uk
Feedback
Grace & Truth Ministry

Grace & Truth Ministry

Відкрити в Telegram

እንኳን ወደዚህ ቻናል በሰላም መጡ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ በእውነት ቃልና በፀጋው መንፈስ ይታነፁ

Показати більше
1 029
Підписники
Немає даних24 години
-77 днів
-2030 днів
Архів дописів
#ተፈቃሪዋ_ጎሜር ወጣቱን ነብይ እንዴት አመንዝራይቱ ጎሜር አፍቅሮ እንዲኖር: እግዚአብሔር አዘዘ?.... በዛ ውስጥ እውነተኛው የእግዚአብሔር ፍቅር ለእኛ ምን ያስረዳናል? ሕይወት ለዋጭ ቃል ሳያደምጡ ሼር አያድርጉ🙏 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351

ትምሕርተ-ፀሎት የቀጠለ ያለ    #መልካም_እና_ደስ_የሚያሰኝ_ጸሎት ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ በጻፈለት መልዕክት ውስጥ  እንግዲህ በቤተክርስቲያን አስቀድሞ ከሁሉ በፊት ለነገስታት ለባለ ስልጣናትና ለሰዎች ሁሉ ልመናና ጸሎት ምልጃና ምስጋና እንዲደረግ አሳስባለሁ ይለዋልለነገስታት እና ለባለ ስልጣናት ጸሎትና ምልጃ መደረግ ያስፈለገበት ምክንያት  “እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ነው ይለናል።(1ኛጢሞ2:4) #በአዲሱ_መደበኛ_ትርጉም_በእውነተኛ መንፈሳዊ ህይወትና በቅድስና ሁሉ በሰላምና በጸጥታ እንድንኖር ነው ይለናልስለሰዎች ሁሉ ምልጃና ጸሎት በቤተክርስቲያን መደረግ ያስፈለገበትን ምክንያት ደግሞ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ እና እውነትን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ ነውአንዳንድ ጊዜ እንደ አገልጋይ ክርስቲያኖች የተወሳሰበን ነገር ይዘው እንድትጸልዩላቸው ወደ እናንተ ሲመጡ ተቀብሎ ማስተናገዱ በጣም አሰልቺ ይሆናልብዙውን ጊዜ እንደዚህ አይነቶቹ ክርስቲያኖች በቤተክርስቲያን ውስጥ (#የቅዱሳን_ሕብረት) ረዘም ላለ ሰአት ወደሚደረገው የጸሎት ፕሮግራም መጥተው ስለራሳቸው እንዲጸልዩና መጸለይን እንዲለማመዱ ሲጋበዙ በፍጹም መገኘትን አይፈልጉምስለራሳቸው ከመጸለይ  በሚመጣባቸው ችግር ውስጥ መውደቅን  ይመርጣሉበምታናግሯቸው  ጊዜ ደግሞ የምትነግሯቸውን ነገር ከማድመጥ ይልቅ እንደ ህጻን የራሳቸውን ጩኸት ብቻ ደጋግመው መጮህ ነው የሚፈልጉትጸ ል ይ ል ኝ... ጸ ል ይ ል ኝ : ለራሳቸው ከመጸለይ ይልቅ ለምን እንደዚህ አይነቱን መንገድ እንደሚመርጡ አይገባኝምእንደዚህ አይነት ክርስቲያኖች : አይደለም ስለ ባለስልጣናት እና ስለ ሰዎች ሁሉ ምልጃና ጸሎት ሊያደርጉ ይቅርና እነርሱ በሌሎች ሰዎች ጀርባ ላይ ታዝለው ወይንም ሌሎች ሰለ እነርሱ እየጸለዩላቸው መኖርን ነው የሚፈልጉትነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል ሌሎች እንዲጸልዩልን ብቻ ሳይሆን በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ራሳችን መጸለይ እንዳለብን ከራሳችንም አልፈን ለነገስታት ለባለስልጣናትና ለሰዎች ሁሉ እንድንጸልይና ወደ እንደዚህ አይነቱ የጸሎት ሕይወት እንድንመጣ ያስተምረናል! በእውነተኛ መንፈሳዊ ህይወት በቅድስና ሁሉ በሰላምና በጸጥታ ለመኖር እንዲሁም ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ እና እውነትን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ ይህ አይነቱ  ምልጃና ጸሎት በቤተክርስቲያን መደረጉ: እጅግ አስፈላጊና ከሁሉ በፊት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ነው።     በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ   ነው 1ኛ ጢሞ 2፥4 ተብሏል። ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ⛪️ #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን ❤   

በውስጣችሁ መለኮታዊ ፕሮግራም እንዳለባችሁ የምታውቁ ቅዱሳን ይኼን ያዳምጡ #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ 👉 @biruk351

ትምሕርተ-ፀሎት የቀጠለ ያለ #የምናምነውን_መጸለይ “አምናችሁም በጸሎት የምትለምኑትን(KJV #የምትጠይቁትን)ሁሉ ትቀበላላችሁ አላቸው።”(ማቴ 21፥22 ) #እምነት_የሁሉ_ነገር_መሰረት_ነው። እግዚአብ
ትምሕርተ-ፀሎት የቀጠለ ያለ #የምናምነውን_መጸለይ “አምናችሁም በጸሎት የምትለምኑትን(KJV #የምትጠይቁትን)ሁሉ ትቀበላላችሁ አላቸው።”(ማቴ 21፥22 ) #እምነት_የሁሉ_ነገር_መሰረት_ነው። እግዚአብሔር አስቀድሞ በፀጋ ሁሉን አዘጋጀ: ያንን ማጣጣም የምንችልበት መንገድ ፀሎት ሲሆን ፀሎት ያለ እምነት ኪሳራ ነው! የጸለይነውን ጸሎት ሁሉ እንድንቀበል የሚያደርገን እምነት ሲሆን የምንጸልየውም ጸሎት በምናምነው ነገር ላይ የተመሰረተ ነውይህም ከመጸለይ በፊት #ማመን_ይቀድማል_ማለት_ነው። 👉አምነን እንጸልያለን እንጂ #ለማመን_አንጸልይም። የዕብራውያን መልዕክት ምዕራፍ  አስራ አንድ(11) ስለ ውጤታማ  ጸሎት ሁለት(2) ዋና ዋና  ነገሮችን ያስቀምጥልናል:: #እግዚአብሄር_እንዳለ_እና_ለሚፈልጉት/ወደ እርሱ ለሚጸልዩ/ዋጋን ወይንም የጸሎታቸውን መልስ እንደሚሰጥ ማመን ያስፈልጋል ይለናልያመንነውን ነገር ወደ ጸሎት ካላመጣነው በስተቀር ማመናችን ብቻውን  ነገሩን የእኛ እንዲሆን አያደርገውምስለዚህ እናምናለን የምናምነውን እንጸልየዋለን አምነን የምንጸልየውን ነገር ከእግዚአብሔር እንቀበላለንይኼ ማለት እምነት የእግዚአብሔርን እጅ መጠምዘዣ ኃይል ሳይሆን: እግዚአብሔር በመልካምነቱ ያደረገውን የምንረዳበትና ልባችንን በእርሱ በማሳረፍ : ለእኛ የሆነውን የምንጠቀምበት መንገድ ነው! ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351   #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን🙏 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ⛪️

ኢየሱስ መስቀል ላይ የሆነልን የቤዛነት ስራ የከበረ ነው...ከዚያ ባለፈ በመስቀል ላይ በመሆን እኛ  ለሕይወታችን የምንማርበትን ብዙ እውነታዎችን አድርጓል..ከእነዚህ መካከል ..#ያድምጡ🙏 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን ⛪️ 👉 @biruk351 👈

ትምሕርተ-ፀሎት የቀጠለ #ጻድቅ_ወደ_እግዚአብሔር_ይጸልያል!! በምድር ላይ የማይፀልይ ሃይማኖት የለም ሁሉም የሃይማኖት ቤቶች ይጸልያሉ: ይህንን ስንል ግን ሁሉም የሚጸልዩት ወደ እግዚአብሔር ነው ማለ
ትምሕርተ-ፀሎት የቀጠለ                  #ጻድቅ_ወደ_እግዚአብሔር_ይጸልያል!! በምድር ላይ የማይፀልይ ሃይማኖት የለም ሁሉም የሃይማኖት ቤቶች ይጸልያሉ: ይህንን ስንል ግን ሁሉም የሚጸልዩት ወደ እግዚአብሔር ነው ማለታችን አይደለም! #የእግዚአብሔር_ቃል"ጻድቅ ወደ እግዚአብሔር ይጸልያል"  ይለናል። የእግዚአብሔርም አይኖች ዘወትር ወደ ጻድቃን ወይንም ወደ እኛ ይመለከታሉ: ስለዚህ ሁል ጊዜ በሚወደን በእግዚአብሔር እይታ ውስጥ ነንበእግዚአብሔር እይታ ውስጥ መሆን በራሱ በእኛ ላይ ያለውን የሁልጊዜ መለኮታዊ ጥበቃና ፍጹም የሆነ ፍቅር የሚያሳይ ነውሰው አይኖቹን በሚወደው ነገር ላይ በትኩረት እንደሚያሳርፍ ሁሉ እግዚአብሔር እኛን ሁልጊዜ በፍቅር አይን ይመለከተናል: እኛ የእርሱ ትኩረቶች ነን! #ይህ_ብቻ_አይደለም_ጆሮዎቹ ለጸሎቶቻችን የተከፈቱ ናቸው። “የጌታ ዓይኖች ወደ ጻድቃን ናቸውናጆሮዎቹም ለጸሎታቸው ተከፍተዋል” (1ኛ ጴጥ 3፥12) እኛ ጻድቃን የምንጸልየው በተከፈተ ጆሮ ሲሆን ፡ የእግዚአብሔር ጆሮዎቹም የጻድቃንን ጸሎት ለማድመጥ ወይንም የጻድቃንን ጸሎት ሰምቶ ለመመለስ ተከፍተዋል!#ሀሌሉያ 🔥🔥🔥 ስለዚህ ጻድቅ ወደ እግዚአብሔር ይጸልያል "የጻድቅ ሰው ጸሎት ደግሞ በስራዋ እጅግ ሃይልን ታደርጋለች" በሌላ ትርጉም፡ "የጻድቅ ሰው ጸሎት ውጤት የሚያስገኝ ታላቅ ኃይል አለው" ይለናል። #ወደ_ቻናላችን_መቀላቀልና_ስለ #ፀሎት_በይበልጥ_ለመረዳትና_ #ለመፀለይ_ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ብቻ_ይንኩ👉 👉@biruk351 👈👈 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ⛪️ #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን❤

ትምሕርተ-ፀሎት የቀጠለ ያለ ...የእግዚአብሔር ሐሳብ ለሰው ልጆች ሁሉ በጎና መልካም ነው: ክፉም የለበትም። በጸሎታችን ጊዜ ወደዚህ በጎና ቅን ሐሳቡ ይስበናል፡፡ እግዚአብሔር ያው ነው ሊቀያየር አይ
ትምሕርተ-ፀሎት የቀጠለ ያለ ...የእግዚአብሔር ሐሳብ ለሰው ልጆች ሁሉ በጎና መልካም ነው: ክፉም የለበትም። በጸሎታችን ጊዜ ወደዚህ በጎና ቅን ሐሳቡ ይስበናል፡፡ እግዚአብሔር ያው ነው ሊቀያየር አይችልም። በእግዚአብሔር ላይ የተቀየረበት ሰው ነው፣ የሚቀየርበትም ተለዋዋጭ ስሜትና ድካም ያለበት ሰው ነው ፤ ስለዚህ የማይለወጠው እግዚአብሔር እኛ በጸሎት ወደ ፊቱ ስንቀርብ፡ ከሱ ከዞርንበት ከየትኛውም አድካሚ ነገር በምህረቱ ወደ ራሱ በማዞር ያቀርበናል፡፡ በዚህም ምክንያት በጸሎት ውስጥ ተሃድሶ፣ መጽናናት፣ ለተፈጠርንበት ኑሮና ዓላማ የሚትረፈረፍ ፀጋ ማግኘት እንችላለን፡፡ ጸልየን ቀና ስንል እግዚአብሔር ለእኛ ወዳዘጋጀው መልካምና በጎ ነገር እንቀርባለን፡ በምህረቱም እንጨብጠዋለን፡፡ ወደ እግዚአብሔር መጸለይ ለሱ የመማረክ፣ እሱን የመውደድና ለፈቃዱ ለመገዛት የመሰጠት ምልክት ነው። ➡️#ግን_ለምን_እንጸልያለን? 1. የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ስለሆነ (ማቴ7፡7-8‚ ሉቃ18፡1-7‚ 1ተሰ5፡17) 2. በየዕለት ባለን ግንኙነት ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ (ያዕ4፡8) 3. የእግዚአብሔር ፈቃድ ይፈጸም ዘንድ (ማቴ6፡10) 4. ከሃጢያትና ከፈተና ለማምለጥ (ማቴ26፡41‚ ሉቃ22፡34-40) 5. ለራሳችንና ለሌሎች ሰዎች መፍትሔ ለመሆን (ኤፌ 6: 19-20) 6. ስለ እግዚአብሔር የሰማናው : እግዚአብሔራዊ እውቀት በማስተዋል እንድንረዳውና የውስጥ አይናችን እንዲበራ (ኤፌ1:17-21፣ ኤፌ 3:14-20) ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ⛪️ #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን🙏

