cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ቃል ስጋ ሆነ⛪️⛪️⛪️

ይህ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን ስብከቶች መዝሙራት የቅዳሴ ምስባክ እና ማኅሌት የሚለቀቅበት ቻናል ነው። ይቀላቀላሉን በብዙ ያተርፋሉ።

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
200
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

✟ ዕድሜና ጤናውን ሰጥቶ ከበዓለ ሆሣዕናው በረከት ለመሳተፍ ያበቃን ልዑል እግዚአብሔር፤ ክብርና ምስጋና ይግባው። በእናቱ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ በቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ ለቅዱሳን አበው፣ ለነቢያት፣ ለሐዋርያት፣ ለጻድቃንና ለሰማዕታት በገባላቸው ቃል ኪዳን፤ በኃጢአታችን ምክንያት በሀገራችን በሕዝባችን እና በቤተክርስቲያናችን እንዲሁም በዓለማችን የመጣብንን ፈተና በቸርነቱ ያርቅልን። ሰሙነ ሕማማቱን በሰላምና በጤና አሳልፎ፤ ከብርሃነ ትንሣኤው በሰላም ያድርሰን። በቀሪው እድሜያችን ልዑል እግዚአብሔር የሚወደውን ፈጽመን፤ የመንግሥቱ ወራሾች ለመሆን ያብቃን።
Показати все...
#SafariomEthuopia: ድጅታችን በ100 ሚሊዮን ዶላር ወጪ በቃልቲ የዳታ ሴንተር ገንብቶ ለደንበኞች የስልክ: የኢንተርኔት: የብሮድባንድ አገልግሎቶችን ለማቅረብ ዝግጁቱን አጠናቋል:: የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችን አባል ለሆኑ ደንበኞች እነዚህን አገልግሎቶች #በከፍተኛ_ቅናሽ እናቀርባለን :: በተጨማሪም እጅግ ዘመናዊ አፕል ላፍቶፕ ኮምፒተርና አይፎን 13 ፕሮማክስ ስማርት ስልክ ይሸለማሉ :: ለወዳጅ ዘመዶቻችሁ ይህንመረጃ ያጋሩ ይህን ልዩ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይጋብዙ :: ይህን ሊንክ ተጭነው ወደ ቴሌግራም ገፃችን ይግብ :: https://t.me/+mdlD0Hgjq_ZlNmE0 ይህን ሊንክ ተጭነው የዩትዩብ ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ :: ከቅናሹ ይጠቀሙ ይሸለሙ https://youtu.be/qELHBnQ3SDY
Показати все...
አይጥ ጠዋት ከእንቅልፏ ስትነቃ በሯ ላይ ወጥመድ ተጠምዶ ታይና በጣም ትደነግጣለች!! ቀስስስስስ ብላ ዳር ዳሯን ይዛ ትሄድና ከቤቱ በር እንደወጣች ዶሮ ስትጭር ታገኛታለች... 🐭፡ እመት ዶሮ ጉድ ሆን🙆‍♂ ዛሬ በቃ አለቀልን😭 መሞታችን ነው.... እያለች ጆሮዋ ላይ ትጮህባታለች! 🐔: ምንድነው? ምን ተፈጠረ? የምን አደጋ ነው? 🐭፡ በቃ ዛሬ ጉድ ሆነናል🤷‍♂ 🐔፡ የሆንሽውን አትናገሪም እንዴ? 