uk
Feedback
SOZO YOUTH

SOZO YOUTH

Відкрити в Telegram

Helping young Christians pursue purity, purpose, relationships, and spiritual maturity. » YOUTUBE https://www.youtube.com/@sozopodcast » TIKTOK https://www.tiktok.com/@s.o.z.o For comment: @inbox_sozo P.O.BOX 387 /1033 ADDIS ABABA

Показати більше
5 794
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 день
Архів дописів
በወጣቶች የሚነሱ ጥያቄዎች በሚል እርስ ብሩስ እና ካሮል ብሪትን ተፅፎ በአለማየሁ ማሞ የተተረጎመው መፀሀፍ በወጣቶች ተዘውትረው የሚነሱ ርዕሶችን ስለትዳር ፣ ስለትጭጭት(ፍቅር) ፣ ቅድመ-ጋብቻ ግብረ-ስጋ ግኑኝነት ፣ እንዲሁም የብዙ ወጣቶች ጥያቄዎችና ከክርትያናዊ መልሶቻቸው ጋር ይዞ ቀርቧል ፣ ትማሩበታላችሁ። አንቡት! ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ኢየሱስ-አዳኝ! “ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ።” — ማቴዎስ 1፥21       ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

📖በእግዚአብሔር ወይስ በሰው እንታመን? ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ " እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በሰው የሚታመን ሥጋ ለባሹንም ክንዱ የሚያደርግ ልቡም ከእግዚአብሔር የሚመለስ ሰው ርጉም ነው። በምድረ በዳ እንዳለ ቍጥቋጦ ይሆናል፥ መልካምም በመጣ ጊዜ አያይም፤ ሰውም በሌለበት፥ ጨው ባለበት ምድር በምድረ በዳ በደርቅ ስፍራ ይቀመጣል። በእግዚአብሔር የታመነ እምነቱም እግዚአብሔር የሆነ ሰው ቡሩክ ነው። በውኃ አጠገብ እንደ ተተከለ፥ በወንዝም ዳር ሥሩን እንደሚዘረጋ ሙቀትም ሲመጣ እንደማይፈራ ቅጠሉም እንደሚለመልም፥ በድርቅ ዓመትም እንደማይሠጋ ፍሬውንም እንደማያቋርጥ ዛፍ ይሆናል። " - ኤር17፥5-8                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ለፍቅር ያሰብኩት የቸርች ሰው ጎዳኝ 》ሰላም ቤተሰቦቼ ዛሬ ይዤ የመጣሁት ርዕስ ከብዙ ክርስቲያን እህቶች እና ወንድሞች በተደጋጋሚ የሚደርሰኝ ጥያቄ ነው። ትንሽ ለማመን ቢከብድም ብዙ ክርስቲያን ወጣቶች ልባቸው የሚጎዳው አብሯቸው ከሚያመልኩ ወጣት አቻቸው ጋር ሊጀምሩ ባሰቡት የፍቅር ግንኙነት ነው። የፍቅር ጥያቄ አቅርበው እምቢ የሚባሉ እንዳሉ ሆነው እሺ ተብለው የፍቅር ግንኙነት የጀመሩ ወጣቶች በጣም በሚገርም ሁኔታ በማማረር እና በከባድ ፈተና ያሳልፋሉ።[ሁሉም ባይሆኑ አብዛኛዎቹ ማለት ነው] 》አንድ አመት ሙሉ እጮኛሽ ነኝ ብሎ አብሯት ቆይቶ ስለ ሰርግ እና አንዳንድ ነገሮች ማውራት እና ማቀድ ከጀመሩ በኋላ ግንገት በነጋታው "ግንኙነታችን እዚህ ጋር ይብቃ" ብሎ ጥሏት የሚሄድ ሰው ቸርች ውስጥ አለ።[ሁሉም እንዲህ አይነት ባህርይ አላቸው እያልኩ አይደለም።] 》ሌላው በጣም ያስተዋልኩት ነገር ከየቸርቹ[ሙሉወንጌል፣ቃለህይወት፣ህይወት ብርሀን፣መሰረተክርስቶስ. . .] አንዳንድ ወንድ ይዛ/ይዞ ፍቅረኛዬ ነው የሚል ሰው ቸርች ውስጥ አለ።[ይታያችሁ ይህ ሰው የአንድነት ፕሮግራም ሊያዘጋጅ ነው ወይስ ትዳር ሊመሰርት?] 》ምን እያልኩ እንደሆነ በዚህ ምክንያት የተጎዳችሁ በደንብ ይገባችኋል ብዬ አስባለሁ። እና በቸርች ልጅ ተጎዳችሁ ማለት ሁሉም የቸርች ልጅ እንደዛ መጥፎ ይሆናል ማለት አይደለም።  ስለዚህ ለምን ከዚህ ሁሉ አንደኛዬን ክርስቲያን ካልሆነ ሰው ጋር ግንኙነት አልጀምርም እነሱ እንደሆኑ እንክብካቤውን እና ማፍቀሩን ተክነውበታል የሚል አቋም ላይ ከመድረሳችሁ በፊት ማድረግ ያለባችሁን ነገር ልነግራችሁ እወዳለሁ። 