#ትምሐርተ_ፀሎት #በክርስትና_ህይወት_መሰረታዊ_ነገር_ የፀሎት ህይወት ነዉ!! ሰለፀሎት  ምንነት በጥልቀት ማየት ጀምረናል ይኼንንም አሁንም እንቀጥላለን ። #የጸሎት_አይነቶች 1. #የንስሃ_ጸሎት፡-  👉 ይህ ጸሎት ልጆች ከአባታቸው ጋር ሕብረታቸውን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚያድሱበት ነው ። ይህ ፀሎት 👉እግዚአብሔርን በበደልንበት ወይም ግልፅ ፈቃዱን በተላለፍንበት ወቅት: ራሳችንን በፀጋው ዙፋን ፊት በማዋረድ : የእግዚአብሔርን ምህረት የምንቀበልበትና ህብረታችንን እንደገና የምናድስበት የጸሎት አይነት ነዉ (ምሳ28፡13‚ 1ዩሐ1፡7-9)፡፡ 👉 የንስሃ ጸሎት ብቻ ሳይሆን ካለፈዉ የተሳሳተ ድርጊታችን በመመለስ በቀጣዩ ምልልሳችን የሚገለጽ ነዉ (2ቆሮ7፡8-11) 2. 📌#የምስጋናና_የዉዳሴ_ጸሎት፡-  👉 የምስጋና ጸሎት እግዚአብሔር ለእኛም ሆነ ለሌሎች ስላደረግነዉ ነገር ሁሉ በማሰብ የምናቀርበዉ መስዋዕት ሲሆን  👉 ዉዳሴ ደግሞ እግዚአብሔርን ስለ አምላክነቱ፣ ክብሩ፣ ታላቅነቱ በአጠቃላይ ስለ ማንነቱ የምናከብርበትና የምናመልክበት የጸሎት አይነት ነዉ፡፡ 👉 ምስጋና፡- መዝ(103)፡1-5‚ ሉቃ17፡11-19‚ ኤፌ5፡20 👉 ዉዳሴ፡- መዝ(93)፡1-3‚ ነህ9፡5-6‚ ራዕ7፡10-17 3. 📌#ልመናና_ጸሎት፡-  👉 የልመና ጸሎት ለግል ህይወትም ሆነ ኑሮአችን የሚያስፈልገንን ነገር ለመቀበል በእግዚአብሔር ፊት የምናቀርበዉ ጸሎት ነዉ መዝ(28)፡6‚ 1ሳሙ1፡26-28 4.📌 #የምልጃ_ጸሎት፡-  👉 ይህ ጸሎት ስለ ራሳችን የምንጸልየዉ ሳይሆን ስለ ሌሎች በእግዚአብሔር ፊት የምናቀርበዉ ልመና ነዉ (ዘኁ14፡17-19‚ ኤፌ6፡18-20‚ 1ጢሞ2፡1-4‚ ያዕ5፡16) 5📌#የውጊያ_ፀሎት የአማኞችና የእግዚአብሔር ጠላት የሆነዉ ዲያቢሎስ ሁልጊዜ አማኞችንና እግዚአብሔርን መንግስት እንደሚዋጋ ቃሉ ይናገራል፡፡ ስለዚህ ባላጋራችንን ከምንዋጋበት መንገዶች አንዱ ፀሎት ሆኖ በኤፌሶን ስድስት ቀርቦልናል። "በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩበዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ" (ኤፌ 6:18) ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ⛪️ #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን❤

ትምህርተ-ፀሎት የቀጠለ..... ፀሎት ፦ በመንፈሳዊ ሕይወታችን ውስጥ፡ ውጤታማነትን የማምጫ መንገድ እንዲሁም ነፍሳችንን የምንገዛበት ስፍራ ነው።    አንድ ክርስቲያን መንገዱን እንደሚፈልገው ለመምራትና እግዚአብሔር ያዘጋጀለትን ሕይወት ለመኖር: መከተል ወይም መተግበር ያለበት ክርስቲያናዊ መርሆች አሉ። ከእነዚህ መካከል የፀሎት ሕይወት አንዱ መርህ ነውና በፀሎት ውስጥ ያሉ ግላዊ ትሩፋቶችን በተወሰነ መልኩ እንይ። ❶ #የመንፈስ_ቅዱስ_ሀይል   ፦ መንፈስ ቅዱስ በሃይል የሚገለጥ አምላክ እንጂ ሀይል አይደለም። ቢሆንም በምንፀልይ ሰዓት በዚህ ኃይል የመነቃቃትና ይኼንን ኃይል መጠቀም የምንችልበትን ጥበብ እናገኘዋለን ። 👉 ሐዋ 1:8   ሐዋ 10:38 ❷ #የእውቀት_ሀይል ፦ፀሎትን ወደ መሰማትና ወደ መልስ ከሚገፉት ሀይሎች መካከል እውቀት አንዱ ነውምክንያቱም እግዚአብሔር የሚሰማውም ሆነ የሚመልሰው ለለቅሶና ለእንባ ሳይሆን እንደ ቃሉ ለሆነ ፀሎት ነው። #እግዚአብሔር_ለቃሉ_ታማኝ_ነው!!     2ቆሮ 4:6 ❸ #የእምነት_ሀይል እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውየፃድቅ እስትንፋስ እንዲሁም መንፈሳዊ አለምን የምንገናኝበት መስመር እምነት ነው። በምንፀልይ ሰዓት አምስቱ የስሜት ሕዋሳትን የተቃውሞ ቀጠና አልፈን ነውና በእምነት መጠንከርን እንለምዳለን።    ዕብ 11:6 ➍ #የንግግር_ሀይል ፦ ንግግር የቀጣዩን ሕይወታችን ምዕራፍ የሚቀይርና ወደፊታችንን መወሰን የሚችል አቅም ነው   📌መልካምን የሚናገር መልካም ዘርን ይዘራል ፍሬውም መልካም ነው።   በተቃራኒውም እንደዛው ይሆናል። ምሳሌ 16 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²³ የጠቢብ ልብ አፉን ያስተምራል፥ ለከንፈሩም ትምህርትን ይጨምራል። ²⁴ ያማረ ቃል የማር ወለላ ነው፤ ለነፍስ ጣፋጭ ለአጥንትም ጤና ነው።   ➎ #የፀሎት_ሀይል ፦ #በፀሎት_ውስጥ   📌የዓላማ 📌የህልምና 📌የራዕይ መገለጥና መነሳሳት ይመጣሉ።    #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ⛪️ ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን❤

