uk
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Відкрити в Telegram

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Канал የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 479 підписників, посідаючи 6 043 місце в категорії Релігія і духовність та 2 334 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 479 підписників.

За останніми даними від 30 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 530, а за останні 24 години на 23, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 39.14%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 10.20% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 666 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 477 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 33.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 01 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

14 479
Підписники
+2324 години
+1447 днів
+53030 день
Архів дописів
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት: በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ!!! በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በፍትሕ መንፈሳዊ እንዲሁም በሕገ ቤተክርስቲያን አንቀጽ 19 ንዑስ ቁጥር 3 አስቸኳይና ድንገተኛ ጉዳይ ሲያጋጥም ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያደርግ በተደነገገው መሠረት ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ በተፈጠረው ወቅታዊ የሃይማኖት፣ የቀኖና እና የአስተዳደራዊ ጥሰቶችን አስመልክቶ ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡ ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊትና ዓለም አቀፋዊት የሆነች ቅድስት ቤተክርስቲያን ሕዝብና አሕዛብን፣ ሰውና መላእክትን፣ ፍጡራን እና ፈጣሪን ይልቁንም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ልዩነት አጥፍቶ የሰው ልጅ ሁሉ በቋንቋ፣ በቀለምና በጐሣ ሳይከፋፈሉ በአንድነት ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና አግኝተው ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማህፀነ ዮርዳኖስ የተወለዱ በማየ ገቦ የተጠመቁ የቤተ ክርስቲያን ልጆች እንዲሆኑ ልዩነት የሌለባትን ዘለዓለማዊት መንግሥተ እግዚአብሔር እንዲወርሱ በደመ ክርስቶስ የተመሠረተች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ የተነሣባትን ፈተና ሁሉ አልፋ ከእኛ ዘመን ደርሳለች፤ ምንም እንኳ ከቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ ከኦርቶዶክስ ትምህርተ ሃይማኖት ፈጽሞ በተለየ ሁኔታ ቤተ ክርስቲያንን በጐሣና በቋንቋ የመለየት ሂደት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንግዳ ክስተት ቢሆንም ቤተ ክርስቲየን ከሃይማኖታዊና መንፈሳዊ ጠባይዋ በተለየ፣ ታሪኳንና ሥርዓቷን በማይመጥን፣ ከሕግ መንፈሳዊ፣ ከሕግ ጠባይአዊ እና ከሕገ አእምሮ በወጣ መልኩ የደረሰባት ጥቃት፣ እና የመፈንቅለ ሲኖዶስን ተግባር ቅዱስ ሲኖዶስን እጅግ አሳዝኖታል፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ ውስጥ ለሀገር አንድነት፣ ለፍትሕ፣ ለጥበብ፣ ለሕዝብ ትስስር፣ ለማኅበራዊ ዕድገት፣ ለጤና፣ ለሥነ-ምግባር መሠረት እና ዐምድ፤ ምሰሶ እና ማገር ሆና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተፈራች፣ የተከበረች እና የተወደደች፤ ዕሴቷ እና ዕምቅ የዕውቀት ሀብቷ በምሁራን የታወቀ፣ በትምህርተ ዓለም ሳይቀር የተቀረጸ፤ በእውነተኛ ሊቃውንት የተመሠከረ፣ ቅርሶቿ የተመዘገቡላት ስትሆን፤ በቅርቡ ራስዋ በሾመቻቸው በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ከፍተኛውና ሐዋርያዊ ተልእኮ እንዲወጡ አደራ በተሰጣቸው ሊቃነ ጳጳሳት መሠረተ እምነትን፣ ሃይማኖታዊ ቀኖናን፣ የአስተዳደር ሥርዓት ሁሉ በጣሰ፣ መንገድ በማኅበረሰብ ዕድገትና አስተዳደር ውስጥ ከሕዝብ ጋር የቆመች፣ ከፖለቲካ የጸዳች መንፈሳዊና ሕዝባዊት ተቋምነቷን በመካድ ከፍተኛ የሆነ ሕገ ወጥ ድርጊት፣ ተቋምን የመናድና መዋቅሯን የማፍረስ ተግባር ተከናውኗል፡-  በዚሁ መሠረት፡- ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ዳጡ ወረዳ ከወሊሶ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው አሮ ባለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተፈጸመውን እጅግ አሳዛኝ እና ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ አስነዋሪ፤ ሕገ ወጥ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አስመልከቶ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት አስቸኳይ የምልዐተ ጉባዔ አድርጓል፤ ቅዱስ ሲኖዶስም በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ያሉ መላው አህጉረ ስብከት፤ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባዔ፣ የሊቃውንተ ጉባኤ፤ የሕግ አገልግሎት መምሪያ፤ በዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የወጣቶች እና የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት፣ መንፈሳውያን ማኅበራት፤ የምእመናን እና አገልጋዮች ኅብረት፣ ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በደብዳቤ፣ በሚዲያ እና በአካል ከሰጡት ምክረ ሐሳብ እና የአቋም መግለጫ በመነሣት፤ በሀገር ውስጥ እና በውጪው ዓለም የሚገኙ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ወዳጆች፣ በተለይም የግብጽ እስክንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶከስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ፓትርያርክ ውጭ የሚደረግ ሢመትን እንደማይቀበሉና ዕውቅና እንደማይሰጡ በላኩት የአቋም መግለጫ፣ የኤርትራ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የሕንድ ማላንካራ ኦርቶዶከስ ቤተ ክርስቲያን፣ እና የሌሎች አኀት ኦርቶዶከስ አብያተ ክርስያናት፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፣ ዓለም አቀፍ መንፈሳዉያን ተቋማት፣ የልማት እና የበጎ አድርጎት አጋር ድርጅቶች፤ ድርጊቱን በማውገዝ የማይቀበሉት መሆኑን የአቋም መግለጫ በመላክ ባሳዩት አጋርነት፤ አስቀድሞ እንደተገለጸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በደመ ክርስቶስ ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈተና የኖረችበት ጊዜ እንደሌለ ቅዱሳት መጻሕፍትና የታሪክ መዛግብት ሲመሰክሩ በዘመነ ሐዋርያት ቢጽ ሐሳውያን፣ በዘመነ ሊቃውንት የተለያዩ መናፍቃን፣… በየጊዜው እየተነሡ ሲፈታተኗት ኑረዋል፡፡ አሁንም በግልጽ እንደሚታየው ከውጭም ከውስጥም በተደራጁ ምንደኞች በመፈተን ላይ ትገኛለች፡፡ ለዚህም ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም. በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ በሶዶ ዳጩ ወረዳ፣ ሀሮ በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአባ ሳዊሮስ መሪነት እጅግ አሳዛኝ ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ አስነዋሪ፣ ሕገ-ወጥ፣ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አንዱ ሲሆን፤ በአባ ሳዊሮስ መሪነት የተፈጸመው የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት ፳፮ መነኰሳትን ከቀኖና የወጣ ሢመት በመስጠትና ሊቃነ ጳጳሳት በሚመሯቸው አህጉረ ስብከት በሕገ ወጥ መንገድ በመመደብ ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አልፎ ሃይማኖትን የሚከፋፍል፤ የሀገር አንድነትን የሚሸረሽር እና የሚያፈርስ፣ ምእመናንን ከምእመናን፣ ካህናትን ከካህናት፣ ሊቃውንትን ከሊቃውንት ወጣትን ከወጣት … የሚያጋጭና ደም የሚያፋስስ ፀጥታን የሚያናጋ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ተገንዝሟል፤ በመሆኑም፤ - ከላይ እንደተገለጸው ሐዋርያት በሦስተኛው ቀሌምንጦስ በሃያ አምስተኛው አንቀጽ “በአውራጃው ሁሉ ያሉ ኤጲስ ቆጶሳት አለቃቸው ማንም እንደሆነ ማወቅ ይገባቸዋል፡፡ አለቃ ያድርጉት፤ ያለ ፍቃዱ ጥቃቅኑንም ደጋጉንም ሥራ ምንም ምን አይሥሩ፤ እርሱም ዳግመኛ ኤጲስ ቆጶሳቱ ሳይፈቅዱ ደጋጉን ሥራ አይሥራ ጥቃቅኑን ቢሠራ እዳ የለበትም፡፡ ሁሉም እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ ሁነው በአንድነት ይኑሩ” ብለው ወስነዋል፡፡ እነዚህ ሕገ ወጥ አካላት ይህን የሐዋርያት ቀኖናን በመሻራቸው፡፡ - ሁለተኛም በአርባ አራተኛው አንቀጽ “ሊቀጳጳሳት (ፓትርያርክ) ኤጲስ ቆጶሳት በተሾሙባቸው አገሮች የሚሠሩትን ሥራ፣ የሚያዙትን ትእዛዝ ይመርምር፡፡ የማይገባ ሥራ ሠርተው፣ የማይገባ ትእዛዝ አዝዘው፣ ቢያኝ ለውጦ የተገለጸለትን ትእዛዝ ይዘዝ፡፡ እርሱ ለሁሉ የሹመት አባታቸው ነውና፤ እነሱም ልጆቹ ናቸውና…” ብለዋል፡፡ ይህን ኢ-ቀኖናዊ ሥርዐተ ሲመት የፈጸሙት ግለሰቦች በሕገወጥ መንገድ በአደባባይ የቅዱስ ሲኖዶስን ሉዓላዊ ሥልጣን እና የቅዱስ ፓትርያርኩን መብት በመጣሳቸው፡፡ - ሢመተ ክህነትን በተመለከተ “ወአልቦ ዘይነሥእ ክብረ ለርእሱ ዘእንበለ ዘጸውዖ እግዚአብሔር … እንደ አሮን በእግዚአብሔር ከተጠራ በቀር ማንም ለራሱ ክብርን የሚወስድ የለም” (ዕብ 5፤4) እንደሚለው የእግዚአበሔር ቃል ከዲቁና ጀምሮ እስከ ፓትርያርክ ሹመት ድረስ ያለው ሹመት በመጀመሪያ ከእግዚአብሔር መጠራቱን የሚጠይቅ ሲሆን እንኳንስ ለተሿሟዎች ለመራጮችና ለአስመራጮች በቀኖና ቤተ ክርስቲያን የተወሰነ፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መስፈርት ያለው፣ መሆኑ ለሁሉም ግልጽ ነው፡፡ ይህንም ቅዱስ ጳውሎስ

መረጃ ስለመስጠት !! ጥር 17/2015 ዓ.ም በሁሉም አህጉረ ስብከቶች የምትገኙ ሰንበት ት/ቤቶች በሙሉ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም የተፈፀመውን ሕገ ወጥ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት
+1
መረጃ ስለመስጠት !! ጥር 17/2015 ዓ.ም በሁሉም አህጉረ  ስብከቶች የምትገኙ  ሰንበት ት/ቤቶች በሙሉ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት  ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም የተፈፀመውን  ሕገ ወጥ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትን በተመለከተ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ ሲሆን ከዚህም መካከል :- ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ግብዓት የሚሆን የችግሩን መንስኤና መፍትሔ የሚጠቁም ምክረ ሀሳብ በማዘጋጀት ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት  በጽሁፍ አስገብተናል :: እንዲሁም  ከቤተ ክርስቲያን ባለ ድርሻ አካላት ጋር በመናበብ የጋራ ሥራዎችም  ይከናወን ጀምረናል፡፡ ስለዚህ  ሁላችንም ከአጥቢያ ጀምሮ ባለው መዋቅር ከሚመለከታቸው የቤተ ክህነት መዋቅር፣ ማኅበራት እና ምዕመናንን ጋር በመናበብ  ቤተ ክርስቲያናችንና አካባቢያችንን በንቃት የመጠበቅና አስፈላጊ የሆኑ ሥራዎችን  የማከናወን ሥራ  ከእኛ የሚጠበቅ መሆኑን እየገለጽን ፤በቀጣይ ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነት የሚጠቅሙ ሥራዎችን እየለየን በመዋቅራት የምናሳውቅ መሆኑን እየገልጽን በያለንበት በጸሎትና በጽናት አገልግሎታችን  እንድቀጥል እናሳስባለን፡፡ "ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ። ከብዙ ጊዜ በፊት ለዚህ ፍርድ የተጻፉ አንዳንዶች ሰዎች ሾልከው ገብተዋልና፤ ኃጢአተኞች ሆነው የአምላካችንን ጸጋ በሴሰኝነት ይለውጣሉ ንጉሣችንንና ጌታችንንም ብቻውን ያለውን ኢየሱስ ክርስቶስን ይክዳሉ።…. እንዲሁም እነዚህ ሰዎች ደግሞ እያለሙ ሥጋቸውን ያረክሳሉ ጌትነትንም ይጥላሉ ሥልጣን ያላቸውንም ይሳደባሉ "።የይሁዳ መልእክት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

መረጃ ስለመስጠት !! ጥር 17/2015 ዓ.ም በሁሉም አህጉረ ስብከቶች የምትገኙ ሰንበት ት/ቤቶች በሙሉ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም የተፈፀመውን ሕገ ወጥ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት
መረጃ ስለመስጠት !! ጥር 17/2015 ዓ.ም በሁሉም አህጉረ  ስብከቶች የምትገኙ  ሰንበት ት/ቤቶች በሙሉ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት  ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም የተፈፀመውን  ሕገ ወጥ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትን በተመለከተ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ ሲሆን ከዚህም መካከል :- ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ግብዓት የሚሆን የችግሩን መንስኤና መፍትሔ የሚጠቁም ምክረ ሀሳብ በማዘጋጀት ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት  በጽሁፍ አስገብተናል :: እንዲሁም  ከቤተ ክርስቲያን ባለ ድርሻ አካላት ጋር በመናበብ የጋራ ሥራዎችም  ይከናወን ጀምረናል፡፡ ስለዚህ  ሁላችንም ከአጥቢያ ጀምሮ ባለው መዋቅር ከሚመለከታቸው የቤተ ክህነት መዋቅር፣ ማኅበራት እና ምዕመናንን ጋር በመናበብ  ቤተ ክርስቲያናችንና አካባቢያችንን በንቃት የመጠበቅና አስፈላጊ የሆኑ ሥራዎችን  የማከናወን ሥራ  ከእኛ የሚጠበቅ መሆኑን እየገለጽን ፤በቀጣይ ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነት የሚጠቅሙ ሥራዎችን እየለየን በመዋቅራት የምናሳውቅ መሆኑን እየገልጽን በያለንበት በጸሎትና በጽናት አገልግሎታችን  እንድቀጥል እናሳስባለን፡፡ "ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ። ከብዙ ጊዜ በፊት ለዚህ ፍርድ የተጻፉ አንዳንዶች ሰዎች ሾልከው ገብተዋልና፤ ኃጢአተኞች ሆነው የአምላካችንን ጸጋ በሴሰኝነት ይለውጣሉ ንጉሣችንንና ጌታችንንም ብቻውን ያለውን ኢየሱስ ክርስቶስን ይክዳሉ።