🐭፡ ጠዋት አገር አማን ብዬ ከጉድጓዴ ስወጣ በሬ ላይ ወጥመድ ተዘርግቷል... ዛሬ ማለቃችን ነው! 🐔፡ 😂 አይ አይጥ ቀልድሽ እኮ አይጠገብም! አንቺ በር ላይ ወጥመድ ስለተጠመደ እኔ ምን አገባኝ? አደጋው ያንቺው ነው በራስሽ ተወጪው!! ስትላት አይጥ አዝና ወደአሳማው ትሄዳለች!! 🐭: አሳምዬ ዛሬ ጉድ ሆነናል፣ በቃ ማለቃችን ነው፣ ጉድ ሆነናል🙆‍♂ 🐷፡ ቺ! ምን አይነቷ ናት በና... ምንድነው በጠዋት መዓት ምትጠሪው ምንድነው የሆንሽው?? 🐭፡ አሳምዬ የሆነ ነገር ካላደረግን ማለቃችን ነው! ጠዋት ስነቃ በሬ ላይ ወጥመድ ተጠምዶ አገኘሁ... ሳናልቅ በፊት አንድ ነገር እናድርግ!!😭 🐷፡ አቤት??😳 በርሽ ላይ ወጥመድ መጠመዱ የአሳማ ስጋት ነው ያለሽ ማነው በናትሽ?? አረ ፍቺ... አየሩን አትበክይው!! ቢላት ጊዜ አሁንም ተስፋ ባለመቁረጥ የዋህ ነው ዝም አይለኝም ብላ አያበጉ ሳር ወደሚግጥበት መስክ መሄድ... 🐭፡ በግሻ እንዴት አደርክ?! ብታይ ጉድ ሆነናል! የሞት አደጋ ከፊታችን ተደቅኗል!🙆‍♂ እባክህ አንድ ነገር እናድርግ!!😭 🐏፡ አይጧ እስኪ ተረጋጊ እና እንነጋገር! ምንድነው የሆንሽው? ተረጋጊ ለሁሉም ነገር መፍትሄ አይጠፋም! 🐭፡ ጎሽ በግዬ መፍትሔ እንደማታጣማ አውቄ ነው አንተ ጋር መምጣቴ! እየውልህ ልክ ጠዋት ከጉድጓዴ ስወጣ በሬ ላይ ወጥመድ ተጠምዶ አላገኝ መሰለህ?? ተባብረን አንድ ነገር ካላደረግን ማለቃችን ነው!!🤷‍♂ 🐏፡ እና ይኼ ከእኔ ህይወት ጋር ምን ያገናኘዋል? 😂😂 እዛው የአይጥ መረዳጃ ማኅበርሽ ላይ ሄደሽ 'እኛ' በይ እንጂ እኔ አንቺ ጉድጓድ አልኖር... ምንድነው ጉድ ሆነናል የምትኝ... እኔ ደግሞ ምን በዓል ደርሶ ይሆን ብዬ መደንገጤ... ብሎ ቀልቧን ቢገፈው... ለመጨረሻ ጊዜ ተስፋ ባለመቁረጥ አያ በሬው መላ አለው ብላ ከግቢው ወጥታ መስኩ ላይ ሳር የሚግጠው በሬ ጋር ደርሳ.. 🐭: አያ በሬው... ጉድ ሆንን!🙆‍♂ በቃ ማለቃችን ነው😭 ማናችንም አንተርፍም ነው የምልህ!! 🐂: ምንድነው እንዲህ የሚያስደነግጥሽ? ምን ሆነሽ ነው?? ምንድነው ጉዱ?😳 🐭፡ በቃ አያ በሬው አሁኑኑ ተነጋግረን አንዳች ነገር ካላደረግን ጠፋን! በቃ ጠፋን! ልክ ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ በሬ ላይ ወጥመድ ተጠምዶልሃል... አሁኑኑ ሁሉንም አስተባብረን አንድ ነገር ካላደረግን... በቃ ማናችንም አንተርፍም!!🙆‍♂😭 🐂፡ ስንት አይነት አይጥ አለ በናታችሁ! አንቺ ከንቱ አንቺ ጉድጓድ ላይ ወጥመድ ስለተጠመድ እንዴት ሆኖ ነው ሁላችን የምንጠፋው?😂 ስራ ፈት ሂጂ ከዚ...!! ሆነ መልሱ! አይጥ ተስፋ ቆርጣ... ቅስስ ባለ አረማመድ በጥንቃቄ ወጥመዱን አልፋ ጉድጓዷ ገባችና ኩርምት ብላ ቁጭ ከማለቷ... ከወደውጪ ኡኡታ🙆‍♂... ነገሩ እንዲህ ነው(ይላል የተዘጋው ዶሴ ተራኪ)... ለአይጥ የተዘረጋው ወጥመድ ቤት ውስጥ ሳይታሰብ የገባውን እባብ🐍 ይይዘዋል.... የቤቱ እማወራ👵 ወጥመዱ መያዙን ሰምተው ሊያዩ ብቅ ከማለታቸው የተያዘው እባብ የሞት ሞቱን መርዙን ቢረጭ እግራቸውን ይነድፋቸዋል!! እሪሪ ሲሉ አባወራው👴 መድረስ... በፍጥነት የሰፈር ሀኪም👨‍⚕ ሲጠራ... ቁስሉን ግጥም አድርጎ አስሮ... 