ትምሕርተ-ፀሎት የቀጠለ "እውነት እላችኋለሁ፥ #በምድር_የምታስሩት_ሁሉ #በሰማይ_የታሰረ_ይሆናል፥ #በምድርም_የምትፈቱት_ሁሉ #በሰማይ_የተፈታ_ይሆናል፤ደግሞ እላችኋለሁ፥ ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚጠይቁት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል። (ማቴ 18 ፥18-19) በኢየሱስ አገላለፅ: በምድር ላይ የሚደረገውን ነገር አስቀድሞ የሚፈታም ሆነ የሚያስር በምድር ያለ የእግዚአብሔር ባለ አደራ እንጂ ሰማይ አይደለም። የሰማይን ፈቃድ በምድር እንዲሆንም ሆነ እንዳይሆን ቀዳሚውን ሚና የሚጫወተው ሰው ነው ። ስለዚህ ሰው በምድር ላይ ያሻውን ማለትም #መልካም ይሁን #ክፉ የማድረግ ስልጣን አለው። ያ ባይሆንና እግዚአብሔር ብቻ በዚህች ምድር ላይ የፈቀደውን የሚያደርግ ቢሆን ኖሮ: ምድርም ልክ እንደሠማይ ሠላምና ፅድቅ የሰፈነባት ትሆን ነበር “#እውነት_እላችኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ #ይህን_ተራራ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል።” (ማር11፥23) እንግዲህ ሰው ስልጣኑን ተጠቅሞ በሁኔታዎች ላይ እንዲያዝ መብት ከተሰጠው ያንን ማድረግ አለበት እንጂ "#ንቀል።" የተባለውን ለራሱ መንቀል ትቶ  እግዝአብሔርን"#ንቀልልኝ" እያለ ሲፀልይ ቢውል ከቃሉ ውጭ የሆነ ፀሎት ስለሆነ ከእግዝአብሔር ዘንድ መልስ አያገኝም። ስለዚህ ሰው በፀሎት በሰማይ ያለውን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ወደ ምድር  የማምጣት መብት ከተሰጠው ሰማይን ማዘዝ ይኖርበታል እንጂ ቁጭ ብሎ "እግዚአብሔር ያውቃል።" በሚል ሰማይ ተዐምር እንዲያወርድለት መጠበቅ አይገባውም። አንዳንድ ሰዎች በዚህ ፁህፌ ይናደዳሉ :በእነርሱ አስተሳሰብ የእግዚአብሔርን ክብር ዝቅ አርጌ የሰውን ከፍ ያደረኩ እየመሰላቸው ነው። እንደዛ አይደለም ! እግዚአብሔር ነው ይኼን ክብር ለሰው የሰጠው ። “የእስራኤል ቅዱስ ሠሪውም እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ስለሚመጣው ነገር ጠይቁኝ፥ ስለ ልጆቼና ስለ እጄ ሥራም እዘዙኝ።”   — ኢሳይያስ 45፥11 “- - -#ሳትለምኑት_አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን ያውቃልና። እንግዲህ እናንተስ እንዲህ ጸልዩ፦ በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፥ ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን- - -" — ማቴዎስ 6፥8-10 እግዝአብሔር ለሰው የሚያስፈልገውን ካወቀ ታዲያ መፀለዩ ለምን አስፈለገ? እግዝአብሔር ሁሉን አዋቂ ቢሆንም በምድር ላይ #መልካምን ነገር ለማድረግ " #ይሁን ።"የሚል የሰው ፈቃድ ይሻል። እግዝአብሔር ሁሉን ስለሚያውቅና ሁሉን ማድረግ ስለሚችል ብቻ የሰውን ፈቃድ አልፎ በዚች ምድር ላይ አንዳች አያደርግም። ምክንያቱም እግዚአብሔር በዘፍጥረት ላይ ምድርን "አብረን እንግዛ።"ሳይሆን "ግዛ ።" ብሎ ለሰው ልጅ  የሰጠው። ምንም እንኳ የሰው ልጅ ቢያምፅና እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መመላለስ ቢሳነውም እግዚአብሔር ታማኝነቱን አጉድሎ ለሰው ልጅ የሰጠውን ስልጣን  አልሻረም። ስለዚህ ሰው በዚች ምድር ላይ ከእግዚአብሔር ጋር አብሮ መልካምን ማድረግ እንደሚችል ሁሉ ከክፉ ጋርም አብሮ ክፋትን መፈፀም ይችላል። በመጨረሻም መጨመር የምፈልገው   መግቢያ ላይ እንደጠቀስኩ ለአንድ አማኝ ፀሎትም ሆነ ፆም #ምርጫ_ሳይሆን_መስፈርት_ነው። ለዚህ ነው ጌታ ኢየሱስ "የምትፀልዩ ከሆነ።" ሳይሆን "#ስትፀልዩ።" ያለው። “#ስትጸልዩም እንደ ግብዞች አትሁኑ።”   — ማቴዎስ 6፥5 “#ስትጸልዩ በከንቱ አትድገሙ።”   — ማቴዎስ 6፥7 “#ስትጸልዩ እንዲህ በሉ።”   — ሉቃስ 11፥2 “#ስትጦሙም፥ እንደ ግብዞች አትጠውልጉ፤ ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠፋሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።”   — ማቴዎስ 6፥16 እንደ ቃሉ ፀልየን በሠማይ ያለውን የአባታችንን በጎ ፈቃድ በምድር ላይ በመግለጥ በፅድቅ ተፅኖ የምናሳድርበት ጊዜ ይሁንልን🙏 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351 #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን ❤

ትምህርተ-ፀሎት የቀጠለ #ፀሎት_ለአማኝ_ምርጫ_ሳይሆን_መስፈርት_ነው። ማለትም ፀሎት ለአንድ አማኝ የየዕለት ተግባሩ እንጂ ሲፈልግ የሚያደርገው ሳይፈልግ ሲቀር ደግሞ የሚተወው ጉዳይ አይደለም፣ ወይም
ትምህርተ-ፀሎት የቀጠለ #ፀሎት_ለአማኝ_ምርጫ_ሳይሆን_መስፈርት_ነው። ማለትም  ፀሎት ለአንድ አማኝ የየዕለት ተግባሩ እንጂ ሲፈልግ የሚያደርገው ሳይፈልግ ሲቀር ደግሞ የሚተወው ጉዳይ አይደለምወይም ፀሎት ችግር  ሲያጋጥም፣ ሲያጋጥም ብቻ መፍትሔ  ለማግኛ ተብሎ የሚታወጅ ኃይማኖታዊ ሥርዐትም አይደለምፀሎት በሰማይ ያለውን የእግዝአብሔርን መልካም ፈቃድ የሰው ልጅ በምድር ላይ እንዲሆን የሚጠይቅበት መንገድ ነውስለሆነም የሰው ልጅ ይህቺን በኃላፊነት የተቀበላትን ምድር እንደ እግዚአብሔር አሳብና ፈቃድ ለማስተዳደር: ምድርን ከሰጠው ከእግዚአብሔር  ጋር: ዕለት ዕለት መነጋገርና ምሪትን መቀበል ይኖርበታል። (ቤተክርስቲያን የምድር ባለአደራና የእግዚአብሔር እንደራሴ ነች) እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ፀሎት ምድር ላይ ብቻ ሳይሆን በሰማይም ላይ ተፅዕኖ ማስከተል ይችላልና። “ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም።”   — ያዕቆብ 5፥17 አጥብቆ መፀለይ ማለት፦ ስልጣንን በመጠቀም ነገሮችን ማዘዝ እንጂ ሲደግሙ መዋል አይደለም። ምክንያቱም ኤልያስ "አጥብቆ ፀለየ።" የተባለውን ክፍል ብንመለከት ኤልያስ ያወጣው የስልጣን ቃል ነበር። “በገለዓድ ቴስቢ የነበረው ቴስብያዊው ኤልያስ አክዓብን፦ #በፊቱ_የቆምሁት_የእስራኤል_አምላክ_ሕያው_እግዚአብሔርን! #ከአፌ_ቃል_በቀር_በእነዚህ_ዓመታት_ጠልና_ዝናብ_አይሆንም_አለው" #ይቀጥላል..... #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 ሼር ስለሚያደርጉ እናመሰግናለን🙏