1. ትክክል አይደለም በሉ 》በምታመልኩበት ቸርች ውስጥ የተጎዳችሁ እናንተ ብቻ አይደላችሁም ልክ እንደ እናንተ በተመሳሳይ ሁኔታ ብሎም በተመሳሳይ ሰው የሚጎዱ እንደሚኖሩ አትርሱ። ስለዚህ ዝም ማለቱ አማራጭ ስለማይሆን ስለጉዳዩ በደንብ ብትጮኹ መልካም ነው ወይም ለምታምኑት ወጣት መሪዎች በዚህ ጉዳይ ግንዛቤ እንዲሰጡ፣ ሆን ብለው ከግንኙነት ወደ ግንኙነት የሚዘሉ ወጣቶችን ቸርች እንድታስጠነቅቅ እና ይዛ እንድትመክራቸው አሳውቁ። [ይህ ሀሳቤ ይቀልዳል እንዴ ሊያስብል ይችላል። ግን እመኑኝ ሞክሩት አውቃለው አንዳንድ ቦታ ወጣት መሪዎች ናቸው ጎጂዎቹ።] 2. ምሬታችሁን ለጌታ አሳውቁ 》መፅሐፍ ቅዱስ ላይ እስራኤላውያን በግብፅ በባርነት በቆዩበት ጊዜ እግዚአብሔር ሙሴን የላከላቸው እንዴት ይመስላችኋል? በምሬት ወደ እግዚአብሔር መጮኸ ሲጀምሩ ነው። እግዚአብሔር ለሙሴ በቁጥቋጦው ውስጥ ተገልጦ "የህዝቤን ጩኸት ሰምቻለው" ነበር ያለው። ስለዚህ ተጎድታችሁ ዝም ማለቱ ተገቢ አይደለምና ምሬታችሁን ለእግዚአብሔር አሰሙ።[እንደሰው ስላልሆነ ባልጠበቃችሁት መንገድ ያክማችኋል።] 》ደግሞ ሰይጣን በበቀል እንድትነሱ እና ሰው እንድትጎዱ ሊያሳስባችሁ ይችላል። ይህን ጊዜ በቀል የእናንተ ሳይሆን የእግዚአብሔር እንደሆነ አውቃችሁ ለእርሱ አሳልፋችሁ መስጠት መልካም ነው። 3. ብቁ ማንነት አትጠብቁ 》ቀጥሎ ወደ ህይወታችሁ የሚመጣው ሰው መልዐክ እንዲሆን አትጠብቁ። ሰው ነው እና አንዳንድ ጉድለቶች ይኖሩታል። አንዳንዴ ታዲያ ይህን ጉድለቱን ስታዪ ሊጎዳኝ ነው የመጣው እያልሽ መጥፎ ሀሳብ ወደ ውስጥሽ ካስተናገድሽ በጣም ልትጎጂ ትችያለሽ። ስለዚህ በጎ በሆነ አመለካከት ራሳችሁን አስታጥቁ።                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

| #ከእንቅልፋችን_እንንቃ | " ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።" (ሮሜ  13:11 )  》ከእንቅልፍ እንንቃ ሲባል ባጭሩ እንቅልፍ አራት ደረጃዎች እንዳሉት ሳይንሳዊ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ እነዚህን ደረጃዎች ከመንፈሳዊ እንቅልፍ አንጻር በማየት የኛን ሁኔታ ስንመለከት:-                                            ደረጃ_1: አይን መጨፈን የሚጀመርበት 》ንቁ ሆነን ስናከናውናቸው የነበሩ ነገሮችን ማከናወን የምናቆምበት ወቅት ነው፡፡ ይህ ጊዜ በቀላሉ ለመንቃት የሚቻልበት ደረጃ የመሆኑን ያህል በፍጥነት ወደ ቀጣዩ እንቅልፍ ደረጃ የሚታለፍበት በመሆኑ ብዙ በዚህ ደረጃ የመቆየት እድል የለውም፡፡ ይህን ከመንፈሳዊ እንቅልፍ አንጻር ስናየው በዚህ ደረጃ ላይ የሚገኝ አማኝ ቀደም ሲል  በንቃት የሚጸልየውን ጸሎት  በፍቅር ለእግዚአብሄር የሚያቀርበውን አምልኮ እንዲሁም በመሰጠት ያነበው የነበረውን የእግዚአብሄር ቃል  ለማንበብ ሃይል የሚያጣበት እና በሃጢያት ላይ ማመቻመች የሚጀምርበት ደረጃ ነው፡፡ የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?( ገላ.3፡1 )   ደረጃ_2: ቀላል እንቅልፍ 》 በዚህ ደረጃ አይንን ከመጨፈን ባለፈ ወደ ቀላል እንቅልፍ የሚገባበት ደረጃ ሲሆን በዚህም የልብ ምት እና ሰውነት ሙቀት የሚቀንስበት ወቅት ሲሆን በዚህም ሰውነታችን ወደ ጥልቅ እንቅልፍ ለመግባት ዝግጅት የሚያደርግበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ የመንፈሳዊ የእንቅልፍ ደረጃ ላይ ልባችን ለክርስቶስ የነበረውን መቃጠል (ፍቅር) የሚያጣበት እና ያለን መንፈሳዊ መነቃቃት የሚቀዘቅዝበት ደረጃ ነው፡፡ …የምነቅፍብህ ነገር አለኝ የቀደመውን ፍቅርህን ትተሃልና። እንግዲህ ከወዴት እንደ ወደቅህ አስብ ንስሐም ግባ የቀደመውንም ሥራህን አድርግ፡፡ (ራእ.2፡4-5)                                                   ደረጃ_3_እና_4: ከባድ እንቅልፍ 》 በዚህ ወቅት ሰውነታችን ጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ የሚገባበት በመሆኑ በዙሪችን እየተከናወኑ ያሉ ነገሮችን ማስተዋል አንችልም፡፡ ንቁ በሆንበት ጊዜ የሚታዘዙን ጡንቻዎቻችን ፓራላይዝድ የሚሆኑበት የእንቅልፍ ደረጃ ነው፡፡ በዚህ የመንፈሳዊ የእንቅልፍ ደረጃ ላይ ከመንፈሳዊ አለም ያለን ቁርኝት የሚቋረጥበት እና ለመንፈሳዊ ነገር ባዳ የምንሆንበት ይልቁንም ስንጸየፋቸው የነበሩ አለማዊ ልምምዶች  ምንም እንዳለሆኑ ተቆጥረው በቤተ ክርስቲያን ስፍራ የሚይዙበት ፣ ከአለም ጋር መዳቀልና መቀላቀል የተለመደ የሚሆንበት ደረጃ ነው፡፡ ወገኞች ሆይ በየትኛውም የመንፈሳዊ የእንቅልፍ ደረጃ  ላይ እንገኝ ያው እንቅልፍ ላይ በመሆናችን እንንቃ እንመለስ! ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ (ሮሜ.13፡11)                 ✍ አገልጋይ Alex መልካም ምሽት!                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ትዕዛዝ ቢጤ ለወንድሞች 》ከፍቅር አጋርህ ጋር ያለህ ቅርርብ መልካም እንዲሆን እነዚህን የፍቅር ዘዴ ለአጋርክ አሳይ!! 1: እንድትለወጥ በምትነግራት ጊዜ ሁሉ የምትጠቀምባቸውን ቃላት ለስለስና ይቅር ባይነት የሞላባቸው መሆናቸውን አረጋግጥ:: °°° እጮኛህ ቁጣ በተሞላባቸው ቃላት ከጮህክባት አትለወጥም:: "እጮኛዬ አይወደኝም::" በማለት ራሷን ታሳምናለች:: እንዴት ልትለወጥ እንደምትችልና የተሻለች የፍቅር አጋር እንደምትሆን ልታስብ አትፈልግም:: በዛ ፈንታ ታለቅሳለች ወይም መልሳ ትጮህብሀለች:: 》ቃሎችህ ለስለስና ይቅር ባይነት የሞላባቸው ከሆኑ ግን ፍቅርህ ይሰማታልና ለመለወጥ ዝግጁ ትሆናለች:: " የለዘበች መልስ ቍጣን ትመልሳለች    ሸካራ ቃል ግን ቍጣን ታስነሣለች። " (መጽሐፈ ምሳሌ 15:1) 2: ለመናገር ቁጣህ እስኪበርድ ጠብቅ:: ለምሳሌ የሆነ ነገር ተነጋግራቹ በተባባላቹበት ጊዜ አላከናወነችውም እንበል:: ወዲያው ስለሁኔታው እንደሰማክ አትናገራት:: እንዴት መለወጥ እንዳለባት ልትነግራት ይህ ጥሩ ጊዜ አይደለም:: ቁጣህ እስኪበርድ ድረስ ጠብቅ ተቆጥተህ እያለህ ብትናገር ቃሎችህ ለስላሳና ይቅርታን የተሞሉ ሊሆኑ አይችሉም:: 3: በምትናገርበት ጊዜ "አንቺ" እንዲህ አደረግሽ ወዘተ... ከማለት "ይሰማኛል" በል:: 》ቀጥሎ በዚህ መንገድ እንዴት እንደምትናገር የሚያሳይ ምሳሌዎች ተጠቀም:: 》 "በተቀጣጠርንበት ቦታ በጊዜ አትገኚም(ትቀርያለሽ) ምክንያቱም ትዝ አልልሽም::" ከማለት ይልቅ በመጀመርያ አንተ ራስህ ቀጠሮ አክባሪ ሁን ከዛ  " በተቀጣጠርንበት ቦታ በጊዜ ስትገኚ ለእኔ ያለሽ ፍቅር እና ክብር ትልቅ እንደሆነ ይሰማኛል::" ብትል መልካም ነው:: 》 "እኔን ስታናግሪ ትህትና የለሽም ምክንያቱም አስተዳደግሽ ልክ ያልሆነ ጋጠወጥ እና ባለጌ ነሽ:: "አትበል ይህ ነቀፋ ነው:: ይህ ይጎዳታል እንጂ እንድትለወጥ አያደርጋትም:: በዚህ ምትክ  " ረጋ ብለሽ ስታወሪኝ እና ነገሮችን ሰከን ባለ መንገድ ስታስረጂኝ እጅግ እንደምታፈቅሪኝ እና ለእኔ ያለሽን መልካም ስሜት የሚያሳይ ይመስለኛል::" ብትል እጅግ የተሻለ ነው::            ጌታ ዘመናቹን ይባርክ!!!            ፍቅራቹ ያለገደብ ይባረክ!!                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ድንግልናዬን መጠበቅ ያለብኝ ለምንድን ነው? ••• ከፅሑፉ በፊት እስቲ የአንዳንድ ሰው የግል አመለካከት ምን እንደሚመስል እንመልከት። “ከየአቅጣጫው የሚመጣው ተጽዕኖ ‘የፆታ ግንኙነት ምን እንደሚመስል ሞክሬ ባየው’ ብዬ እንዳስብ ያደርገኛል።”​—ኬሊ “የፆታ ግንኙነት ሳልፈጽም እስካሁን መቆየቴ ያሳፍረኛል።”​—ጆርደን “ዘንድሮም ድንግል ነሽ?” ••• እንዲህ ያለው ጥያቄ ሽምቅቅ እንድትዪ ያደርግሽ ይሆናል። በብዙ ቦታዎች አንዲት ወጣት ድንግል ከሆነች ችግር እንዳለባት ተደርጋ ትታያለች። ከዚህ አንጻር በርካታ ወጣቶች ገና በአሥራዎቹ ዕድሜ ውስጥ እያሉ የፆታ ግንኙነት እየፈፀሙ ነው። ፍላጎታችሁና እኩዮቻችሁ የሚያሳድሩባችሁ ተጽዕኖ ••• ክርስቲያን ከሆንሽ መጽሐፍ ቅዱስ ‘ከዝሙት እንድትርቂ’ የሚሰጠውን ማሳሰቢያ ታውቂያለሽ።        [ 1 ተሰሎንቄ 4:3 ] ••• ያም ሆኖ የፆታ ስሜትሽን መቆጣጠር አስቸጋሪ ሊሆንብሽ ይችላል። ••• አንድ ወጣት እንዲህ ሲል በግልጽ ተናግሯል፦ “አንዳንድ ጊዜ ከፆታ ግንኙነት ጋር የተያያዙ ሐሳቦች ያለ ምንም ምክንያት ወይም ሳልፈልግ ወደ አእምሮዬ ይመጣሉ።” አብዛኛውን ጊዜ እንዲህ ያለው ስሜት በተፈጥሮ ያለ ነገር ነው። ••• ይሁንና ድንግል በመሆንሽ ጓደኞችሽ ነጋ ጠባ የሚያሾፉብሽና የሚነዘንዙሽ ከሆነ ሁኔታው ከባድ ነው። ለምሳሌ፣ √ አንድን ወጣት እኩዮቹ ‘የፆታ ግንኙነት የማትፈጽም ከሆነማ ወንድ ነኝ አትበል’ የሚሉት ቢሆንስ? √  አሊያም ደግሞ አንዲትን ወጣት ጓደኞቿ ‘የፆታ ግንኙነት ካልፈጸምሽ ምኑን ሴት ሆንሽው’ ቢሏትስ? ••• ሔርመን እንዲህ ብላለች፦ “እኩዮቻችሁ የፆታ ግንኙነት መፈጸም የሚያስደስትና ሁሉም ሰው የሚያደርገው ነገር እንደሆነ ይናገራሉ። ከዚህም ከዚያም ጋር ካልተኛችሁ ከሰው የተለያችሁ እንደሆናችሁ አድርገው ይቆጥሯችኋል።” ••• ይሁንና ከጋብቻ በፊት የፆታ ግንኙነት ከመፈጸም ጋር በተያያዘ እኩዮችሽ የሚደብቁሽ ነገር አለ። ለምሳሌ ያህል፣ ••• ከወንድ ጓደኛዋ ጋር የፆታ ግንኙነት የፈጸመች ማሪያ የተባለች አንዲት ወጣት እንዲህ በማለት ታስታውሳለች፦ “ድርጊቱን ከፈጸምኩ በኋላ በኀፍረትና በጥፋተኝነት ስሜት ተዋጥኩ። ራሴን ጠላሁት፤ የወንድ ጓደኛዬንም ጨርሶ ላየው አልፈለግኩም።” ••• አብዛኞቹ ወጣቶች ባያውቁትም እንዲህ ዓይነቱ ሁኔታ ብዙ ጊዜ የሚያጋጥም ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ ከጋብቻ በፊት የፆታ ግንኙነት መፈጸም ብዙውን ጊዜ የስሜት ሥቃይ የሚያስከትል ከመሆኑም ሌላ አስከፊ መዘዞች አሉት! ይቀጥላል. . .                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ጥቂት ሰው እንፈልጋለን! ••• በተዘጋጀ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ሀሳብ መስጠት እና በማህበራዊ ሚዲያ አገልግሎት የመሳተፍ ፍላጎት ያላችሁ በውስጥ መስመር @inbox_sozo ላይ አሳውቁን። [ፕሮግራሙ የቪዲዮ ቀረፃ ስለሚኖረው ለጊዜው አ.አ ለሆናችሁ ቅድሚያ እንሰጣለን።]                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ምን አይነት ወንድ ለመሆን ታስባለክ?               》እግዚአብሔር ለአብርሀምም የወደፊት ህይወቱን በተለያየ መንገድ ሲገልፅለትና ሲያሳየው ነበር:: ከምንም በላይ አብርሀም ሁሉን ነገር ትቶ እግዚአብሔር ወደተናገረው ስፍራ ጨርቄን ማቄን ሳይል ወቷል:: 》እግዚአብሔር በህይወትህ ይሆናል የሚልክ ነገር ልክ እንደ አብርሀም ቢዘገይብህ ምን አይነት አባት የምትሆን ይመስልሀል? 》አብርሀም ከአምላኩ ጋር እለት እለት ይነጋገር እና ይፀልይ ነበር:: በዚህ ፀሎት ስፍራው ከእግዚአብሔር ጋር የማይቋረጥ ህብረት ያደርግ ነበር:: ከእግዚአብሔር ብዙ ትዕዛዝ ተቀብሏል:: እግዚአብሔር የሚስቱን ስም የአብርሀምን ስም ቀይሯል በአጠቃላይ ቤተሰቡን ከመሀንነት እና ፍሬ ከሌለው ማንነት አንስቶ ለብዙዎች አባትና ፍሬያማ አድርጓቸዋል:: ወደፊት ምን አይነት አባት መሆን ትፈልጋለህ? 》ይስሀቅም እንደ አባቱ አብርሀም የፀሎት ህይወት ነበረው:: እለት እለት ከእግዜአብሔር ትዕዛዝን ይቀበል ነበር::በዛ የፀሎት ስፍራ አምላክ ይስሀቅን እና ቤተሰቡን ጎብኝቷል:: 》ይስሀቅ ታጋሽ ነበር:: ልጅ ለመውለድ ዘግይታ ለነበረችው ሚስቱ ከምንም በላይ ክብርና ትልቅ ፍቅር ነበረው:: አንዳች መጥፎ ነገር አልተናገራትም:: ከሌላ ሰው እንድትወልድ አልመከራትም:: አላንቋሸሻትም:: አልፈታትም:: ወደ ሌላ ሴት አልሔደም:: ነገር ግን በእግዜአብሔር ቃል ላይ ታምኖ በፅናት ይጠብቅ ነበር:: እግዜአብሔር የሰጣችሁ ተስፋ ሲዘገይ ምን ታደርጋላችሁ? 