uk
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Відкрити в Telegram

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Канал የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 484 підписників, посідаючи 6 043 місце в категорії Релігія і духовність та 2 334 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 484 підписників.

За останніми даними від 30 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 530, а за останні 24 години на 23, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 39.14%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 10.20% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 666 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 477 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 33.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 01 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

14 484
Підписники
+2324 години
+1447 днів
+53030 день
Архів дописів
መጻጉዕ ቅዱስ ያሬድ አራተኛውን የዓቢይ ጾም ሳምንት መጻጉዕ ብሎታል። መጻጉዕ ደዌ ለረጅም ዓመታት የጸናበት ህመምተኛን የሚገልጽ ቃል ነው። በዚህ ወቅት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ስለበሽታ ምንነት የሚመጣባቸውን ምክንያቶች እና በበሽታ የተመሰለ ኃጢአትን እንድንርቀው የሚያደርጉ ትምህርቶችን ታስተምርበታለች ፣ ምንባባትን ታነብበታለች ቅዳሴውን ትቀድሳለች ፣ መዝሙሩንም እንዲስማማ አድርጋ አሰናድታ ትዘምራለች። የበሽታ (የደዌ) አይነቶች 1. ደዌ ዘኃጢአት ፡ ይህ ደዌ ሰው ኃጢአት ሲፈጽም ከእግዚአብሔር ሲጣላ እና ከሕግጋቱ በአፍአ ሲሆን የሚመጣበት በሽታ ነው። በዮሐ 5፡1 ጀምሮ 38 ዓመት በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁራኛ እግሩ ሰልሎ የተኛው ሰው (መጻጉዕ) በሽታው ያገኘው ቀድሞ በፈጸመው ኃጢአት መሆኑን ጌታ ሲገልጽ "ከዚህ የባሰ እንዳያገኝህ ደግመህ አትበድል።" በማለት አስጠንቅቆታል። 2. ደዌ ዘጸጋ ፡ ይህ ደዌ ደግሞ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጸጋ ፣ ዋጋ ፣ በረከት የሚያስገኝ ደዌ ነው። እንደ ቅዱስ ኢዮብ ፣ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ያለ ደዌ ከአምላካቸው ጸጋ ዋጋ በረከት ያገኙበት በመሆኑ ደዌ ዘጸጋ እንለዋለን። 3. ደዌ ዘእሴት ፡ ይህ ደዌ ደግሞ ከአገልግሎት ብዛት ሊመጣ የሚችል የደዌ አይነት ነው። ይህም ዋጋ የሚያሰጥ ደዌ ሲሆን በጾም ፣ ረጅም ሰዓት በመስገድ ፣ ለአገልግሎት አቀበቱን በመውጣት ቁልቁለቱን በመውረድ ሊከሰት የሚችል ነው። እንደ ቅዱስ ጢሞቴዎስ ያለ። 1ኛ ጢሞ 5፡22 4. የእግዚአብሔር ክብር የሚገለጥበት ደዌ ፡ አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር ክብሩን የሚገልጽበትን ደዌ ሊሰጠን ይችላል። በዮሐ 9፡1 ጀምሮ ስንመለከት ሲወለድ ጀምሮ እውር የነበረውን ሰው እንደዚያ ሆኖ ለመወለዱ ኃጢአት ያደረገው እርሱ ወይም ወላጆቹ መሆኑን ሐዋርያት በጠየቁት ጊዜ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንም "የእግዚአብሔር ሥራ በእርሱ እንዲገለጥ ነው እንጂ እርሱ ወይም ወላጆቹ ኃጢአት አልሠሩም።" በማለት ሰውዬው በያዘው ደዌ ክብረ እግዚአብሔር እንደሚገለጥ ተናገረ። እግዚአብሔር አምላካችን በደዌ ከተመሰለ ኃጢአት ሁላችንንም በቸርነቱ ይፈውሰን። ለንስሐ ሞት ያብቃን። የስሙ ቀዳሾች የመንግሥቱም ወራሾች ያድርገን። ይቆየን! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