…. እንዲሁም እነዚህ ሰዎች ደግሞ እያለሙ ሥጋቸውን ያረክሳሉ ጌትነትንም ይጥላሉ ሥልጣን ያላቸውንም ይሳደባሉ "።የይሁዳ መልእክት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

የቅዱስ ሲኖዶስ መልዕክት """"""""""""""""""""""""" ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዩወርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመላው ዓለም ለሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት በየትኛውም የዓለማችን ክፍል የሚገኙ አበው ሊቃነ ጳጳሳት በቤተ ክርስቲያናችን ላይ በተፈጸመው የቀኖና ጥሰትና ሕገ ወጥ ድርጊት ዙሪያ ለመወያየት በየትኛውም የዓለማችን ክፍል የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገራቸው እንዲገቡ ጥሪ መተላለፉን አስታውሰው በአየር ትራንስፖርቱ ዘርፍ በጉዞአቸው ላይ ችግር እንዳይገጥማቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቅድሚያ እንዲሰጣቸው ከቤተ ክርስቲያናችን በቀረበው ጥሪ መሠረት አየር መንገዱ ፍጹም ፈቃደኛና ተባባሪ መሆኑን አረጋግጧል ። የኢትዮጵያ አየር መንገድም የቤተ ክርስቲያንን ጥሪ ተቀብሎ ፈቃደኛነቱን በመግለጹ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልባዊ ምስጋናዋን እያቀረበች በየትኛውም የዓለማችን ክፍል የምትገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት አየር መንገዱ የሰጠውን እድል በመጠቀም ወደ ሀገራችሁ በመምጣት ቤተክርስቲያናችን በረጅም ዘመን አገልግሎቷና በታሪኳ ገጥሟት የማያውቀውን ችግር በጋራ ሆነን እንፍታ በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መግለጫ
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መግለጫ

እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው:: የማቴ 28:19
እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው:: የማቴ 28:19

ያን ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዬሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ ::
ያን ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዬሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ ::

🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።   " ኅየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ "     {"በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ" }  [ መዝ.፵፬፥፲፮ ] በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ በ ፳፻፲፬ ዓ.