》ይስሀቅ አብዝቶ ወደ እግዜአብሔር ይቀርብ ነበር::                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ድንግል አላገባም 》ይህ አባባል አሁን አሁን ብዙ አሳሳቢ እየሆነ የመጣ እና ሰይጣን ብዙዎችን ሊያስት የሚጠቀምበት ዘዴ ሆኗል። ለዚህም በብዙዎች ዘንድ ምክንያት የሚሆኑ ነገሮችን አስቀምጧል። ከምክንያቶቹም መሀል ● ለወንዶች "ድንግል የሆነች ሴት ስለ ሩጋቤ-ስጋ ምንም እውቀት ስለማይኖራት ስትጋቡ በጣም ትቸገራላቹ" ● ለሴቶች ደግሞ "እስካሁን ድንግል ነሽ? ምን ነክቶሽ ነው ወደፊት ከምታገቢው ሰው ጋር የመጀመርያ ምሽትሽ በስቃይ የተሞላ እንዲሆን ትፈልጊያለሽ?በይ ተሸክመሽ ከምትዞሪ ቶሎ አስወግጂው።" °°°እነዚህን እና ሌሎችን እዚህ ግባ የማይባሉ ምክንያቶችን ያቀርባል። 》በጣም ማስተዋል ያለብን እነዚህን ሀሳቦች ራሱ ሰይጣን አካል ለብሶ አይናገራችሁም። ይህን ሀሳቡን አውቀው ይሁን ሳያውቁ በተለያየ መንገድ የሚያራምዱ ሰዎች አሉ። ስለዚህ ከእንደነዚህ አይነት ሰዎች ራሳችንን መጠበቁ እጅግ መልካም ነው። እስከ ጫጉላ ጊዜ ድረስ ንፅህናችንን ጠብቀን ራሳችንን ለትክክለኛው ሰው እንጠብቅ። አስተውሉ ድንግልና ብዙዎች እንደሚሉት የማያስፈልግ ነገር ቢሆን አምላክ ባልፈጠረው ነበር። ይልቁን ትልቅ ሚስጢር ያለው ነው። 》መፅሐፍ ቅዱስ ቤተክርስቲያንን እንደ ንፅህት ክብሯን ጠብቃ ባሏን እንደምትጠባበቅ ሴት ይመስላል። እንደዚህ አይነት ክብራችሁን እንድትጥሉ ከሚያደርጓችሁ አይነት ሰዎች ፈፅሞ ራቁ። እስካሁን ይህን ውሸት ሰብኳችሁ ከሆነ ሁለተኛ እድል አትስጧቸው። □ አትሳቱ! ለሁሉም ጊዜ አለው። ••• በዙሪያችሁ ያሉ ጓደኞቻችሁ ይህን ተግባር(sex) ከማውራት አልፎ በየቀኑ ሊፈፅሙት ይችላሉ ያ ማለት እያደረጉ ያሉት ነገር ልክ ነው ማለት አይደለም። በእነሱ ደግሞ ትቀናላችሁ ብዬ አላስብም። እውነት ለመናገር በተለያዩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከቤተሰቦቻቸው ተለይተው የሄዱ ወጣት ሴትና ወንዶች ይህን በማድረግ ተወጥረው ይሆናል ግን ማስተዋል ያለባችሁ በወጥመዳቸው መያዝ እንደሌለባችሁ ነው። ከምንም በላይ አላማችንን መዘንጋት የለብንም። በወደቀ ሞራል ተመርቆ መውጣት ቀሪውን ህይወታችንን ጭምር በተጨማለቀ ህይወት ያደርገናልና ተጠንቅቀን እንጓዝ። 》ብዙ ጊዜ ወድቀን ሊሆን ይችላል ማወቅ ያለብን ግን መነሳት እንዳለ ነው። ስጋ ለባሾች ነን በአንድም በሌላም የተሳሳተ ውሳኔ ወስነን ይሆናል ነገር ግን በስህተታችን ጎዳና ጉዟችንን መቀጠል የለብንም። ፃዲቅ ሰባቴ ቢወድቅ ሰባቴ ይነሳልና በሀጢያታችን ምክንያት ከቤቱ ከመራቅ ይልቅ በንስሀ ወደ እግሩ ስር መመለሱ እጅግ የብልህ ሰው ውሳኔ ነውና ጌታ ይርዳን!!                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

እኔና የቅርብ ጓደኛዬ ተመሳሳይ ወንድ አፈቀርን ● በቅርቡ በመማሪያ ክፍላችን ውስጥ አንድ ቆንጂዬ ወንድ አስተዋልኩ:: በጣም እወደዋለሁ ግን በጣም የምቀርባት ጓደኛዬም ትወደዋለች:: ልጁ ደግሞ እሷን እንደወደዳት ያስታውቃል:: ብዙ ጊዜ በመንገዳቸው ላልገባና ላልበጠብጣቸው እወስንና ብዙም ሳይቆይ ስሜቴን ማድመጥ እጀምራለሁ:: ይህን ስሜቴን እከተልና ብዙ መጥፎ ነገር ለማድረግ እና ለማበላሸት ማቀድ እጀምራለሁ:: ይህን ሰው ማፍቀር እንዴት ላቁም??? መልስ:- 》የሮማንቲክን ፍቅር ከባድ የሚያደርገው ስሜቱን እንዲህ ነው ብሎ በቃላት መግለፅ ስለማይቻል ነው:: በዚህም ምክንያት ነው ያፈቀርነውን ሰው ዝም ብሎ ማሰቡ እና ማሰላሰሉ የሚቀለን:: የመጀመርያ ፍቅር ሲሆን በተለይ ትክክለኛውን መንገድ እንዳናስተውል አይናችን ይጋረድብናል:: ለዚህ ወንድም ያለሽ ፍቅር ውስጥሽን ተቆጣጥሮ መልካሙን እና ክፉውን ነገር ሳታስተወይ ቀጥታ የትኛውንም አይነት መስዋትነት ከፍለሽ እሱ የራስሽ እንድታደርጊ የሚያሳስብሽ:: ከዚህ በፊት በመንገዳቸው ላለመግባት ወስነሽ ነገር ግን ስሜትሽ ይህን እንዳታደርጊ ያገደሽም