ምኲራብ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ቅዱስ ያሬድ የአብይ ጾም 3ኛ ሳምንትን ምኲራብ በማለት ሰይሞታል። በዚህ ሳምንት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ አይሁድ ምኲራብ ገብ
ምኲራብ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ቅዱስ ያሬድ የአብይ ጾም 3ኛ ሳምንትን ምኲራብ በማለት ሰይሞታል። በዚህ ሳምንት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ አይሁድ ምኲራብ ገብቶ ማስተማሩ ይታሰብበታል። እነዚህንም የሚያሳዩ ምንባባት ፣ ዝምሬ ፣ ስብከት እና ቅዳሴ በዚህ ሳምንት ሲሰበክ ሲቀደስ ሲዘመር ሲታሰብ ይሰነበታል። ከጾመ ድጓ "ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት ፡ ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ።" የሚለው መዝሙር ይዘመራል። በቅዱስ ወንጌሉም ጌታችን ወደ ምኲራብ ገብቶ በዚያ የሚሸጡ የሚለውጡትን እንዳስወጣቸውና ቤቱ የጸሎት ቤት መሆኗን ያወጀበትን የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 2 ከቁጥር 12 ጀምሮ ያለው ታሪክ ይነገርበታል። በምስባኩም "እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ፤ ትዕይርቶሙ ለእለይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ፤ ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡ የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቆአልና ነፍሴን በጾም አስመረርኋት፡፡" የሚለው የዳዊት መዝሙር ይሰበካል። መዝ 68፡9 ይቆየን! መዋዕለ ጾሙን አስፈጽሞ ለብርሃነ ትንሳኤው እንዲያደርሰን የአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን!!! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

ቅዳሜ መጋቢት 3 ቀን 2014 ዓ.ም ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ አስከሬን በመስቀል አደባባይ ሽኝት ይከናወናል!!! ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ቅዳሜ መጋቢት 3 ቀን 2014 ዓ.ም ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ አስከሬን በመስቀል አደባባይ ሽኝት ይከናወናል!!! +++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት በሰጠው መግለጫ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ የሽኝት እና የቀብር ዝርዝር መርሐ ግብርን አስመልክቶ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ሲሆኑ ለቅዱስነታቸው የሽኝትና የቀብር መርሐ ግብር 12 አባላት ያሉት ዐቢይ ኮሚቴና 5 ንዑሳን ኮሚቴዎች መደራጀታቸውን ገልፀዋል። የቅዱስነታቸውን አስከሬን ቅዳሜ መጋቢት 3 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ መስቀል አደባባይ በማሳረፍ ሕዝባዊ ስንብት የሚከናወን እንደሆነም አሳውቀዋል። በማስቀጠልም የቅዱስነታቸው አስከሬን ወደ መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ገዳም ተመልሶ ጸሎተ ወንጌል ከደረሰ በኋላ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጸሎተ ፍትሐት ሲከናወን እንደሚያድር አስረድተዋል። እሁድ መጋቢት 4 ቀን 2014 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ መሪነት ከሌሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ የቅዳሴው ሥነ ሥርዓት ተከናውኖ በዕለቱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ምዕመናን በተገኙበት ግብዓተ መሬቱ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የሚፈፀም መሆኑን አስታውቀዋል። ዜናው የተገኘው ከአዲስ አበባ ሃገረስብከት የቴለግራም ገጽ ነው፡፡ ለተጨማሪ መረጃ የአንድነቱን ማኅበራዊ ድረ-ገጾች ይጎብኙ:- 1. ድረ-ገጽ:- https://eotc-gssu.org/a/ 2. ፌስ ቡክ ገጽ:- https://www.facebook.com/nssu.eotcss 3. ቴሌግራም ቻናል:- https://t.me/EOTCNSSU