ትምህርተ-ፀሎት የቀጠለ... #አንድ_ሰው_እንዳሉት.. አለመፀለይ በእግዚአብሔር አሁናዊነት የአለማመን ውጤት ነው ይሉ ነበር.. ፀሎት በእግዚአብሔር ዘለአለማዊነት ብቻ ሳይሆን ዛሬውነት አሁንነት ላይ
ትምህርተ-ፀሎት የቀጠለ... #አንድ_ሰው_እንዳሉት.. አለመፀለይ በእግዚአብሔር አሁናዊነት  የአለማመን ውጤት ነው ይሉ ነበር.. ፀሎት በእግዚአብሔር ዘለአለማዊነት ብቻ ሳይሆን ዛሬውነት አሁንነት ላይ ሲጀምር እምነታችን ይፈተናል።  አሁን በዚህ ሰዓት ጣልቃ እንደሚገባ አሁን የሆነ ነገር እንደሚፈጠር መፀለይ እምነት ይጠይቃልእግዚአብሔር መልካም እንደሆነ ታውቃለህ: ረዳትህ አጋዥህ መሆኑንም በአእምሮ ደረጃ ታውቀዋለህ: ይሁን እንጂ አሁን ወገብህን ለቆረጠው የትኛውም ነገር አሁን ጣልቃ ሊገባ ፈቃደኛ እንደሆነ ታምናለህ ወይ? የሚለው ውስጥህን ይንጠዋልስጋህ ሰበባሰቦችን ይዘከዝካል ለምሳሌአንተ አሁን እግዚአብሔር ሰምቶ ሊመልስልህ የተገባህ አይደለህም ምን አይነት ሰው እንደሆንክ ታውቃለህ?ይኼ ነገር አንተ ራስህ ልትወጣው ትችላለህ በትንሽ ትልቁ እግዚአብሔር አትበል .. ይኼ ነገር ለመመለስ ፈቃዱ ባይሆንስ.. እና እንዲህ ያለ ሺህ አንካሳ ሀሳቦች ወደ አእምሮ ይመጣሉ : ያን አልፎ መሄድ የእግዚአብሔር አሁናዊነትን ማመን ነው! #በፀሎትም_የምትተጉ_ሁኑ_! ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351         ♡ ㅤ    ❍ㅤ      ⎙       ⌲       ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ        ❍━━━━━━━━━━❍          @biruk351         @biruk351         @biruk351         🖇ተ🀄️ላ🀄️ሉን    ፀጋና እውነት ቤተክርስቲያን ጅማ

📖 ስላለንበት ሁኔታ ከእግዚአብሔር ከመስማት ይልቅ፡ እግዚአብሔር ስላለበት ክብርና ስላካፈለን ክብር መስማት ታላቅ መልስ ነው! 💌በማንነቱ ያሳረፈን አምላክ ስሙ ቡሩክ ይሁን!! (ትምህርተፀሎት የሚለውን መልዕክት እንቀጥላለን) ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351 🙏         ♡ ㅤ    ❍ㅤ      ⎙       ⌲       ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ        ❍━━━━━━━━━━❍          @biruk351         @biruk351         @biruk351         🖇ተ🀄️ላ🀄️ሉን    ፀጋና እውነት ቤተክርስቲያን ጅማ

#ትምህርት_ፀሎት ባለፉት ረዥም አመታት ስለ ጸሎት ብዙ አይነት ትርጓሜና ትንተና ብዙ አይነት ትምህርትም ተሰጥቶበታል። ሊቃውንትና መምህራን ብዙ አይነት ትንተናም አሳይተውናል። እኔ የእነሱን አይነት ትንተናም ሆነ ትርጓሜ ለመስጠት አቅምም ሆነ ሁኔታው አይፈቅድልኝም። የኔ አላማ በዛሬው አጭር ጽሑፍ ውስጥ: ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ቅዱሳን የፀለየውን ለመፀለይ መጣር ነው። ለመግቢያ ያህል ግን ጆን ማክአርተር እንደሚለው "...ጸሎት ማለት የእኛ ሁሉም ፍላጎቶቻችንና ዓላማዎቻችንን ከፈቃዱከሉዓላዊነቱከጽድቁና ከክብሩ ጋር ለማጣጣም የሚናደርገው መንፈሳዊ ልምምድ ነው።" ብዬ ብጀምር መልካም ይመስለኛል። በእርግጥ ጸሎት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንዲስማማ ለማድረግ የሚደረግ ሙከራ አይደለም። የስጋ መሻቶቻችን እንዲሟሉ ጌታን የምንነዘንዝበት ወይም የምናግባበት ነገርም አይደለም። ጸሎት የእግዚአብሔር ክብር በእኛ እንዲገለጥበፈቃዱ እውቀት ለመሞላትና እርሱን ለማወቅ ሁለንተናችንን በትህትና የምናሰለጥንበት ቦታ ነው። ሐዋሪያው ጳውሎስ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች ከጸለየላቸው ጸሎት አንዱ ይህ  ነው ። ኤፌሶን 1V17-20 (አዲሱ መ.ት) ሐዋሪው በዚህ ጸሎቱ ለሦስት መሰረታዊ ነገሮች ይልይላቸዋል፦ 1- እግዚአብሔርን እንድያውቁ 2- የተጠሩለትን ተስፋ እንድረዱ 3- እግዚአብሔር ለእነርሱ በክርስቶስ በሰራው፡ አሁን በእነርሱ ውስጥ የሚሰራውን ኃይል እንዲጠቀሙ         #ጸሎት አባቴ ሆይ የክብር አባት የሆነውን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ የሆንከውን አንተን:ይበልጥ እናውቅህ ዘንድ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንድታበዛልንበዚህ እውቀት ሁለንታናችንን እንድትሞላበዚህ ውስጥ ባለው ትሩፋት ደግሞ እንድትባርከንባንተ ደስተኞች እንድንሆን እለምንሃለሁአዎ የሰጠን ሕይወት ይኼው ነውና! : ደግሞም አባቴ ሆይ የተጠረንለት ተስፋ እንድንረዳምንነቱን እንድናወቅበቅዱሳኑ ዘንድ ያለው ክቡር የሆነው የርስትህ ባለጠግነት ምን እንደሆነ እናስተውል ዘንድ የልቦና ዐይኖቻችን እንዲበሩክርስቶስን ከሙታን ስታስነሣ የተገለጠውን ያንን ታላቅ ኀይል ደግሞ እንድናወቅ እንድትረዳን እለምንሃለሁበመንፈስህ አብርኆት ውስጥ ያለውን ይህንን ታላቅ እውቀት እንድትሞላን እለምንሃለሁቅዱስ አባት ሆይ አንተን ይበልጥ እንድንፈልግህይበልጥ ለአንተ እንድንሰጥ እጅህን ሳይሆን ራስህን ይበልጥ እንድንራብ ጸጋህን አብዛልንአባቴ ሆይ በዚህ ሁሉ ፍጹም በንተ የረካ ሕይወት እንዲኖረን: ባልተረጋጋ አለም ውስጥ በአንተ የተረጋጋ ሆነን ነፍሳችን ኃጢአትን እንድትፀየፍ እለምንሃለሁ። #አሜን!!! #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 #ሼር_ያድርጉ🙏