ለዚህ ነው:: 》እኔ የምመክርሽ የሴት ጓደኛሽ ከምንም በላይ ትልቁ ስጦታሽ ናት ብዬ አምናለሁ:: የመጀመርያውን አቋምሽን አጠናክረሽ ብትቀጥይ መልካም ነው:: ይህን ማድረጉ ትንሽ ሊከብድሽና ስሜትሽን ሊጎዳው ይችላል:: እውነት ለመናገር እሱን እንድትጠይ የሚያደርግ ቀመር ኖሮኝ ብሰጥሽ ደስታዬ ነበር ነገር ግን የለም:: አሁን ላይ ይህን አምኖ መቀበሉ እንደሚከብድሽ አውቃለሁ:: ነገር ግን ይህን ስሜትሽን የምታሸንፊበት ጊዜ እሩቅ አይደለም:: ለሳምንታት ወይም ለወራት ሊከብድሽ ይችላል ግን ሁሉንም ነገር መስመር መያዙ አይቀርም:: ከምንም በላይ ግን አምላክ እንዲያበረታሽ ፀልይ። ጌታ ዘመንሽን ይባርክ!!!                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ለጌታ ምናችሁን ታወልቃላችሁ? በዛሬው ቆይታችን እግዚአብሔር ስለ ቅድስና መጀመርያ ያወራበትን ክፍል አንስተን በጣም አጭር ደቂቃ አብረን እናሳልፋለን። ዘጸአት ምዕራፍ 3 ላይ ሙሴ የእሳት ነበልባል ውስጥ ቁጥቋጦ ሳይቃጠል በማየቱ ወደ ኮሬብ ተራራ ወጥቶ ከእግዚአብሔር መልአክ ጋር ሲገናኝ እና ወደ ግብፅ እንዲሄድ እስራኤላዊያንን ነፃ እንዲያወጣ ምሪት ሲቀበል ያሳየናል።[ሙሉ ክፍሉን አንብቡትማ] ለዛሬ ግን ቁጥር 5 ልቤን ሳበው። እንዲህ ያላል። ". . . አንተ የቆምህባት ስፍራ የተቀደሰች መሬት ናትና ጫማህን ከእግርህ አውጣ አለው።" ••• እግዚአብሔር ቅዱስ ነው። ለዚህ ነው እኛም ከእርሱ ጋር ህብረት አለን የምንል መቀደስ ያለብን። ዛሬ ላይ እግዚአብሔር እኛን እኔ ያለሁበት ስፍራ ቅዱስ ነውና ብሎ  ልክ እንደ ሙሴ የእግራችሁን ጫማ አውልቁ ይላል ብዬ አላስብም።[ምናልባት ሊልም ይችላል] ግን ከጫማ ይልቅ የአሁን ዘመን ክርስቲያኖች እኛ አውልቀን መጣል ያለብን ብዙ ነገር አለ። እመኑኝ እኛ የአዲስ ኪዳን ትውልዶች ከሙሴ በበለጠ ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት እንድናደርግ በክርስቶስ ሞት በኩል ታላቅ እድል ያገኘን ነን። በብሉይ ኪዳን ቅዱሳን ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሲሔዱ ማድረግ ያለባቸው ነገሮች። ራሳቸውን ቢያረከሱ ማድረግ አለባቸው ብሎ እግዚ አብሔር የሰጣቸው ህግ አለ።[ስለሱ ሌላ ጊዜ እናወራለን] °°° ዛሬ ግን እኛ ራሳችን የመንፈሱ ማደሪያ የሆንን ከስላሴ ጋር ህብረት አለን የምንል ራሳችንን በብዙ ቀድሰን መንቀሳቀስ ያለብን ዘመን። ፠ እግዚአብሔር ለሙሴ የእግርህን ጫማ አውልቅ አለው። እኛን ፊት ለፊት ቢያወራን እግዜብሔር ምናችንን አውልቁ ሊል የሚችል ይመስላችኋል?    °°° የሀጢያት ማንነትን?    °°° ትዕቢትን?    °°° እምቢተኝነትን?    °°° ርኩሰትን?    °°° ዘረኝነትን?    °°° የልምምድ ህይወትን?     °°° አስመሳይነትን? ወይስ ሁለንተናችንን አራቁተን ከእግሩ ስር እንድንወድቅ ያዘናል? ••• ሁላችንም ብናስተውል ለጌታ ክብር ማውለቅ ያለብን እጅግ ብዙ ነገር ይኖራል። አስተውሉ! አውላቂውም አስታጣቂው ህያው መንፈስ ቅዱስ ነው። ስለዚህ ጥበባችንን ወዲያ ብለን ሁለንተናችንን ለእርሱ ሰጥተን ቡቱቷችንን እንዲያወልቅ እና ቅዱስ ማንነትን እንዲያለብሰን እድል እንስጠው።   ቅድስና ለእግዚአብሔር!!                          #ሼር                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