የመርሃ ግብር ማስተካከያ፡፡ የካቲት 27 ይከናወናል ተብሎ የነበረው የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሥርዓተ ቀብር እሁድ መጋቢት 4 ቀን 2014 ዓ.ም በመ
የመርሃ ግብር ማስተካከያ፡፡ የካቲት 27 ይከናወናል ተብሎ የነበረው የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሥርዓተ ቀብር እሁድ መጋቢት 4 ቀን 2014 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ። ዜናውን ያገኘነው ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የፌስ ቡክ ገጽ ላይ ሲሆን ይህንን ለማረጋገጥ የመምሪያውን ኃላፊ መምህር አካለወልድ ተሰማን (Dr) በስልክ አነጋግረን ለማረጋገጥ ችለናል፡፡

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር እሁድ የካቲት 27 ቀን እንዲፈፀም ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰኔ አሳለፈ:: +++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር እሁድ የካቲት 27 ቀን እንዲፈፀም ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰኔ አሳለፈ:: +++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ ቅዱስ ሲኖዶስ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ አራተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር እሑድ የካቲት 27 ቀን 2014 ዓ.ም እንዲፈጸም ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ አራተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚከናወን ከኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት የፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ የዜናው ምንጭ የተገኘው ከአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት የቴሌግራም ገጽ ነው፡፡

ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ - በበፊት ስማቸው አባ ዘሊባኖስ ፈንታ የሚባሉት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ፣ በጎንደር ክፍለ ሀገር በደብረ ታቦር አውራጃ በአለታ ወረዳ አረጊት ኪዳነ ምሕረት በተባለችው ገዳም ሰበካ፣ ልዩ ስሙ ማር ምድር በ1930 ዓ.ም.፣ ከብላታ ፈንታ ተሰማና ከወ/ሮ ለምለም ገሰሰ ተወለዱ፡፡ - ማዕርገ ምንኵስናን በጣና ገዳም ዳጋ እስጢፋኖስ በመግባት ከመምህር ኃይለ ማርያም (በኋላ የባሕር ዳር ቅዱስ ጊዮርጊስ መልአከ ገነት) በ1961 ዓ.ም. የተቀበሉ ሲሆን፣ በዚሁ ዓመት ማዕርገ ቅስናን፣ ከጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ ተቀብለዋል፡፡ - ባላቸው በቂ የቤተ ክርስቲያን ዕውቀትና ባሳዩትም የመንፈሳዊ አገልግሎትና የሥራ ወዳድነት፣ ቤተ ክርስቲያኗ ጥር 13 ቀን 1971 ዓ.ም. ባደረገችው የ13 ኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ፣ በካህናትና በምእመናን በከፍተኛ ድምፅ ተመርጠው የኦጋዴን አውራጃ ኤጲስ ቆጶስ ኾነው ተሾመዋል፡፡ - ብፁዕ አቡነ መርቆሬዎስ፣ በ1971 ዓ.ም. ወደ ጎንደር ሀገረ ስብከት ተዛውረዋል፡፡ - ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ፣ 4ኛ ፓትርያርክ ኾነው የተሾሙት፣ ነሐሴ 29 ቀን 1980 ዓ.ም. ሲኾን፣ በፖሊቲካዊ ግፊትና ጫና መንበራቸውን ለቀው ከሀገር ከመውጣታቸው በፊት እስከ ነሐሴ 28 ቀን 1983 ዓ.ም. ድረስ ለቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ አመራር ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ - ከ26 ዓመታት ስደት በኋላ፣ ሐምሌ 25 ቀን 2010 ዓ.ም.፣ በስሙ በተሠየሙበት በሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ክብረ በዓል ወደ ቅድስት ሀገራቸው ኢትዮጵያ መመለሳቸውን፣ ይታወቃል፡፡ - አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከቀናት በፊት ህመም አጋጥሟቸው በሃሌሉያ ሆስፒታል በህክምና ላይ የነበሩ ሲሆን ዛሬ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተነግሯል። የቅዱስነታቸው በረከት በሁላችን ላይ ይደር፡፡ የዜናው ምንጭ TIKVAH-MAGAZINE