👨‍⚕: እባብ ለነደፈው ሰው የዶሮ መረቅ እጅግ ፍቱን ነገር ነው... እንዳው እስኪ ፈጠን አድርጋችሁ አዘጋጁላቸው!! ሲላቸው አባወራው👴 🦃🔪🩸 ዶሮውን አርደው #መረቅ!! እሜትዬ 👵 ደግሞ መርዙ ክፉኛ ዘልቋቸው ኖሮ... ለሳምንት ተኝተው ታክመው ምንም አልሻላቸው አለ!! የሰፈሩ ሀኪምም 👨‍⚕: ይኼ ነገር ማምረሩ ነው እና ከተማ ሄደው በሃኪም መታየት ይኖርባቸዋል!! አባወራው👴 በጊዜው ብር አልነበራቸውምና 🐖🔪🩸 አሳማውን አርደው ሸጠው እሜትዬን👵 ሊያሳክሙ ወደከተማ 🚑 እሜትዬ👵 ከተማ ሊታከሙ በሄዱበት መታመማቸውን የሰሙ ዘመዶቻቸው👨‍👩‍👦👨‍👩‍👧👨‍👩‍👧‍👦 ሊጠይቋቸው ወደእነእሜትዬ ቤት ይጎርፋሉ... ያው ገጠር እንደመሆኑ ጠያቂው ሁሉ ከራሚ ነበርና ያን ሁሉ ሰው ለመመገብ መደበኛ ቀለብ አይበቃም!! የአባወራው👴 ልጅ👨‍🦰 🐏🔪🩸 በጉን አርዶ በልቶ ለሰራተኛዎቹ መስጠት.... እሜትዬ👵 ግን ያው መቼም ክፉኛ ተነድፈዋል ቀናቸውም ደርሶ ነበርና ነፍሳቸው አልከርም ብላ ሆስፒታል ውስጥ እያሉ አረፉ⚰! ለቀብር🙆‍♂😭 የመጣው ህዝብ ህዝብ አይደለም መቼም.... አብዬም👴 ከሚስቴ ወዲያማ ምን ቀረኝ ብለው 🐂🔪🩸 በሬውን አርደው ለቀስተኛ መሸኛ ሲያደርጉት... ይኼንን ሁሉ ቁጭ ብላ የታዘበች ማናት?? 🐭 ባለወጥመዷ!! አይን ሲታመም፣ መላ ሰውነት ይታመማል... አካል ችግር ሲገጥመው፣ መላ ሰውነት መከራ ያንዣብብበታል!! የወንድምህ ችግር አፍንጫዬ ላይ ካልደረሰ አያገባኝም አትበል!! መልካም ረቡዕ... መልካም የጥምቀት በዓል!!
Показати все...
"ክልኤቱ አእሩግ አመ በከዩ ብካየ ረከቡ ወለተ ዘታስተሰሪ ጌጋየ ለወንጌላውያን ኩልነ ዘኮነተነ ምጉያየ ኢያቄም ወሐና ወለዱ ሰማየ ሰማዮሙኒ አሥረቀት ፀሐየ" (ኹለቱ አረጋውያን ልቅሶን ባለቀሱ ጊዜ ለኹላችን ወንጌልን ለምናስተምር መሸሻን የኾነችን በደልን በምልጃዋ የምታስደመስስ ልጅን አገኙ፤ ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱ፤ ሰማያቸውም ፀሐይን አወጣች) ነግሥ እናቶቻችንን ምን ያክል እንደምንወድ ኹላችን እናውቃለን ገና በልጅነቷ እናቷን ያጣች እመቤታችን ደግሞ የሀናን መዓዛ እጅግ ትወዳለች ያጠባቻትን ጡጦችዋን ትናፍቃለች እኛም ለዚህ ነው "በእንተ ሐና እምኪ" ብለን የምንማጸናት። አንዳንዶቻችን ያለ እናት አንዳዶቻችን ያለ አባት አድገናል አለፍ ሲልም ኹለቱንም አጥተን ያደግንም ጥቂቶች አይደለንም ፤ የዓለማትን ጌታ የወለደች የሁላችን እናት ያለ እናት ያለ አባት ማደጓን ባሰብን ጊዜ ከሀዘናችን እንጽናናለን፤ እንደ እርሷም በቤተ መቅደሱ በደጀ ሰላሙ እናድጋለን እንኖራለንም። ዲ/ን ዘ፲፪ እሸቱ ሕዳር 10/2014ዓ.ም. አ.አ ኢትዮጵያ
Показати все...