አባት ሴት ልጁን የመከረው ምክር የቀጠለ... 👉ወጣት ሴቶች ልጆች እንዲጠነቀቁ 👉 ወላጆች ሴቶች ልጆቻቸውን እንዲመክሩ ይረዳችኃልና ! አንብቡት • ክርስቲያን ሴቶች ሊያገቧቸው የማይገቡ  ወንዶች ሲባል :- እነዚህ ጠንካራ ምክሮች ያልተጋቡትን እንጂ  በትዳር ውስጥ ያሉትን አይመለከትም፡፡ ••• ትዳር ከተጀመረ የኃላ ማርሽ የለውም ማለት እንደገና ለማስተካከል እድሉ የለም። በክርስቶስ የገነትን ኑሮ በምድር መጀመር ሲቻል የሲኦል ኑሮ በምድር ለምን ይጀመራል ? ልዩነቱን ማሰብ ይቻላል። °°° እጮኛ ስትመርጪ በምድር ያለኝ እድሜ ሙሉ በሙሉ የምሰጠው ብለሽ ማሰብ ይኖርብሻል። ስለዚህ ጥንቃቄ ለሚፈልገው የእጮኛ አመራረጥ የሚጠቅሙሽ ጥቂት ነጥቦች እነሆ :- 1. የማያምን ሰው፡- ••• የማያምን ወንድ ያገቡ ሴቶች ፤ የሚያቀርቡት ምክንያት “በሂደት ይቀየራል” የሚል ነው፡፡ ነገር ግን እነሱን በጅ ካስገቡ በኃላ ይብስባቸዋል።  ምናልባት ለጥቂቶች ሰርቶ ይሆናል፤ እውነቱ ግን ጌታን አምኖ ያልመጣ ሴት ልጅ አይቶ አይጸናም።  ከማያምኑ ጋር ያለን ጋብቻ እግዚአብሄር እንዴት እንደሚቃወም ተመልቱ፣ “ከማያምኑ ጋር …አትጠመዱ” (2ቆሮ.6፡14)፡፡ ••• አማኝ ማግባት ያለበት የሚያምንን ብቻ ነው፡፡ °°°የሚያምን ማለት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን የግል አዳኙ አድርጎ የተቀበለና ያመነ በእምነቱም የጸናውን ነው ።   2. በእድሜ ካንቺ የሚያንስ ሰው፡- •••  እንዲህ አይነቱን ሰው ማግባት ሐጢያት ነው ባልልም፤ ሁላችንም ሚስት ለባሏ እንድትገዛ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያዝ እናውቃለን (ኤፌ.5፡22) በእድሜ ከሷ ካነሰ ብዙ ጊዜ "መገዛት" የሚለውን ትዕዛዝ ፈተና ላይ ይጥላል። እግዚአብሄር የቤተሰቡን አመራር የተሰጠ ነው። እግዚአብሄር መጀመሪያውንም የጋብቻን ተቋም ሲመሰርት፣ አዳምን በመጀመሪያ ቀጥሎ ሔዋንን በመፍጠር ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ “…በወንድ ላይ ልትሰለጥን አልፈቅድም፡፡ አዳም ቀድሞ ተፈጥሮአልና፣ በኋላም ሔዋን ተፈጠረች፡፡” (1ጢሞ.2፡11-14)  ባጠቃላይ እድሜ በጋብቻ ላይ ተፅዕኖ ያደርጋል፡፡ ስለዚህ ያላገቡ ሴቶች ከእነርሱ በእድሜ ብልጫ ያለውን ወንድ ቢያገቡ መልካም ነው፡፡ 3. በመንፈሳዊ ህይወቱ ያላደገ ሰው፡- ••• እድሜ ለጋብቻ ወሳኝ እንደሆነ ሁሉ መንፈሳዊ ብስለትም ወሳኝ ነው፡፡   ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን እንደወደዳት የሚወዳችሁን ሰው ፈልጉ፤ ቤተክርስቲያንን ክርስቶስ እንዴት እንደወደዳት ያልተረዳ ከሆነ፣ ከዚህ ሰው ጋር የምትለያዩበት ጊዜ ቅርብ እንደሆነ እወቁ፡፡ እንደገና በአንድ እወነተኛ ቤ/ክ መያዙን  እርግጠኛ ሁኑ፤ በቤተክርስቲያን ውስጥ መንፈሳዊ ተሳትፎ እነዳለው መጋቢውን ወይም የቤተክርስቲያኑን ሽማግሌ በመጠየቅ ተረዱ፡፡ ጋብቻ ትልቅ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ በመሆኑ ነገሮችን ደረጃ በደረጃ አድርጉ ፈጥናችሁ ለመውጣት አይናችሁን ጨፍናችሁ አትግቡ፡፡ 4. አግብቶ የፈታ ሰው፡- •••  ይህ ጉዳይ በመጽሀፍ ቅዱስ በቀጥታ የተገለፀ ነው፤ “ሚስቱንም የሚፈታ ሁሉ ሌላይቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፣ ከባልዋም የተፈታችውን የሚያገባ ያመነዝራል፡፡ ” (ሉቃስ 16፡18) በዝሙት ምክንያት ካልሆነ በቀር (ፍቺና) ሁለተኛ ጋብቻ በእግዚአብሄር አይን የተጠላ ነው …..፡፡ (1ቆሮ.6፡9)፡፡ 5. ተናዳጅ ሰው፡- ••• ከትዳራቸው በፊት ስሜታቸውን መቆጣጠር የማይችሉ ወንዶች በየትኛውም መንገድ ከትዳርም በኋላ ብስጩዎች ናቸው፡፡ችግር የለውም የሚያናድደውን ነገር እቀንሳለሁ ብሎ ማሰብ አደገኛ ነው። ድንገተኛ ቁጣ የተሰወረ ማንነት መገለጫ ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ ድርጊት በኋላ ላይ ለሚከሰተው የቤት ውስጥ ጥቃት አይነተኛ ማሳያ ነው፡፡ የትዳር መሰረት ፍቅር መሆኑን መርሳት አይገባም፤ (ገላ.5፡19-21) 6. እራስ ተኮር የሆነ ሰው፡- ••• ብዙ ጊዜ ሴቶች የሚፈልጉት ሊታይ የሚችል ነገር ያለው እጮኛ ማግኘት ነው፡፡ነገር ግን እራስ ተኮር የሆነ ሰው እርሱ እንጂ ለሌላ መኖር የሚባል ነገር ፈጽሞ አይገባውም።  