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ከዚሀ ዓለም ድካም አርፈዋል። በረከታቸው ትድረሰን።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ከዚሀ ዓለም ድካም አርፈዋል። በረከታቸው ትድረሰን።

እንኳን ለአድዋ የድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 h
እንኳን ለአድዋ የድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU

እንኳን ለታላቁ የዐቢይ ጾም በሰላም በጤና አደረሳችሁ!! ጾሙ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ እንዲሁም ለሰው ልጆች ሰላም እና ለተቸገሩ ሁሉ መጽናናት የምናገኝበት እንዲሆንልን አምላ
እንኳን ለታላቁ የዐቢይ ጾም በሰላም በጤና አደረሳችሁ!! ጾሙ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ እንዲሁም ለሰው ልጆች ሰላም እና ለተቸገሩ ሁሉ መጽናናት የምናገኝበት እንዲሆንልን አምላካችን በቸርነቱ ይርዳን! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

በላኢ ሰብ እና እሥራኤል ዘሥጋ በታሪክ እንደሚታወቀው እሥራኤል ዘሥጋ በግብጽ ባርነት ለ430 ዓመት ተገዝተው ነበር፡፡ እግዚአብሔርም የሲዖል ምሳሌ ከምትሆን ግብጽ በዘጠኝ ታላላቅ ተዓምራት በአሥረኛ ሞተ በኵር በአሥራ አንደኛ ስጥመተ ባሕር ግብጽን በመቅሰፍ ነጻ አውጥቷቸዋል፡፡ እስራኤል ዘሥጋ ግን ይህንን ታላቅ ውለታ በማሰብ ፈንታ አምላካቸው እግዚብሔርን አሳዘኑ ቀልጦ ለተሠራ ጣዖት ሰገዱ ሰዉለትም፡፡ ‹‹እስራኤል ሆይ ስማ እነዚህ ከግብጽ ምድር ያወጡህ አማልክትህ ናቸው አሉ፡፡›› ዘጸ 32፡1-14 መዝ 105፡23 የእግዚአብሔርም ቁጣ በሕዝቡ ላይ ነደደ፡፡ ያጠፋቸውም ዘንድ ከተመረጠው መስፍን ከሊቀ ነቢያት ሙሴ ጋር መከረ፡፡ ‹‹ይህንን ህዝብ አየሁት እነሆ አንገተ ደንዳና ነው፡፡ አሁንም ቁጣዬ እንዲቃጠልባቸው እንዳጠፋቸውም ተወኝ፡፡ አንተ ግን ለታላቅ ሕዝብ አደርግሃለው፡፡›› አለው፡፡ ዘጸ 32፡9-10 ሙሴም ሕዝቡን እንዳያጠፋቸውና ከቁጣው ይመለስ ዘንድ ስለ ሕዝቡ ያማልድ ጀመር፡፡ በተለይም እግዚአብሔር ከቅዱሳኑ ከአብርሃም ከይስሐቅ እና ከያዕቆብ ጋር የገባውን ቃልኪዳን ያስብ ዘንድ ለመነ፡፡ ‹‹ዘራችሁን እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደ ምድር አሸዋ አበዛዋለው፡፡ ይህችንም የተናገርኳትን ምድር ለዘራችሁ ሁሉ እሰጣለው፡፡ ለዘላለምም ይወርሷታል ብለህ በራስህ የማልክላቸውን አብርሃምንና ይስሐቅን እስራኤልንም አስብ፡፡›› አለው፡፡ ዘጸ 32፡13 እግዚአብሔርም የቅዱሳኑ ስም ተጠርቶ ሲሰማ የገባላቸውን ቃል ኪዳን