ም/2014 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ትምህርታቸውን  ተከታትለው  ያጠናቀቁ እና በሀገረ ስብከት በብሔራዊ ደረጃ  በአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ምዘና ተደርጎላቸው ያለፉ  የ ፬ [4] ኛ , የ፮ [6] ኛ እና የ፲ [10] ኛ ክፍል ተማሪዎች የዕውቅና መስጠት መርሐ ግብር !!! ------------------------------------- ጥር ፮ [ 6 ]  ፳፻፲፭ [ 2015 ] ዓ.ም  - ከቀኑ 6:30 ሰዓት ጀምሮ  - በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ 📌 በዕለቱ የሚኖሩ ሌሎች መርሐ-ግብሮች 💧 በ፳፻፲፬ ዓ.ም [ 2014 ዓ.ም ] በክረምት መርሐግብር  በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የተማሩ የተተኪ መምህራን ምርቃት ፤ 💧በሰንበት ት/ቤቶች  አንድነት ለሥርዓተ ትምህርቱ ማስተማሪያ የተዘጋጁ መጻሕፍት ገለጻ  ፤ 💧 በ፳፻፲፭ ዓ.ም [ 2015 ዓ.ም ] የመስቀል ደመራ  በዓል ላይ ትርዒት እና መዝሙር ላቀረቡ የየሰንበት ት/ቤቱ አባላት እና ባለድርሻ አካላት የዕውቅና መርሐ ግብር  ፤  በተጨማሪም የተለያዩ መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች ተሰናድተዋል። 📌 እርስዎም በዚህ ልዩ መርሐግብር ላይ ጥር 6/2015 ዓ.ም ከቀኑ 6:30 ሰዓት ጀምሮ በሚሊኒየም አዳራሽ ተገኝተው የመርሐግብሩ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን! [ የአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ] ✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥

እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ !!! በዓሉ በሃይማኖታችን የምንፀናበት እና ለሀገራችን ፍፁም ሰላም የምናገኝበት ያድርግል ::
እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ !!! በዓሉ በሃይማኖታችን የምንፀናበት እና ለሀገራችን ፍፁም ሰላም የምናገኝበት ያድርግል ::

ዛሬ ምሽት 2፡00 በEOTC Tv ይከታተሉን። ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ Facebook 👇 http://face
ዛሬ ምሽት 2፡00 በEOTC Tv ይከታተሉን። ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

" ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ" መዝ ፵፭÷፲ ✔️ ይህ ቅዱስ ዳዊት ልጁ ስለምትሆን የአለም ሁሉ እናት ስለሆነች አምላክን ለመውለድ ስለተመረጠች ስለቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተመቅደስ መግባት በትንቢት መነፅር ተመልክቶ የተናገረው ቃል ነው፡፡ የሱንም ቃል የዜማው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ይዞ "ስምኢ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምኢ ዕዝነኪ ርስዒ ሕዝበኪ ቤተ አቡኪ እስመ ፈተወ ንጉሥ ሥነኪ ቀደሰ ማኅደሮ ልዑል ወይቤ ዝየ አኀድር እስመ ኀረይክዋ፡፡" (ልጄ ሆይ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብለሽ አድምጪ፤ ሕዝብሽንና የአባትሽን ቤት እርሺ ንጉሥ ውበትሽን ወዷልና፡፡ ልዑል ማደሪያውን ለየ በዚች አድራለሁ መርጫታለሁና::) ሲል አዜመ፡፡ ✔️ ቅዱስ ዳዊት ልጄ ብሎ የጠራት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሲሆን ዳዊት ልጄ ያለበት ምክንያት "ትወጽእ በትር እምሥርወ እሴይ" በትር (ከእሴይ ሥር ከዳዊት ዘር ትወጣለች) እንደተባለው በሥጋ ከዳዊት ዘር ለተገኘች ለእርሷ ስለሆነ አባቷ መሆኑን ሲናገር ነው፡፡ ✔️ ሕዝብሽንና