበረው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን እንዲጠናቀቅና በአካባቢው የነበሩ ምእመናንም በሰበካ ጉባኤ እንዲደራጁ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡ ሢመተ ጵጰስና ባላቸው በቂ የቤተ ክርስቲያን ዕውቀትና ባሳዩትም የመንፈሳዊ አገልግሎትና የሥራ ወዳድነት፣ ቤተ ክርስቲያናችን፣ ጥር 13 ቀን 1971 ዓ.ም. ባደረገችው የ13 ኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ፣ በካህናትና በምእመናን በከፍተኛ ድምፅ ተመርጠው የኦጋዴን አውራጃ ኤጲስ ቆጶስ ኾነው ተሾመዋል፡፡ በዚህ አውራጃ፣ በጠላት ፈርሶ የነበረውን ቤተ ክርስቲያን በማሠራትና በማሳደስ፤ በጦርነት ምክንያት የተሸበረውንና የተደናገጠውን ሕዝብ በማጽናናት ስለ ኢትዮጵያ አገሩ ፍቅር በማስተማርና በማስረዳት ሐዋርያዊ ተልእኳቸውን ፈጽመዋል፡፡ ብፁዕ አቡነ መርቆሬዎስ፣ በ1971 ዓ.ም. ወደ ጎንደር ሀገረ ስብከት ተዛውረዋል፡፡ ቅዱስነታቸው በጎንደር ሀገረ ስብከት የፈጸሙአቸው ሥራዎች፡- በወቅቱ በነበረው አለመረጋጋት፣ በጭልጋና በደባርቅ አውራጃዎች እየተዘዋወሩ ሕዝቡን በማስተማር ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክተዋል፡፡ ብፁዕነታቸው በየጊዜው በሚያሳዩት መልካም የሥራ ውጤት፣ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የሊቀ ጵጵስና ማዕርግ ተቀብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ራሷን እንድትችል ለማድረግ ቀዳሚ ተግባር የሚኾነው ምእመናንን በሰበካ ጉባኤ ማደራጀትና ማጠናከር ስለኾነ፣ በሀገረ ስብከት በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የሰበካ ጉባኤን በማቋቋምና በማጠናከር፣ የሰንበት ት/ቤቶችንም በማስፋፋት ቅርሳቅርሶች በክብካቤ እንዲያዙ፣ ቅዱሳት መጻሕፍት፣ መጽሔቶችና ጋዜጦች ለሕዝበ ክርስቲያን እንዲደርሱ፣ የቤተ ክርስቲያን መመሪያና ደንብ ቃለ ዐዋዲ በተግባር እንዲተረጎም አድርገዋል፡፡ በጎንደር ክፍለ ሀገር የፈረሱ አብያተ ክርስቲያናት እንዲታደሱና በርከት ያሉ አዲስ አብያተ ክርስቲያናት እንዲታነፁ አድርገዋል፡፡ በተለይም በደብረ ታቦር አውራጃ በእስቴ ወረዳ፡- የአረጊት ኪዳነ ምሕረትን ቤተ ክርስቲያን በግል ገንዘባቸው ቆርቆሮ እንድትለብስ አድርገዋል፡፡ በዚሁ ወረዳ ውስጥ የምትገኘውን ደብረ ምሕረት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን፣ ከግል ገንዘባቸው ብር 9ሺሕ በማውጣት ቆርቆሮ እንድትለብስ አድርገዋል፡፡ መንፈሳዊ አዳሪ ት/ቤቶች እንዲከፈቱ፣ የካህናት ማሠልጠኛ እንዲቋቋምና ካህናት በተግባረ እድ የሚሠለጥኑበት ት/ቤት እንዲከፈት አድርገዋል፡፡ ምንም መተዳደሪያ ያልነበራቸው የአብነት መምህራንና ሊቃውንት፣ ለክህነት ከሚከፈለው ገንዘብ ደመወዝ እንዲቆረጥላቸው በማመቻቸት ሳይሰለቹና ሳይቸገሩ ሞያቸውን ለትውልድ እንዲያስተላልፉና የሀገረ ስብከቱ ሠራተኞችም በትምህርት አቅማቸውን እንዲያሻሽሉበት አድርገዋል፡፡ ከዚህም ሌላ ለአንድ የዜማ መምህር፣ ለአንድ የቅዳሴ መምህር፣ ለአንድ ዕቃ ቤት ጠባቂ በድምሩ ለሦስት ሰዎች ከራሳቸው ደመወዝ በመክፈል ሓላፊነታቸውን እንዲወጡ አድርገዋል፡፡ በብፁዕነታቸው ሊቀ ጵጵስና፣ 43 አብያተ ክርስቲያናት ተተክለዋል፤185 አብያተ ክርስቲያናት ተሠርተዋል፡፡ የልማት ሥራዎች፤

መሠረተ ግእዝ - Статистика та аналітика Telegram каналу @learngeez1