አሰበ፡፡ በሕዝቡ ላይ ሊያደርገው ስለነበረው መቅሰፍት ፈጽሞ ራራላቸው፡፡ ይቅርም አላቸው፡፡ ‹‹ከመረጥኳቸው ጋር ቃልኪዳኔን አደረግሁ፡፡›› ያለ አምላክ ከተመረጡት ቅዱሳን ከአብርሃም ከይስሐቅ ከያዕቆብና ከሌሎችም ቅዱሳን ጋር ቃልኪዳኑን እንዳደረገ እንዲሁ ከተመረጡ የተመረጠች ከተለዩ የተለየች ከእናታችን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያምም ጋር እንዲሁ ቃልኪዳኑን በዛሬው ዕለት የካቲት 16 ቀን አድርጓል፡፡ እመቤታችንም ‹‹መታሰቢያዬን የሚያደርገውን፣ በስሜ ቤተ ክርስቲያን የሚያንጸውን ፣ የተራቆተ የሚያለብሰውን፣ በሽተኛ የሚጎበኘውን፣ የተራበ የሚያበላውን፣ የተጠማ የሚያጠጣውን፣ ያዘነን የሚያረጋጋውን የተበሳጨ የሚያስደስተውን፣ መመስገኛየን የጻፈና ያጻፈ ፣ ወንድ ወይም ሴት ልጁን በስሜ የሰየመውን፣ በምመሰገንበት ቀን ዝማሬ ያቀረበውን ዓይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን የሰው ኅሊና ተመራምሮ ያልደረሰበትን መልካም ዋጋ ትሰጥልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡›› ብትለው፡ ጌታም ‹‹መሃልኩ ለኪ በርዕስየ በከመ ኢይሔሱ ኪዳንየ›› ያልሽውን ሁሉ ላደርግልሽ ቃል ኪዳኔንም ልጠብቅልሽ በራሴ ማልሁልሽ በማለት የምህረት ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡ የአብርሃም የይስሐቅ እና የያዕቆብ ቃልኪዳን የእግዚአብሔርን ሕልውና ለካዱ ቀልጦ ለተሠራ ጣዖት ለሠገዱ ለእስራኤል ዘሥጋ መትረፉን መጽሐፍ ቅዱስ ከነገረን በተዓምረ ማርያም ላይ ደግሞ ስምዖን በግብር ስሙ በላኢ ሰብ 70 ሰዎችን በልቶ በቃልኪዳኗ ተጠቅሞ መዳኑን ይነግረናል፡፡ እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ቃልኪዳን የማይሆነውን እንዲሆን የሚሆነን ደግሞ እንዳይሆን ያደርጋል፡፡ ያጠረውን ያስረዝማል፡፡ የረዘመውን ያሳጥራል፡፡ ኃጥኡን ያጸድቃል፡፡ ዛሬም እስራኤል ዘነፍስ የምንሆን እኛ ክርስቲያኖች በእመቤታችን ቃልኪዳን በመታመን ሀገራችን ላይ እና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ላይ የተቃጣውንና እየደረሰ ያለውን መከራ እርሱ በቸርነቱ ያርቅልን ዘንድ ስለ እናትህ ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ብለህ ማረን ይቅር በለን እያልን ተግተን ልንለምነው ይገባል፡፡ የአብርሃም የይስሐቅ የያዕቆብ ስም ሲነሳ በእስራኤል ዘሥጋ ላይ ያልጨከነ ለድካማቸውም የራራ አምላካችን የእናቱን ስም ጠርተን በቃልኪዳኗ ብናምለው እንደምን አይራራልንም? ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