++ አባቶቻችን እንዲህ አሉ ++ "መካሪ አያስፈልገኝም የማለትን ያህል ታላቅ ትዕቢት የለም" ቅዱስ ባስልዮስ "በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ ጸሎትህን እንዳታቆም። ንስሓ እስከምገባ ድረስ ብለህ ጸሎት ካቆምክ መቼም ንስሓ አትገባም። ምክንያቱም ጸሎት ራሱ የእውነተኛ ንስሓ መግቢያ በር ነው" ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ "ሰዎች አንድ ሰው ተነሥቶ ሌላውን ሲገድል ወንጀለኛ ነህ ይሉታል። አንድ ላይ ተሰባስበው ብዙ ሰዎችን ሲገድሉ ግን ውጊያ ይሉትና መግደላቸውን ጀግንነት ይሉታል" ቅዱስ ቆጵሮሳዊ "የክርስቲያኖች መሣሪያ በእጃቸው ሰይፍን መታጠቅ ሳይሆን እጃቸውን ወደላይ ለጸሎት መዘርጋት ነው" ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ "እግዚአብሔር ለአብርሃም "ከሀገርህ ውጣ ከወገኖችህ"ተለይ ብሎት ነበር። በዚህ ጥሪ እግዚአብሔር ሁላችንንም የተወለድንበት ዘር እንድንተው ይጠራናል። ሰማዕቱ ዮስጦስ (100 AD-165 AD) "ክርስቶስ ጴጥሮስን "ሰይፍህን ወደ ሰገባው አስገባ" ሲለው ትጥቅ ያስፈታው ጴጥሮስን ብቻ ሳይሆን እንደ ጴጥሮስ በእርሱ የሚያምኑትን ሁሉ ነበር" ሊቁ ጠርጡለስ (160 AD - 220 AD) ‹‹ይጸልያል ነገር ግን የሌሎችን ጸሎትም ይሰማል፡፡ ያለቅሳል የሌሎችን ዕንባ ግን ያብሳል፡፡ ሰው ነውና አልዓዛር ወዴት እንደተቀበረ ጠየቀ፡፡ አምላክ ነውና አልዓዛርን ከሞት አስነሣ፡፡ እርሱ በርካሽ ዋጋ ያውም በሠላሳ ብር ብቻ ተሸጠ፡፡ ነገር ግን ዓለምን በውድ ዋጋ በከበረ ደሙ ገዛ፡፡ እንደ በግ ለመታረድ ተነዳ እርሱ ግን የእስራኤል እረኛ የዓለምም ሁሉ ጠባቂ ነበረ፡፡ እንደ በግ ዝም አለ ነገር ግን እርሱ በምድረ በዳ በሚጮኽ ሰው ድምፅ የተሰበከ ቃል ነበር፡፡ እርሱ የተሰቃየና የቆሰለ ነበር ፤ ሁሉንም በሽታና ቁስል ግን ይፈውስ ነበር›› ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ "ለቤተ መቅደስህ ተክል ያደረግኸኝ፡፡ አቤቱ ሆይ የውጭ ተክል አታድርገኝ፡፡ የጽድቅ ተክል አድርገኝ፡፡ የኃጢአት አይደለም፡፡ የዕውነት ተክል አድርገኝ የሐሰት አይደለም የፍቅር ተክል አድርገኝ የጽል አይደለም፡፡ የመጻሕፍት መጀመሪያ የምትሆን ኦሪት ደመና የምትጋርደኝ፡፡ ከቅዱስ ወንጌል ፈሳሽ የምጠጣ ከጎንህ ከፈሰሰው ደም የምረካ ልሁን፡፡ በናትህ በድንግል ጸሎት የሃይማኖት አበባ ላብብ፡፡ የጽድቅ ፍሬን ላፍራ ከቅዱሳንህ ሐዋርያትም ከቃላቸው ፍሬ የተነሣ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ የተባረከ የወይን ቦታ ልባል የጽድቅን ፍሬ የሚያስቀረውንም የኃጢአት እሾህ ጠምዝዘው ከደጁም አሜከላውን አረሙንም ሙጃውንም ንቀለው፡፡ አቤቱ ከኔም አርቀው ሥርዓትህን የሚሠሩትን ያበባቸውን ፍጻሜ እንዳፈራ አድርገኝ" ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
Показати все...
የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፤ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ፤ ፀሐይና ብርሃን ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ፥ ደመናትም ከዝናብ በኋላ ሳይመለሱ፤ ቤት ጠባቆች በሚንቀጠቀጡበት፥ ኃያላን ሰዎችም በሚጎብጡበት፥ ጥቂቶች ሆነዋልና ፈጭታዎች ሥራ በሚፈቱበት፥ በመስኮትም ሆነው የሚመለከቱ በሚጨልሙበት፥ በአደባባይም ደጆቹ በሚዘጉበት ቀን፤ ከፍ ያለውን ደግሞ ሲፈሩ፥ ድንጋጤም በመንገድ ላይ ሲሆን፤ ለውዝም ሲያብብ፥ አንበጣም እንደ ሸክም ሲከብድ፥ ፈቃድም ሲጠፋ፤ ሰው ወደ ዘላለም ቤት ሲሄድ፥ አልቃሾችም በአደባባይ ሲዞሩ፤ አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፥ ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ። መጽሐፈ መክብብ 12 : 1-7 መልካም አዲስ ዓመት
Показати все...
መጽሐፈ ጨዋታ ወንጌላዊ ክፍል ፭ ኢዮብ መከራ ቢታገስ ለራሱ ብዙ እድሜ እጥፍ ገንዘብ አገኘ ክርስቶስ ግን ያንን ሁሉ መከራ ቢታገስ ለእኛ ጥቅም ነው እንጂ ለራሱ አይደለም። ሶምሶን በሶስት መቶ ቀበሮ ጅራት እሳት አቆራኝቶ የፍልስጥኤምን አዝመራ አቃጠለ። ክርስቶስ ግን በአስራሁለቱ ሃዋርያት መንፈስ ቅዱስን አቆራኝቶ አለሙን በፍቅር እሳት አቃጠለ። የእግዚአብሔር ልጅስ እጅግ ቀላ ሥጋ መሰለ እውራኑም እያዩ ደንቆሮዎችም እየሰሙ አንካሶችም እየሮጡ አደነቁት። ክርስቶስ በደብረ ታቦር ላይ ቢለወጥባቸው ሁሉም ወደቁ ።ጴጥሮስ ይለፈልፍ ጀመር፣ይህ ባላገር አምላክን አይቷት አያውቅምን ይሆን፣አምላክን አይቶ እንደዚህ የፈራ ሌላ መከራ ቢመጣበት እንዴት ሊሆን ነው። የፍቅር ምንጭ ማነው ክርስቶስ ነው። አምስት ሺ አምስት መቶ ዘመን ለተራቡ ስጋውን ለተጠሙ ደሙን ለግሷልና።አይሁድ ጦማቸውን አጥርተው ይጦማሉ፣ክርስቲያኖች ግን ጦማቸው የጠራ አይደለም ፣አርብ የታረደውን የበግ ስጋ ይበላሉና።አይሁድ ከእንስሳ እንኳ ለይተው ነው የሚበሉት ክርስቲያኖች ግን ወንድማቸውን ነው የሚበሉት። ዮሐንስ እነሆ የእግዚአብሔር በግ ሲል አይሁድ ላይበሉት ተሽቀዳድመው አረዱት።