የአባትን ቤት እርሺ ያለበት ምስጢር ስለሁለት ነገር ነው በመጀመሪያ ኑሮሽ በቤተ መቅደስ ከመላእክት ጋር ነውና የአባትሽ የኢያቄም ቤት አያጓጓሽ የሕዝብሽን የዕብራውያን ባህልና ልማድ እርሺ አንቺ ለዚህ ዓለም ግብር በዘልማድ የተፈጠርሽ አይደለምና፤ የዚህ ዓለምን ነገር ተዪው ትዝ አይበልሽ ሲል ነው፤ ዳግመኛ የአባትሽን የአዳምን ቤት (አዳማዊ ባሕርይሽን) እርሺ ያደፈው የጎደፈው ያረጀው ያፈጀው የአዳም ባሕርይ ወደ አንቺ አይሻገርም ለአንቺ አይመጥንሽም ሕዝብሽን እርሺ የሔዋን ልጆችን የሚያስቡትን ምድራዊ ሀሳብ እርሺ ሲል ነው፡፡ ✔️ለምን የተባለ እንደሆነ የነገሥታት ንጉሥ እግዚአብሔር ውበትሽን ንጽሕናሽንና ቅድስናሽን ወዷልና፤ አንድም አንቺን ለእናትነት መርጧልና አንድም ማኅፀንሽን ዓለም አድርጎ ሊመሰገንበት አስቧልና በማለት እመቤታችን ከዚህ ዓለም ግብርም ሆነ ክብር ተለይታ እንድትኖር የታዘዘችበትን ምክንያት ተናግሯል፡፡ ✔️ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ይህን የቅዱስ ዳዊት ቃል ሰምታ ጆሮዋን አዘንብላ የእግዚአብሔርን ቸርነት መልአኩን ተመልክታ ከእጁም ሰማያዊ መብል ተመግባ ሰማያዊም መጠጥ ጠጥታ ገና በህፃንነቷ እናትና አባቷን ትታ ወደ ቤተመቅደስ ገብታለች፡፡ ይህን መብል የተቀበለ መዳፉአን ሊቃውንተ ቤተመቅደስ ሲያመሰግኑ " ሰላም ለእራኅኪ ተመጣዌ ኅብስት ወማይ፡፡ ሶበ ያመጽኡ ለኪ መላእክተ ሰማይ፡፡ እንዘ ሀሎኪ ማርያም በመቅደሰ ኦሪት አባይ፡፡ ይትወከፍ ሊተ ኪዳንኪ ከመ መሥዋዕተ ሠርክ ኅሩይ፡፡ ለእመ ህፍነ ማይ አስተይኩ ለጽሙዕ ነዳይ" ( ታላቅ በሆነች በኦሪት መቅደስ ሳለሽ የሰማይ መላእክት ምግብሽን ባመጡልሽ ጊዜ ሰማያዊ ኅብስት ሰማያዊ መጠጥን ለተቀበለው መዳፍሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ለተጠማ ችግረኛ እፍኝ ውኃ ባጠጣ ኪዳንሽ እንደተመረጠ የማታ መሥዋዕት ይቀበልልኝ፡፡) ብለዋል፡፡ ✔️ ይህ እድሜ (3 ዓመት) ለአንድ ህፃን ልጅ የቤተሰቦቹ እንክብካቤ የሚያስፈልገው መሆኑ ግልፅ ነው በዚህ እድሜ ከቤተሰብ መለየት ለሁለቱም ሐዘን ነው፡፡ እመቤታችን ግን በዚህ እድሜዋ ከቤተሰቦችዋ ተለይታ ቤተመቅደስ በመላእክት እንክብካቤ ትኖር ነበር፡፡ አባ ፅጌ ድንግል በህፃንነቷ ከእናትና አባቷ መለየቷ ቢያሳዝነውም በመልአኩ እጅ በሆነው ነገር ደግሞ እንደሚደሰት " የኃዝነኒ ማርያም ዘረከበኪ ድክትመና አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ እንዘ ትጠብዊ ሐሊበ ሐና። ወያስተፌሥሐኒ ካዕበ ትእምርተ ልኅቀትኪ በቅድስና ምስለ አብያጺሁ ከመ አብ እንዘ ይሴስየኪ መና። ፋኑኤል ጽጌ ነድ ዘይከይድ ደመና፡፡" (ማርያም ሆይ የሐናን ጡት እየጠባሽ ሳለሽ ወደ ቤተ መቅደስ በገባሽ ጊዜ ያገኘሽ ደሀ አደግነት፤ ብቸኝነት ያሳዝናል፤ ዳግመኛም በደመና የሚሄድ ተፈጥሮው ከእሳት የሆነ ፋኑኤል ከጓደኞቹ ጋር መና የመገበሽ በንጽሕና በቅድስና ጸንተሸ የማደግሽ ተአምር ያስደስተኛል፡፡) ሲል ተናግሮአል፡፡ ✔️ መቅደስ የተሰኘች አመቤታችን በዚህ እድሜዋ በቤተ መቅደስ እንዴትና እንደምን ትኖር ነበር? ምንስ ትመገብ ነበር ? የሚል ካለ ቅዱስ ያሬድ " አንቲ ውእቱ ንጽሕት እምንጽሕት ዘነበርኪ ውስተ ቤተ መቅደስ ከመ ታቦት ወመላእክት ያመጽኡ ወትረ ሲሳየኪ ስቴኪኒ ስቴ ሕይወት ውእቱ ወመብልእኪኒ ኅብስት ሰማያዊ፡፡" (እንደ ታቦት በቤተ መቅደስ የኖርሽ መላእክት ዘወትር ምግብሽን የሚያመጡልሽ መጠጥሽም የሕይወት መጠጥ ምግብሽም የሕይወት ምግብ የሆነልሽ፤ አንቺ ከንጹሐን ሁሉ ንጽሕት ነሽ፡፡) ሲል ምስክርነቱን ይሰጣል፡፡ በተጨማሪም "ንጽሕተ ንጹሐን ከዊና ከመ ታቦር ዘዶር ዘሲና ውስተ ቤተ መቅደስ ነበረት በቅድስና ሲሳያ ኅብስተ መና ወስቴሃኒ ስቴ ጽሙና፡፡ በሲና እዳለች እንደ ታቦት ዘዶር ከንጹሐን በላይ ንጽሕት ሆና በቤተ መቅደስ ኖረች መግቧ ኅብስተ መና መጠጧ የጽሙና መጠጥ ነው፡፡) ሲል ሊቁ ተናግሮአል፡፡ ይህም የሆነው ታኅሳስ 3 ቀን ነው፡፡ ✔️ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት በረከት አይለየን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ ✍️ ሚኪያስ ግዛቸው