(ትምህርተ-ፀሎት የሚለው ርዕሳችን ይቀጥላል :ጊዜውን እንጠቀም ብለን ነው ) "በሆሳዕና" ግርግር መሃል፥ ኢየሱስ አለቀሰ! 😥 ኢየሱስ፦ ስላላወቁት አለቀሰ! የተቀበሉት በትክክል አውቀውት ባለመሆኑ፣ ከሚጠብቃቸው ጥፋት ሊያድናቸው እንደማይችል እያሰበ አለቀሰ! "ሆሳዕና" (እባክህ አሁን አድን) የሚለው የተማፅኖ ጩኸታቸውና "በጌታ ስም የሚመጣ ንጉስ የተባረከ ነው" የሚለው ምስጋናቸው: በትክክለኛ መረዳት ላይ የተመሰረተ አልነበረም። "አሁኑኑ አድነን" እያሉት ነው ግን አላወቁትም ነበር። 😪 "በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው" ብለው ተቀበሉት እንጂ፥ "ጌታ" መሆኑን አልተቀበሉም። 😪 የሚያድናቸው የመሰላቸው ከስጋ ባርነት ነው። የእሱ ማዳን ግን ከሰይጣን፣ ከኃጢአት፣ ከስጋ ምኞት፣ ከዓለም፣ ከሕግ፣ ከእርግማንና ከሞት ባርነት ነበር። ነፃ የሚያወጣቸው የመሰላቸው ከሮማውያን ቅኝ ግዛት ነው። የእሱ ነፃ ማውጣት ግን ከሰይጣን ቅኝ ግዛት ነበር። ይጠብቁ የነበሩት ድንገት በፊታቸው ተለውጦአክሊል ጭኖየተሳፈራትን ውርንጭላ በፈረስ ቀይሮጦሩን አስከትሎከስጋ ጠላቶቻቸው እንደሚቤዣቸው ነውእሱ ግን ሊቤዣቸው የመጣው ከራሳቸው ነበርሊያሳምር የመጣው የምድር ቆይታቸውን ሳይሆን ዘላለማቸውን ነበር። ሊያሳርፋቸው የመጣው የበሽታው ምልክት ከሆነው ከጦርነት ሳይሆን፥ ከበሽታው እና ከምንጩ ከኃጢአት ነበር። ንግስናው በስጋ ሳይሆን በመንፈስ ነበር! ተዋጊ ሳይሆን ተወጊ*፣ፈራጅ ሳይሆን አማላጅ፣ ቀጪ ሳይሆን ተቀጪ፣ እንደአንበሳ ሳይሆን እንደሚታረድ በግ ሊሆን ነበር የመጣው። #ሆኖም_አላወቁትም። የመጣበትን ዓላማ አላወቁም። የመዳኛ ጊዜያቸውን አላወቁም። "ሆ" ብለው እያጀቡት ግን ከኢየሱስ ጋር ተላለፉ! እንዳሰቡት ወደኢየሩሳሌም ሲገባ የሚጠብቀውቤተመንግስት ሳይሆንየጎሎጎታ ተራራና የራስ ቅል ስፍራ ነበር*፤ የወርቅ አክሊል ሳይሆን፥ የእሾህ አክሊል ነበር፤ የወርቅ ዘንግ ሳይሆን፥ የብረት ሚስማር ነበር፤ ምርቃት ሳይሆን ምራቅ ነበር፤ ወይን ሳይሆን ሃሞት ነበር፤ ዙፋን ሳይሆን መስቀል ነበር፤ ክብር ሳይሆን ውርደት ነበር ሆኖም ገድሎ ጀብዱ የሚፈፅምላቸውን እንጂ: ሞቶ የሚያድናቸውን ኢየሱስን አልነበረም ሚጠብቁት። "ሆሳዕና" ብለው፣ ዘንባባ ይዘው፣ ልብሳቸውን እያነጠፉለት፣ "ንጉስ" እያሉት፣ "በእልልታና በሆታ" ቢቀበሉትም ኢየሱስ ለአፍታም አልፈገገም። ሳቅ አልታየበትም። ይልቅ ከፋው፣ አለቀሰ!😪 "ሆሳዕና" ብለው የጠበቁት ሳይሆን ሲቀርባቸው፥ "ይሰቀል!" እንደሚሉ እያሰበ አለቀሰላቸው። ከቀናት በኋላ ከነሕመማቸውከነነቀፋቸውከነቅጣታቸውከነፍርዳቸውከነመሞታቸው ራሳቸውን በእሱ ውስጥ ሲያዩ ፊታቸውን እንደሚያዞሩበት ስላወቀ ለራሱ ሳይሆን ለእነሱ አለቀሰ! ምን አይነት ፍቅር ነው እንደዚህ የሚያደርገው😪 (ሉቃስ ወንጌል  19: 37- 44) ዛሬስ እኛም እሱን የምንጠብቀው እሱን በሚያስለቅሰው ነገር ላይ ይሆን: እግዚአብሔር ፍፁም ማስተዋልን ያድለን🙏 ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን 🙏 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ

#ትምሐርተ_ፀሎት "ሳታቋርጡ ጸልዩ" እንደ ተባለ፣ ሁልጊዜ አባታችንና አምላካችንን እንጠራለን፣ እናነጋግራለን፣ #የልባችንንም_እናፈስሳለን። በዚሁ መካከል ደግሞ ወደ ራሳችን መለስ ብለን ከነፍሳችን ጋ
#ትምሐርተ_ፀሎት "ሳታቋርጡ ጸልዩ" እንደ ተባለ፣ ሁልጊዜ አባታችንና አምላካችንን እንጠራለን፣ እናነጋግራለን፣ #የልባችንንም_እናፈስሳለን። በዚሁ መካከል ደግሞ ወደ ራሳችን መለስ ብለን ከነፍሳችን ጋራ እናወራለንእንደ ቃሉ እናበረታታለን : የምንጠራውን አምላክ ይዘን ነፍሳችንን እናናግራለንዘማሪው ከነፍሱ ጋራ ይነጋገራል፤ "#ነፍሴ_ሆይ፤ ለምን ትተክዢያለሽ? ለምንስ በውስጤ ትታወኪያለሽ? ተስፋሽን በአምላክ ላይ አድርጊ" (መዝ 42፥5)። ይህ መዝሙር ዘማሪው አምላኩን የናፈቀበትጥም እንደያዛት እንስሳ አምላኩን የተጠማበት: የቅኔ ጸሎት ነውእግዚአብሔር ወደ ፈለግንበት ጕዳይ ወይንም ሁኔታ ድምፁን እስኪያመጣ የሚሻለው መተከዝ ሳይሆን፣ #የተከዘችውን_ነፍስ_ማነጋገር ነው። ራሳቸውን በእግዚአብሔር ቃል ማነጋገርና ማረጋጋት የሚችሉምለሌሎች ጽኑ መጽናኛ ይሆናሉሊያመነቱ ቢችሉም እንኳ ፈፅሞ ተስፋ አይቆርጡምሲፀለዩ በእግዚአብሔር የተስፋ ቃልና ፍፁማዊ ባሕሪው ላይ ተደግፈው ሰለሆነ : ከገጠማቸው ከየትኛውም ነገር በላይ ጌታ በቃሉ ታማኝ እንደሆነ ተንበርክከው ለነፍሳቸው ይነግራሉ ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ 👉 @biruk351         ♡ ㅤ    ❍ㅤ      ⎙       ⌲       ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ        ❍━━━━━━━━━━❍          @biruk351         @biruk351         @biruk351         🖇ተ🀄️ላ🀄️ሉን    ፀጋና እውነት ቤተክርስቲያን ጅማ

ሰላም በጅማ አከባቢ ለምትኖሩ ቅዱሳን ነገ ወዲያ አርብ የሚጀምር "ኢየሱስን የማድመቅ ኮንፍረንስ" በተገለጠ የእምነት ቃል ቤተክርስቲያን ተዘጋጅቷል ። በሰዓቱ ኢየሱስ ለእኛ ዘንድ የተሰጠ ሁለንተናዊ
ሰላም በጅማ አከባቢ ለምትኖሩ ቅዱሳን ነገ ወዲያ አርብ የሚጀምር "ኢየሱስን የማድመቅ ኮንፍረንስ" በተገለጠ የእምነት ቃል ቤተክርስቲያን ተዘጋጅቷልበሰዓቱ ኢየሱስ ለእኛ ዘንድ የተሰጠ ሁለንተናዊ #ገፀ_በረከት_መሆኑ_የሚታወጅበት: ኢየሱስ በመስቀል የሰራው ምትካዊ ስራ ያለ መሸቃቀጥ የሚሰበክበት እና ለሁሉም ነገራችን ኢየሱስ በቂ መሆኑን መንፈሳዊ መረዳት የምንካፈልበትና ይሆናልበዚህም ምክንያት ለበሽተኞች በልዩ ልዩ ጭንቅ ውስጥ ላሉ እጅ በመጫን የሚፀለይበት ድንቅ ጊዜ ይኖረናልመንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን ማክበር ይወዳልና በብዙ መገኘት ይኼንን ክብር ይመሰክርልናል ። በመገኘት ፀጋ ይካፈሉ 🙏 #አድራሻ_ጅማ_ኢሚግሬሽን_ቢሮ_ጀርባ ለበለጠ መረጃ ይደውሉ ፦0984970314 ፦ 0913465194         ♡ ㅤ    ❍ㅤ      ⎙       ⌲       ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ        ❍━━━━━━━━━━❍          @biruk351         @biruk351         @biruk351         🖇ተ🀄️ላ🀄️ሉን    ፀጋና እውነት ቤተክርስቲያን ጅማ