እንኳን ለመዋለ ጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ! ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን በመዋለ ስብከቱ ጸሐፍት ፈሪሳዊያን ከጠየቁት ጥያቄ በመነሳት ስለ ሰብዓ ነነዌ እንዲህ በማለት ተናግሮ ነበር። "በዚያን
እንኳን ለመዋለ ጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ! ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን በመዋለ ስብከቱ ጸሐፍት ፈሪሳዊያን ከጠየቁት ጥያቄ በመነሳት ስለ ሰብዓ ነነዌ እንዲህ በማለት ተናግሮ ነበር። "በዚያን ጊዜ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን አንዳንዶቹ መለሱና፦ መምህር ሆይ፥ ከአንተ ምልክት እንድናይ እንወዳለን አሉ። እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው፦ ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፥ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም። ዮናስ በዓሣ አንባሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ፥ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል። የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፥ እነሆም፥ ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ።" ማቴ 12፡38-41 ቀድሞ አምላካቸውን ያሳዘኑት ሰብዓ ነነዌ (የነነዌ ሰዎች) ስለ ኃጢአታቸውና ስለ በደላቸው ምህረትን ጠይቀው ንስሐ ገብተው ሦስት ቀን ጾመው ጸልየው በአምላካቸው እስኪመሰከርላቸውና በትውልዱም ላይ ለመፍረድ ሥልጣኑን እስኪሰጣቸው ድረስ ይቅርታውን ምሕረቱን ቸርነቱን እንደገለጠላቸው እኛም ጾሙን ጾመን ንስሐ ገብተን አምላካችን ይቅር ይለን ዘንድ ተግተን እንለምነው። ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

AnimatedSticker.tgs0.41 KB

እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ዕረፍት አስተርዮ ማርያም በሰላም አደረሳችሁ!! "ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው። በዚህች ቀን
እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ዕረፍት አስተርዮ ማርያም በሰላም አደረሳችሁ!! "ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው። በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው። በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው። በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ። አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት የተለያየ ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ።" (ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ) መልካም በዓል!! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ Website 👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️ Facebook 👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU

መንፈሳዊ በዓል ለማክበር በወጡ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚደርስ ጥቃትን አጥብቀን እንቃወማለን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአደባባይ ከምታከብራቸው በዓላት መካከል አንዱ የሆነውን የጥምቀት በዓል እና የቃና ዘገሊላ በዓልን በመላ ሃገሪቱ በሚባል ደረጃ በሠላም ለማክበር የተቻለ ሲሆን ለዚህ ደግሞ ቤተክርስቲያኒቱ እና አማኞቿ በጋራ ላሳዩት ኦርቶዶክሳዊ ሥነ ስርዓትና ለጸጥታ ኃይሉ ባሳዩት መልካም ትብብር ሊመሰገኑ ሲገባቸው ጥር 12 ቀን 2014 ዓ.ም በየሺ ደበሌ አካባቢ በምትገኘው የወይብላ ማርያም ታቦትን አክብረው በሚመለሱ ካህናት ፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች እና አዛውንት፣ ጎልማሳና ወጣት ምዕመናን ላይ ለጸጥታ ማስከበር ስራ በተሰማራ የጸጥታ አካል ኃይል የተሞላበት ጥቃት ምክንያት የደረሰው ችግር በተደጋጋሚ አንድ አካባቢ ሆነ ተብሎ ሃይማኖታዊ ሥርዓታቸውን የሚፈጽሙ ክርስቲያኖችን ከማወክ አልፎ ለሞት መዳረጉ በቤተክርስቲያናችን ላይ የሚድረስውን በደል የሚያሳይ ኢ ሰብአዊ ና ኢ ፍትሃዊ ድርጊት በመሆኑ የሰንበት ት/ ቤቶች አንድነት በጽኑ ይቃወማል። ድርጊቱ ባለፈው ዓመትም የተከናወነ በመሆኑ ከባለፈው አመት ተመክሮ በመነሳት ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን እና የጸጥታ አካላት ጋር በዓሉ በሰላም ለማክበር ሰፊ ውይይት በማድረግ ሁሉም ድርሻውን ለመወጣት ኃላፊነት ተወስዶ በዚያ መልኩ ቢፈጸምም በቦታው ዘንድሮም በድጋሜ የተፈጠረ መሆኑ በአጋጣሚ የተፈጠረ ክስተት ሳይሆን የመንግስትን ስልጣን ተጠቅመው ቤተ ክርስቲያኒቱን የሚያጠቁ አካላት ትልቅ ማሳያ በመሆኑ መንግስት አስቸኳይ ማስተካከያ እርምጃ እንዲወስድ እንዲሁም በድርጊቱ በቀጥታ የተሳተፉና ትዕዛዝ በመስጠት ያስፈጸሙ አካላትን በሕግ አግባብ እንዲጠየቁና ውጤቱን ለህዝቡ ይፋ እንዲያደርግ እያሳሰብን በዚህ ሂደት ለተፈጠረው ችግር የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን በቀጣይ ሙሉ ሂደቱን እና ቀጣይ ሥራዎችን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!!! የሀገር አቀፍ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጥር 13 ቀን 2014 ዓ.ም https://t.me/EOTCNSSU