አቡነ ዜና ማርቆስ ** ቅዱስ አባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ ሀገራቸው ዞረሬ /ጽላልሽ/ ነው። አባታቸው ካህን ዮሃንስ የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የአቡነ ጸጋዘአብ ወንድም ነው። እናታቸው ዲቦራ (ማርያም ዘመዳ) ትባላለች። የአቡነ ቀዎስጦስ እህት ናት። ህዳር ፳፬ /24/ ተወልዷል። አርባ ቀን ሲሞላው ሊያስጠምቋቸው ቤተ ክርስቲያን ወሰዷቸው። ጸሎተ ጥምቀቱ ደርሶ ከውሃ ውስጥ ሲከቷቸው ቆመው እሰግድ ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብለው 3 ጊዜ ሰግዶአል። ውሃው ፈላ አጥማቂው ቄስ የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የአቡነ ጸጋዘአብ ወንድም ካህኑ እንድርያስ ነበር። እድሜው 72 ዓመት ስለነበር በሕፃኑ ድርጊት ፈርቶ ወደ ቤተ መቅደስ ሮጠ። ቅዱስ ሩፋኤል ከፍርሃቱ አጽናንቶት ከማየ ጸሎቱ ራሱን እንዲቀባ ነግሮት በራ የነበረ ራሱ ጸጉር በቅሎለታል። **አቡነ ዜና ማርቆስ 5 ዓመት ሲሞላቸው ወላጆቻቸው ለመምህር ሰጧቸው። በ 3 ዓመት ብሉይንና ሐዲስ አጥንተው በ8 ዓመታቸው ከቅዱስ ቄርሎስ ድቁና ተቀብለው ሲመጡ ሽፍቶች የእጃቸውን በትር ነጠቁaአቸው፡፡ እሳቸውም ወደ ጌታ ቢያመለክቱ በትራቸው እባብ ሆና ነድፋ ገድላቸዋለች። 30 ዓመት ሲሆናቸው ማርያም ክብራ ለምትባል ደግ ሴት አጋቧቸው። ልማደ መርዓዊ ወመርዓት (ሙሽራውና ሙሽራይቱ) ያድርሱ ብለው መጋረጃ ሲጥሉባቸው በሌሊት ወጥተው ሄዱ። መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ሀገረ ምሑር አድርሷቸውዋል። በዛም የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በመጥራታቸውና ከንጉሱ (ሀገረ ገዢው) አብላኝ በማለታቸው የኔ አምላክ ማኮስ ነው ኢየሱስ የምትለው ማን ነው ቢላቸው አምላካችን ነው ቢሏቸው ወስዶ ቤተ ጣዖት ቢያሳያቸው በእግር ረግጠው አሰጠሙት። መስፍኑ ተቆጥቶ አሰራቸው። መልአኩም ከእስራታቸው ፈቷቸዋል። እንዲያበላቸው ዳግም ሀገረ ገዢውን ቢጠይቁት ተናዶ በጦር ሊወጋቸው ሲል ምድር አፏን ከፍታ ባሕር ሆና አሰጠመችው። እንዲህ እያሉ ብዙ ስለ ጌታ መስክረዋል። ኋላም ወደ ምድረ ጉራጌ ወርደው ብዙውን አስተምረው ወደ እምነት መልሷል። ብዙዎችም አሳምነው አጥምቋቸዋል። በጸሎታቸውም ብዙ በሽተኞችን ፈውሶ የትሩፋት ሥራን ሠርተዋል። ሃላም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ምንኩስና ሰቷቸው ወደ ደብረ አስቦ (በደብረ ሊባኖስ) ተክልዬ ለ29 ዓመታት የጸለዩበት ቦታ ሄዱ። **ከዚህ በኋላ አቡነ ዜና ማርቆስ ደብረ ብስራትን ገድመው እያስተማሩ ኖረው ፪፻ አናብስት በ፪፻ አናብርት ታጅበው በደመና ተጭነው ብዙ ቦታ በመሄድ አስተምረው አሳምነዋል። ከእረፍታቸው በፊትም ልጆቻቸውን በሙሉ ከየሀገሩ ጠርተው ቅዳሴ ቀድሰው ሲያቆርቡ ከብዛታቸው የተነሳ ፀሐይ ልትገባ ስለሆነ ወደ ጌታ አመልክተው አቀብለው እስኪፈጽሙ ድረስ ፀሐይ ባለችበት እንድትቆም አድርገዋል። ከዚህ የበዙ ተዓምራትን ሲያደርጉ ኖረው በተስፋቸው ያመነ በኪዳናቸው የተማጸነ ዋጋውን እንደማያጣ ጌታ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸው በተወለዱ በ 140 ዘመናቸው ታህሳስ 3 ቀን ዐርፈዋል። ወስብሐት ለእግዚአብሔር።

ዛሬ ምሽት 2፡00 EOTC Tv ላይ ይከታተሉን
ዛሬ ምሽት 2፡00 EOTC Tv ላይ ይከታተሉን