#ትምሐርተ_ፀሎት ....በመፀለይ እያመንኩ ያለሁበት ደረጃ ላይ ነኝ ! የዚህ ዘመን ችግር የእውቀት እጥረት ብቻ እንደሆነ ያመለከቱን ሰዎች እውቀቱንም በሚገባ ከገለጡና ከተነተኑ በኋላ ውጤቱን ማየት እየቻሉ አይደሉም! የሆነ ቦታ ስታክ አድርገናል: ሕያው ቃሉ የመማረክና የመግዛት አቅሙ በኑሮአችን ላይ በሚነቀፍ መልኩ ላልቷል። ምክንያቱም እየተማረክንለት አይደለም : ስለዚህም በሕይወታችን እውነተኛ ውጤት ቀዝቅዟል! ቃሉ ባለስልጣን ነው.. ቢሆንም እየተዋሃደን አይደለምና የእውነት የተጠቃሚነት መብታችን ተገድቧል። ምንድነው ግን መዋሃድ?  ጥቅስ አለማወቅ ነው?..  ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ የታሪክ ፍሰት አውድና ቋንቋን በረቀቀ ሁኔታ ማፍለቅለቅ አለመቻል ነው? አይደለም!! የትንታኔ እጥረት አይደለም! በአጭሩ አለመታዘዝ ነው!  እግዚአብሔር ይኼ ይጠቅምሃል በዚህ ሂድ ሲል አይ ብሎ በራስ ፈቃድ መጓዝ ነው ፣ እግዚአብሔር ያ ይጎድሃል ከሰጠው ክብር ጋር አይሄድም ሲል በራስ ፈቃድ ክብርን ማርከስ ነው! ስማኝ ተንበረክክ ሲልህ አለመንበርከክ ነው ፣ ከእግዚአብሔር ይልቅ ለሶሻል ሚዲያ ለጓደኞች ረጅም ሰዓት መስጠት ነው! መፍትሔው አንድ ወዳጄ እንዳለው መፀለይ ነው!  ፀሎት በእግዚአብሔር ላይ የሚደገፉ አቅመ ደካማነታቸው የገባቸው ሰዎች የሚሄዱበት መንገድ ነው። በጣም እያወቅን ሲመስለን በጣም ስንራቀቅ እውቀት ብቻ አእምሯችንን ሲገዛ: በፊት ከነበረን ልምምዳችን ወደ  ኋላ ኪስ በዋሌት ቦርሳ የምንከታት ነገር ብትኖር ፀሎት ነች። እናም ካልተጠነቀቅን ገና ልንበረከክ ስናስብ ስለ እግዚአብሔር ያለን እውቀት ያስጨንቀናል.. እናም እንራቀቃለን : ገና ሳልፀለይ ያውቃል ፣ ብፀለይ ባለፀለይ እርሱ ሉዓላዊ ነው በእኔ ሕይወት እርሱ የፈለገው ይሆናል ፣ መፀለዬ ምን ጥቅም አለው? እርሱ በእኔ ሕይወት ሁሉን አስቀድሞ ወስኗል..  ገና ይኼን የመሳሰሉትን ስታወጣ ስታወርድ: ሌላ በፀሎት መልሳቸውን የተቀበሉ፣ በፀሎት ያመለጡ ፣...መፅሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶች ያፈጡብሃል እናም ሼም ይዞህ ስትፀልይ ልባዊ ሆነህ ሳይሆን ስርዓታዊ ሆነህ ነው 😥   አስተውላችሁ ታውቃላችሁ? ጎበዝ የቃል አስተማሪዎች ቃላቸው ከአንደበታቸው ሲወጣ የሚጣፍጥላቸው እንኳ ፀሎት ሲጀምሩም ሲጨርሱም በሌላ ሰው ማፀለይ እንደሚፈልጉ? አንድ ወዳጄ እንዳለኝ የትኛውንም የመፅሐፍ ቅዱስ ሀሳብ ከሰዎች ጋር ለመወያየት ፣ መንፈሳዊ አጋዥ መፅሀፎችን ለማንበብ ፣ ደክሜ አቅሜ አጥቼ አላውቅም ሁሌም ግን የሚገርመኝ መፀለይ ሲባል አቅም አጣለው ፣ ስፀልይ ከየትኛውም ልምምዴ በላይ ሐልሆቱን፣ ጠረኑን አውቃለሁ ቢሆንም አቅሙን አጣለሁ። በመፀለይ ሕይወታቸው የሚገበዙ ሁሌም እንደ እነርሱ መንፈሳዊ የሌለ በማስመሰል የሚኮንኑ እንዳሉ አውቃለሁ ፣ የሚገርም የፀሎት ሕይወት እያላቸው  በአእምሮ ክፍላቸው የታደስ አመለካከት የሌላቸው ጨካኝ አማኞችን አውቃለሁ.. እኛ ግን ሚዛናዊ እንሁን እንፀልይ 🙏 #የእግዚአብሔር_መንፈስ_እርዳታ_ይብዛልን ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል እነዚህ ሊንክ ይንኩ 👇👇👇         ♡ ㅤ    ❍ㅤ      ⎙       ⌲       ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ        ❍━━━━━━━━━━❍          @biruk351         @biruk351         @biruk351         🖇ተ🀄️ላ🀄️ሉን    ፀጋና እውነት ቤተክርስቲያን ጅማ