መንፈሳዊ በዓል ለማክበር በወጡ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚደርስ ጥቃትን አጥብቀን እንቃወማለን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአደባባይ ከምታከብራቸው በዓላት መካከል አንዱ የሆነውን የጥምቀት በዓል እና የቃና ዘገሊላ በዓልን በመላ ሃገሪቱ በሚባል ደረጃ በሠላም ለማክበር የተቻለ ሲሆን ለዚህ ደግሞ ቤተክርስቲያኒቱ እና አማኞቿ በጋራ ላሳዩት ኦርቶዶክሳዊ ሥነ ስርዓትና ለጸጥታ ኃይሉ ባሳዩት መልካም ትብብር ሊመሰገኑ ሲገባቸው ጥር 12 ቀን 2014 ዓ.ም በየሺ ደበሌ አካባቢ በምትገኘው የወይብላ ማርያም ታቦትን አክብረው በሚመለሱ ካህናት ፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች እና አዛውንት፣ ጎልማሳና ወጣት ምዕመናን ላይ ለጸጥታ ማስከበር ስራ በተሰማራ የጸጥታ አካል ኃይል የተሞላበት ጥቃት ምክንያት የደረሰው ችግር በተደጋጋሚ አንድ አካባቢ ሆነ ተብሎ ሃይማኖታዊ ሥርዓታቸውን የሚፈጽሙ ክርስቲያኖችን ከማወክ አልፎ ለሞት መዳረጉ በቤተክርስቲያናችን ላይ የሚድረስውን በደል የሚያሳይ ኢ ሰብአዊ ና ኢ ፍትሃዊ ድርጊት በመሆኑ የሰንበት ት/ ቤቶች አንድነት በጽኑ ይቃወማል። ድርጊቱ ባለፈው ዓመትም የተከናወነ በመሆኑ ከባለፈው አመት ተመክሮ በመነሳት ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን እና የጸጥታ አካላት ጋር በዓሉ በሰላም ለማክበር ሰፊ ውይይት በማድረግ ሁሉም ድርሻውን ለመወጣት ኃላፊነት ተወስዶ በዚያ መልኩ ቢፈጸምም በቦታው ዘንድሮም በድጋሜ የተፈጠረ መሆኑ በአጋጣሚ የተፈጠረ ክስተት ሳይሆን የመንግስትን ስልጣን ተጠቅመው ቤተ ክርስቲያኒቱን የሚያጠቁ አካላት ትልቅ ማሳያ በመሆኑ መንግስት አስቸኳይ ማስተካከያ እርምጃ እንዲወስድ እንዲሁም በድርጊቱ በቀጥታ የተሳተፉና ትዕዛዝ በመስጠት ያስፈጸሙ አካላትን በሕግ አግባብ እንዲጠየቁና ውጤቱን ለህዝቡ ይፋ እንዲያደርግ እያሳሰብን በዚህ ሂደት ለተፈጠረው ችግር የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን በቀጣይ ሙሉ ሂደቱን እና ቀጣይ ሥራዎችን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!!! የሀገር አቀፍ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጥር 13 ቀን 2014 ዓ.ም https://t.me/EOTCNSSU