👑Ethio pic
የ ኢትዮ pic አባል በመሆን በፎቶ ውድድር ይሸለሙ ለማንኛውም አስተያየት @yowbizz or @tteda @naniboy1 ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር ታላቅ የ pic Competition Telegram ላይ ታዋቂ famous ለመሆን ከፈለጉ የእርስዎን አሪፍ pic ይላኩ👌 👇👇 Join us👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAESVJQasdYJg0blmXQ
БільшеКраїна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
289
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
- Підписники
- Перегляди допису
- ER - коефіцієнт залучення
Триває завантаження даних...
Приріст підписників
Триває завантаження даних...
ትምህርት ተከፍቶ የዜግነት ክብር ሲባል
═══••🇪🇹••═══
የኮሮና ፍርሃት በኢትዮጵያችን ፀንቶ
ታየ ቤት መቀመጥ ዳር እስከ ዳር ብርቶ
ለሰላም ለፍቅር ለህዝቦች ነፃነት
እጃችንን ታጥበን ቆመናል በርቀት
መሰረቱ ፅኑ በሽታ መጥቶብን
ህዝቦች ነን ከስራ ከስራ የራቅን
ድንቅ ገዳይ በሽታ የሞትም ባለቤት
የተፈጥሮ እርግማን የበሽታዎች ሁሉ እናት
እንርቅሃለን አለብን አደራ
ኮሮና ጥፋልን እኛም ስራ እንስራ
የምን አንብቦ ማለፍ ነው ገባ ገባ በሉ እንጂ @ethiopicc01
እናሆ ምስጋና፤
ሰባራ ባቡር አካባቢ የሚገኘው ዕድገት በህብረት ህንጻ ባለቤቶች 150 ለሚሆኑ ተከራዪቻቸው ለሁለት ወር በነፃ እንዲገለገሉበት ፈቅደውላቸዋል።
ለአከራዮች ያቀረብነውን ጥሪ ተከትሎ ይሄንን ውሳኔ በመወሰናቸው አክብሮቴን መግለጽ እፈልጋለሁ።
ሌሎች አከራዮችም የእነሱን ፈለግ እንደሚከተሉ ባለሙሉ ተስፋ ነኝ።
[Takele Uma Banti]
ቻይና የኮሮና ቫይረስ የመጀመሪያዎቹን ሁለት የህመም ደረጃዎች ለማከም የተጠቀመችባቸውን የባህል መድሃኒቶች ለኢትዮጵያ በድጋፍ መልክ ልትሰጥ ነው፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የጤና ሚኒስቴር ከቻይና የባህል ሃኪሞችና ተመራማሪዎች ጋር ቫይረሱን መቆጣጠር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ተወያይተዋል፡፡
ቻይና የባህላዊ መድሃኒቶችን በመጠቀም ስኬታማ በሆነ መልኩ የኮሮና ቫይረስን መቆጣጠር የቻለችባቸው መንገዶችን ለኢትዮጵያ ለማጋራት ፍቃደኛ መሆኗን ገልፃለች፡፡
በተለይ የቫይረሱ ህመም የመጀመሪያዎቹ ሁለት ደረጃዎችን ለማከም የተጠቀመችባቸውን ሁለት የመድሃኒቶች ዓይነቶች ለኢትዮጵያ በድጎማ መልክ ለመስጠት ተስማምታለች፡፡
ረጅም እድሜ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ የባህል ህክምና ተቋማዊ በሆነ መልኩ ወደ ስራ እንዲገባ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረትም በቴክኖሎጂ፣ በቁሳቁስ እና በሙያም እደግፋለሁ ብላለች፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር ኢንጂ.) የኮሮናን ቫይረስ ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ ሀገር ከተጀመሩ ስራዎች ጎንለጎን የቻይና ድጋፍ ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ የባህላዊ መድሃኒቶችም ህጋዊ ማዕቀፍ ኖሯቸው ወደ ስራ እንዲገቡ የተጀመረው ጥረት እንዲሳካም የቻይናን ልምድ ኢትዮጵያ ትፈልጋለች ብለዋል፡፡
[Ministry of Innovation and Technology - Ethiopia]
#ኮቪድ19 በዓለም አቀፍ ደረጃ በማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚ ዘርፎች የሚያስከትለውን የጫና ክብደት በመገንዘብ፣ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ባለፉት ሳምንታት ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል ሲዘጋጅና ርምጃዎችን ሲተገብር ቆይቷል፡፡
እስካሁን ሊከሰቱ የሚችሉትን ፈታኝ ሁኔታዎች ያለማቋረጥ በመገምገም፣ ከሁኔታዎቹ ጋር ተመጣጣኝ የሆኑ ርምጃዎች ሲወሰዱ ቆይቷል፡፡ የኮቪድ19 ወረርሽኝ በዓለም አቀፍም ሆነ በሀገር ደረጃ መስፋፋቱን በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚኒስቴሮች ምክር ቤት፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 93 በተደነገገው መሠረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ደንግጓል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሁሉም ሰው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ድንጋጌዎች ተፈጻሚ እንዲያደርግ እና የጤና ሚኒስቴር ያወጣውን ቫይረሱን የመከላከል መመሪያ በጥብቅ እንዲተገብር ይጠይቃሉ፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት የኮሮና ወረርሽኝ እየተባባሰ በመምጣቱ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ ዐውጇል፡፡
#Ethiopia declares state of emergency to fight #COVID19
Оберіть інший тариф
На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.