#ትምሐርተ_ፀሎት(የቀጠለ) ዛሬም ቢሆን ልክ እንደ አምናው ለመፀለይ ከመፀለይ ውጭ ሌላ መፍትሄ የለውም: ፀሎት የቱንም ያህል ግራ የሚያጋባና "ጅልነት" ቢመስለንም እግዚአብሔር ግን በቤተክርስቲያን ውስጥ ያስቀመጠው ወይም የደነገገው ስርአት ነው: ኢየሱስ ፀልዮ ፀልዩ ካለ እኔ እከተልሃለሁ የምለውማ ምን ያህል መፀለይ አይኖርብኝ? ጳውሎስ ፀልዮ ፀልዩ ካለ ከእኔማ ምን ያህል ይጠበቅ!? ፀሎት በአቦ  ሰጡኝ ከሚመራ ሕይወት ይጠብቃል:: ኃይለኛ ፀሎታችን ሳይሆን ፀሎትን የሚሰማው እግዚአብሔር ነው፣ ስለዚህ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንንበረከካለን: ለፀሎት የልብ ልብ የሚሰጠንም የፀሎት ርእሳችን መተለቅ ወይም መብዛት ሳይሆን በሰማያት የሚኖረው አባታችን ነው:: “#አማኝ_በጣም_ “ያወቀሲመስለው መጀመሪያ የሚያቆመው ነገር መጸለይን ነውመጽሃፍ ቅዱስ ከሚያስተምራቸውና ክርስትና ከያዛቸው መንፈሳዊ እሴቶች መካከል ደግሞ አንዱ ይሄው “#ሞኝነት” #የሚመስለውንና “ስናውቅከኋላ ኪሳችን የምናስቀምጠውን ጸሎትን ነው፡፡ ጸሎት ከፍተኛ የሆነ እምነትን ወይም መታመንን ይጠይቃል፡ የሚጸልይ ሰው እግዚአብሔር አለ ደግሞም ጸሎትን ይሰማል ብሎ ያምናል ማለት ነው፡ ታዲያ እንደዚህ ማመን ከባድ አይደለምን? እንደዚህ የማያምን ሰው “ቢጸልይም” እየጸለየ አይደለም፡፡ ጸሎት የራስ ውስንነትን ወይም አለመቻልን ያገናዘበ ነው፡ በአጭሩ እውነተኛ ጸሎት የሚጸልይ ሰው “እኔ አልችልም አንተ ትችላለህ” እያለ ነው፡፡ የሚጸልይ ሰው በዚህ ዓለም ላይ “በአመጽ” እየተነሳ ነው: ምክንያቱም እግዚአብሔርን በዚህ ዓለም ውስጥ “#የአንተ_ፈቃድ_ይሁን” እያለው ነው፡ ሌላ ፈቃድ በነገሰበት ዓለም ውስጥ የእግዚአብሔርን ፈቃድ እየጠራ ነው። ከሰዎች ፈቃድ ጋር መጣመር ቀላል ነው፡ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ወይም ሃሳብ ጋር መጣመር ግን ከባድ ነው ምክንያቱም በጸሎት “ሞኝ” መሆንን ይጠይቃል። እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር በጸሎት “#ሞኝ_እንድንሆን_ይርዳን።         ♡ ㅤ    ❍ㅤ      ⎙       ⌲       ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ        ❍━━━━━━━━━━❍          @biruk351         @biruk351         @biruk351         🖇ተ🀄️ላ🀄️ሉን    ፀጋና እውነት ቤተክርስቲያን ጅማ

#ትምሐርተ_ፀሎት prayer ....ወደ ኋላ ልመልሳችሁ እና ሰው በኤደን ገነት ሀጢያት ከመስራቱ በፊት ከእ/ር ጋር ሲኖር ሳለ ፀሎት ነበረ ወይ?: የሚለውን መጠየቅ ያስፈልጋል። ፀሎት ስንል ቶሎ አእምሯችን ላይ የሚመጣ ነገር አለ፥ ብዙ ሰዎች በቶሎ የሚያስቡት መለመን ነው፣ አእምሯቸው ላይ ቀድሞ የሚመጣው፧ ነገር ግን ፀሎት ከልመና የሚያልፍ ነው ልመና ፀሎት አይደለም የፀሎት አንዱ ክፍል እንጂ መለመን ብቻ ፀሎት አይደለም። ፀሎት principle ነው ; አምላካችን በ የprinciple አምላክ ነው እ/ር የመርህ (የስርዓት አምላክ ከሆነ በprinciple የቀረቡ ሰዎች የሚፈልጉትን ነገር enjoy የሚያደርጉበት reality እንጂ ጨቅጭቀው እና ለምነው ያለፍላጎቶ ከእርሱ እጅ የሚቀበሉበት system አይደለም ። በመሰረቱ ተነዝንዞ ተጨቅጭቆ የሚሰጥ ትክክለኛ አይደለም ምክኒያቱም ተጨቅጭቆ ሰጠ ማለት አይፈልግም ነገር ግን ስለተጨቀጨቀ ነው የሰጠው። ለእንደዚህ አይነት ፀሎት ምሳሌ ስለ አንድ አመፀኛ ዳኛ መፅሐፍ ቅዱስ ሲናገር በአንዲት ከተማ አንድ አመፀኛ ዳኛ ነበረ፡ በየቀኑ እየመጣች ፍረድልኝ እያለች የምትጨቀጭቀው ሴት ነበረች፣ መበለት የሚለው ቃል በጣም ደካማ አቅም የሌላት እርዳታ የምትፈልግ ባል የሞተባት ሴት ማለት ነች። እቺ ሴት አመፀኛው ዳኛ ፊት ቀርባ እለት እለት ትጨቀጭቀው ነበር፥ ከባለ ጋራዬ ፍረድልኝ እያለች እለት እለት ስትጨቀጭቀው አመፀኛው ዳኛ ምንም ቢሆን እ/ርን ባልፈራ ሰውንም ባላፍር ስለ ንዝነዛዋ እና ስለ ጭቅጨቃዋ ከእንግዲህ እንዳታሰለቸኝ ለምን ፈርጄላት አልገላገልም በሚል ፈለረደላት ብሎ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ጥሩ ምሳሌ አቅርቦልናል። ይህ አመፀኛ ዳኛ ጥሩ ሰው አይደለም ከስሙም አመፀኛ ነው ይሄ የእ/ር ምሳሌም አይደለ፤ ይሄ ሰው ክፉ ነው ከክፉ መልካም ማውጣት አትችሉም የሰጠውም እንዳይጨቀጨቅ ለራሱ ሰላም እና እረፍት ሲል እንጂ ለሴትየዋ አዝኖላት አይደለም። ይሄ ክፍል በትጋት በአንድ ጉዳይ ላይ ስለ መፀለይ እንጂ የአባታችሁን የእ/ርን ባህሪ አያሳይም ፥ ሰው በውድቀት ከእ/ር ከመለየቱ በፊት ካለ ምንም ችግር በእ/ር መገኘት ውስጥ ሲኖር ሳለ ፀሎቱ እንዲህ ነበር ወይ? አሁን እኛን ጠዋት ማታ የሚያስጮሁን ጥያቄዎች ሳይኖሩ ችግር እና መከራ ሳይፈጠር ሰይጣን እና ሰይጣን ያመጣቸው ነገሮች ሳይኖሩ በ perfect world የሰው ልጅ የዚህ አለም ገዢ በነበረበት ወቅት ያን ጊዜ ፀሎት ነበረ: ልመና አልነበረም። ሲቸግራችሁ ብቻ እና ፀሎትን ልመና አድርጋችሁ የምትወስዱ ሰዎች አዳም እና ሔዋን ፍፁም እና ምንም ጥያቄ ባልነበረበት አለም ሲፀልዩ ከነበረ ምን ነበረ የሚለምኑት የሚለውን እራሳችሁን ጠይቁ። ከውድቀት በፊት ነበረ የሚለውን ሀሳብ ለማብራራት እፈልጋለሁ፤ ምን ነበረ የሚፀልዩት ከተባለ ፀሎትን መተርጎም የመጀመሪያው ስራችን መሆን አለበት። ፀሎት relationship ነው ፀሎት fellowship ነው ከእ/ር ጋር አባት እና ልጅ መሀከል የሚደረግ conversation ወይም ፍቅራቸውን የሚገልፁበት መንገድ ነው act of worship አንድ ልጅ ከአባቱ ጋር የሚነጋገርበት መነጋገሪያው ፀሎት ይባላል .......ይቀጥላል #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን 🙏 ወደቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351