እነሆ አይሁድ ያረዱትን በግ አሕዛብ እየበሉ ወፈሩ።ቁመታቸውም እስከ ሰማይ ደረሰ።እስራኤል ግን ኮስሰው የማንም መጫወቻ ሆኑ። መጽሐፍ አንዳንድ ጊዜ አያውቅም ሰው ቢሞት ደስ አይበልህ ይላል።ክርስቶስ ባይሞት ለኔ መንግስትን ማን ይሰጠኝ ኖሯል።የእርሱ ሞት እኔን ጠቀመኝ እሰይ እሰይ እንኳን የሞተልኝ።እልል እልል እንግዲህማ ስጋውን ብበላው ደሙንም ብጠጣው።ምነው እኔን የመሰላችሁ ሁሉ ደስ ይበላችሁ። ዳዊት ይሁዳን አገሩ ምድረ በዳ ትሁን እያለ ምነው ይራገማል።እርሱ ካልበላሁለት ብሎ ነውን እንደ ይሁዳ ያለ መልካም ነጋዴ የለም ።የዘለዓለሙን ምግብ በ 30 ብር ሸጠልን። የእግዚአብሔር ልጅስ እጅግ በረታ ከአንዲት ሴትዮ ስጋቱን ነጥቆ ወስዶ በሰው መካክል በቀራንዮ ሰቀለው።አወይ አለማፈር። እግዚአብሔር ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ከሙሴ ጀምሮ እስከ ነቢያት ድረስ ጮኸ፣ጮኸ የሚሰማው ታጣ፣ቃሉም ታሰረ እንግዲህ በምኑ ይናገራችሁ። https://t.me/Kalsigahone17
Показати все...
ቃል ስጋ ሆነ⛪️⛪️⛪️

ይህ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን ስብከቶች መዝሙራት የቅዳሴ ምስባክ እና ማኅሌት የሚለቀቅበት ቻናል ነው። ይቀላቀላሉን በብዙ ያተርፋሉ።

መጽሐፈ ጨዋታ ወንጌላዊ ክፍል ፭ እግዚአብሔር ፈሪ ነው እኛ ብንበድለው ልጁን ልኮ ቀስ ብለህ ተዛምደህና ብሎ በልጁ ታረቀን፣አሁን ምን ያደርጉኝ መስሎት ነው ለካ በየቤቱ ፍርሀት አይታጣም እኛ ስለ በደልነው የምንክሰውን እርሱ ካሰን። እንግዲህ ወዲህ ስጋችን ከሆነ በሰበብ ባስባብ ብለን ከእርስቱ እንካፈለዋለን፣ ጥቂት ስጋ በአንድ መርፌ ትወጋ እንዲሉ እንኳን ልጁን ልኮ ተዛመደን። የክርስቶስ ነገር አጅግ አስቸገረ ፣ልጅ ስለሆነ ይሆን፣አንድ ጊዜ ተርቤ አላበላችሁኝም ይላል፣ አንድ ጊዜ አምስት እንጀራ ለአምስ ሺህ ህዝብ አብልቶ አትርፎ ያነሳል። ለበሬ ቀንድ አለው ፣ለንጉሥም ዘውድ አለው፣እረ ለእግዚአብሔር የምንሰጠው ክብር ምንድር ነው፣አንለይለትምን አምልኮ፣ ስግደት፣ ምስጋና ፣ለእርሱ ነው በጣም እንገዛው፣እንለማመጠውም።እንታጠቅለትም።ታላቅ ጌታ ፣ሰጭም ነሽም ነውና። አዳኝም ገዳይም እርሱ ነውና።በሰማይና በምድር ከእርሱ በቀር የለም።ሁሉ ከእርሱ ነው የተገኘው ሁሉ በእርሱ ነው የሆነው ።ያለ እርሱ ምንም የሆነ የለም ምስጋና ይገባዋል ለዘለዓለሙ አሜን። እግዚአብሔር እሩቅ ነው ጥበቡ አይታይምና። እግዚአብሔር ቅርብ ነው ቶሎ ይሰማልና። እግዚአብሔር መኰንን ነው ቶሎ ይፈርዳልና። እግዚአብሔር እንግዳ ነው ቶሎ ወሬ ይሰማልና። እግዚአብሔር ትሑት ነው ሰውን አይንቅምና። እግዚአብሔር መሐሪ ነው ቶሎ ይቅር ይላልና ርኅሩኅ ነው። እግዚአብሔር ሐኪም ነው ሁሉን በጥበብ አድርጓልና። እግዚአብሔር ምስጉን ነው ፀሐይን ጨረቃን ፈጥሯልና። እግዚአብሔር ክቡር ነው ሰማይና ምድር የእርሱ ናቸውና። እግዚአብሔር ባእለጸጋ ነው ለሁሉ ይመግባልና። እግዚአብሔር ረቂቅ ነው አይጨበጥምና። እግዚአብሔር ግዙፍ ነው በዓለሙ ሁሉ ሞልቷልና። እግዚአብሔር ብሩህ ነው ጨለማ የለበትምና። እግዚአብሔር ኃያል ነው የሚቋቋመው የለምና። እግዚአብሔር እሳት ነው እጅግ ያስፈራልና። እግዚአብሔር መካር ነው መጻህፍትን ሰጥቷልና ። እግዚአብሔር አባት ነው አሳድጐናልና። እግዚአብሔር ወንድም ነው ሰው ሆኗልና። እግዚአብሔር ወዳጅ ነው የሆዱን ነግሮናልና። እግዚአብሔር ሀገር ነው እንኖርቀታለንና። እግዚአብሔር ማርና ስኳር ነው ይጣፍጣልና። እግዚአብሔር ገናና ነው የሚያህለው የለምና። እግዚአብሔር ትልቅ ነው ስፍራ አይበቃውምና። እግዚአብሔር ጥልቅ ነው በዋና አይገኝምና። እግዚአብሔር ፋሲካ ነው ለሁሉ ታርዶልና። እግዚአብሔር ዐመት በዓል ነው ለሁሉ ደስታ ነውና። እግዚአብሔር ጨው ነው ሁሉን ያጣፍጣልና። እግዚአብሔር ክረምት ነው ሁሉን ያበቅላልና። እግዚአብሔር አይጠረጠርም ሁሉን ያውቃልና። እግዚአብሔር አይዘነጋም በሁሉ ድካም የለበትምና። እግዚአብሔር አይሰጋም የሚሽረው የለምና። እግዚአብሔር የሰው ሎሌ ነ፣ በክረምት ለማብቀል፣ በበጋ ለማብሰል፣ የተዘጋጀ ነው። እግዚአብሔር እንግዳ አይደለም ፣ከጥንት የነበረ ነውና። ምስጋና ይሁን ለአብ ፣ለወልድ፣ ለመንፈስ ቅዱስ፣ ጥንት ለነበረ ፣አሁን ላለ ፣ኋላም ለሚኖር ፣አሜን። https://t.me/Kalsigahone17
Показати все...
ቃል ስጋ ሆነ⛪️⛪️⛪️

ይህ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን ስብከቶች መዝሙራት የቅዳሴ ምስባክ እና ማኅሌት የሚለቀቅበት ቻናል ነው። ይቀላቀላሉን በብዙ ያተርፋሉ።

መጽሐፈ ጨዋታ ወንጌላዊ ክፍል ፬ እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ አለ መብራት አብርቶ ከእንቅ ቀታች የሚያኖር ያለም ይላል።ዓለምን ያህል እንቅብ ደፍቶብን የለምን፣እኛ በወዴት እናብራ ጳውሎስስ እንኳ እስከ እድሜው ልክ አበራ። አንተ ነጋዴ እያላችሁ ስለምን ትሳደባላችሁ፣ ገበያ ተደመቀ ምን ደኅና አለ፣ከእግዚአብሔር የበለጠ ምን ንጉስ አለ፣ገበያ ቢያመቸው 1 ልጁን ለዓለም አለወጠውምን ዮሴፍንስ ወንድሞቹ ለ 30 ብርቱካን አልሸጡትምን።ከተሸጠስ ከዃላ ግን ለሜድረ ግብጽ እና ለከነአን የረሃብ መድኀኒት ሆነ። አንበሳ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ዱር ገባ ምን እንስሳ ይሰብር ይሆን፣ከዲያብሎስ በቀር። እነዚያ 4 መላእክት እንስሶች ናቸው።ከጀርባቸው ላይ ወጥቶ ተሰው ላይ ሲወድቅ አለመናገራቸው ከነዚህስ ገብርኤል ይሻላል ተሽቀዳድሞ ወጥቶ ለቆንጆይቱ የነገረልን። የሰማይ እሳት ከሰው ላይ ወድቆ አለማቃጠሉ ምንድር ነው። ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔር ልጅስ ገንዘባችሁን እየሰበሰባችሁ ወደ ሰማይ ላኩ፣ ከዚያ ይቆያችኋል ይለናል። ለካ የእርሱ ገንዘብ አላበቃው ቢል ወደእኛ ልጁን የላከው ቀስ ብሎ ገንዘባችንን በብልሃት እንዲያከማች ኖሯል። እንግዲህ አውቀንበት ገንዘባችንን አናባክን፣ከሰማይስ እኛ ምን አለን፣ገንዘባችንን ወደዚያ አሸክመን ከምንልክ አንካሶችን እውሮችን፣ችጋረኞችን ወንድሞቻችንን ይዘን እንክት አድርገን እንበላዋለን፣እንጠጣዋለን ፣እንለብሰዋለን፣በገዛ ገንዘባችን ምን ይመጣብናል ። አላመጣችሁም ብሎ የሚያደርገውን እናያለን። አባቶቻችንን ከዚ ቀደም አታሎ የወጣው ገንዘብ ይበቃዋል፣ባለፀጋ ወደ መንግስተ ሰማያት ከሚገባ ገመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይሻላል ይላል። ከእርሱ የበለጠ ባለጸጋ አለን፣እርሱ በመንግስተ ሰማት ይኖር የለምን፣ይህንንም እያመካኘ የሰው ገንዘብ አሻግሮ ማየቱ ምንድንነው ከዚህ ቀደም አስሩን ተናግሮ ተናግሮ ከወንጌል አደረሰን ፣አታስቡ እያለ ገንዘባችንን ቢያስበላብን ወዲያው ተርቤ አላበላችሁኝም። ተጠምቼ አላጠጣችሁኝም ። ታርዤ አላለበሳችሁኝም። ታምሜ አልጠየቃችሁኝም ። እኝግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝም። ታስሬ አልጠየቃችሁኝም ። ይህን ያህል 6ቃል ምን ያናግረዋል።ወዲህ ለነገ አታስቡ ይላል ።ወዲህ አላበላችሁኝም ይላል።ከእኛ ወገን የተራበ ፣የተጠማ ፣የታረዘ የለም መስሎት ይሆን ፣ከሰማይ ተሰዶ መጥቶ ተርቤአለሁ፣ ተጠምቻለሁ፣ታርዣለሁ ምንድር ነው፣ሰማይን ያህል ሰፊ አገር ይዞ አባቱ ከዚያው አይመግበውም፣ አያጠጣውም ፣አያለብሰውም፣ልጁስ ቢቀላውጥ ለእርሱ ነውር አይፈራምን።እኛስ ለሰማይ ንጉስ ልጅ አናበላም፣አናጠጣም፣አናለብስም፣ከዚሁ ካሉት ከድሆች ወንድሞቻችን ጋር ገንዘባችንን ተካፍለን እንበላለን፣እንጠጣለን፣እንለብሳለን፣ እንደዚህ ያለ ዘወትር ንዝንዝ ምንድር ነው።በወንጌል ገንዘባችን ሊወርስ።የጦም አዳር እያለ ሊከፍለን አስቦ ነው መሰል። https://t.me/Kalsigahone17
Показати все...
ቃል ስጋ ሆነ⛪️⛪️⛪️

ይህ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን ስብከቶች መዝሙራት የቅዳሴ ምስባክ እና ማኅሌት የሚለቀቅበት ቻናል ነው። ይቀላቀላሉን በብዙ ያተርፋሉ።

Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.