ምክንያቱም ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን በወደደበት መጠን  አንቺን ሊወድሽ አይችልም፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ በጭራሽ አንቺን አይወድሽም፤ የሚወደው ራሱን ነው ምናልባትም የሚፈልግሽ ለጊዜያዊ ስሜት እርካተው ሊሆን ይችላል፡፡ በእኔነቱ ሁሉም ለኔ ብቻ በማለቱ ታውቂዋለሽ ፡፡ 7. የማይታመን ሰው፡- እምነት አጉዳይነት አደገኛ ነው፡፡ ትዳር የሚመሰረተው በመተማመን ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ከሆነ የተገነባው ሁሉ እንዳልነበር ነው የሚሆነው፡፡ እህቶች ከጋብቻችሁ በፊት የሚዋሻችሁ ከሆነ ፣ ከጋብቻም በኋላ የሚሆነው እንደዛው ነው፡፡ ከጋብቻ በፊት የግብረ ስጋ ግንኙነት የሚያደርግ ከሆነ፣ ከጋብቻም በኋላ በዚህ ጉዳይ ከማታለል አይመለስም፡፡ ታማኝ ሰው ለማግኘት በትጋት ፀልዩ ፡፡ 8. በተለያዩ ሱሶች የተጠመደ ሰው፡- ••• ጓደኛሸ በወሲብ ወይም በአደንዛዥ እጾች የተለከፈ እንደሆነ ከደረሽበት  ከእርሱ ጋር ጊዜሽን አታባክኚ ያለሽን ግንኙነት ወዲያውኑ አቋርጠሸ፣ ለቤተክርስቲያን መሪዎች ስላለበት ሁኔታ ተናገሪ፤ ሰውየው በዚህ ወቅት የሚያስፈልገው መንፈሳዊ እርዳታ እንጂ ሚስት አይደልም ፡፡ ኃጢያታቸውን ደብቀው ወደ ቤተክርስቲያን የሚመላለሱ ወንዶች በጣም መጥፎና ውሸታሞች አደገኞች  ናቸው፡፡ እነደዚህ ዓይነት ወንዶች በአብዛኛው በስህተት የተሞሉ ናቸው፡፡ ምንም ያህል ሊያሳምንሽ ቢሞክር እንዳትቀበይው፤ ሰውየው የሚያስፈልገው ኢየሱስ ነው እንጂ ሴት አይደልም፡፡ ከእስራቱ እስኪፈታ ድረስ ለክርስቶስ ተይለት (ዘፀአ. 20፡3)፡፡ 9. ሰነፍ ሰው፡- ስንፍና ወደፊት በሚኖራችሁ ትዳር አንቺ እየሰራሽ እንድተቀልቢውና የሆናል። የቤተሰቡን ኃላፊነት ዘላቂ ትዳር አይመሰረትም። ስራን በተመለከተ ጥልቅ የሆነ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ አለ፤ ወንድየው ቤተሰቡን መርዳት የማይችል ከሆነ ከማያምን ሰው ይልቅ የከፋ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ በግልፅ ያስቀምጣል (1ጢሞ.5፡8)፡፡  10. በሕይወቱ እግዚአብሔርንና ፈቃዱን የማያስቀደም፡- ••• ለመንፈሳዊ ሕይወቱ ግድ የለሽ ከሆነ አደገኛ ነው። አምላኩን ያላስቀደመ እኔን ያስቀድማል ብለሽ እንዳታስቢ እንዲህ አይነት ወንድ አደገኛ ነው። " አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።" (ማር 12:30) ✍ Alex ተባረኩልኝ! #ሼር                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ጠቃሚ ምክር √ የፍቅር ጓደኝነት መጀመራችሁን አገር እንዲያውቅ ማድረግ አያስፈልግም። [ ይሁንና ማወቅ ለሚገባቸው ሰዎች መናገር ይኖርባችኋል። አብዛኛውን ጊዜ የአንተም ሆኑ የእሷ ወላጆች ጉዳዩን ማወቅ ይኖርባቸዋል። ] #ሼር                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ልባችሁን ጠብቁ! 💌 ልባችሁ የአምላካችሁ ማደርያ ነውና ከክፉ ጠብቁት!! 💌 ከእግዚአብሔር ቀጥሎ ልባችሁ ውስጥ መንገስ ያለበት ትክክለኛ የፍቅር አጋራችሁ ነውና/ናትና ለትክክለኛ ሰው ልባችሁን አስቀምጡ:: መልካም ቀን!                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

አባት ሴት ልጁን የመከረው ምክር ይህ አባት ለሴት ልጁ የመከረው ምክር ነውና በማስተዋል አንብቡት ! 👉ወጣት ሴቶች ልጆች እንዲጠነቀቁ 👉 ወላጆች ሴቶች ልጆቻቸውን እንዲመክሩ ይረዳችኃልና ! ወድ ልጄ በምድር እንድትኖሪበት የተሰጠሽን ሕይወት ዳግመኛ ተመልሰሽ አትኖሪበትም ! የተፈጠርሽበትን ዓላማ ከፈጠረሽ አምላክ ጠይቂ ! በተሰጠሽ ዘመን ለፈጠረሽ አምላክ ፈቃድ ተገዢ ! ☞ሴት ልጅ ውድ ነች ርካሽ ብትሆን ለውዷ ቤተክርስቲያን በምሳሌ አትሰየም። በእግዚአብሔር ላንቺ የተመዘነው ዋጋ የክርስቶስ ደም ነው። ራስሽን ማየት ያለብሽ እግዚአብሔር በሚልሽ እንጂ ሰይጣንም፣ ሰውም፣ ሁኔታም፣ በሚገልጽሽ ማንነት አይደለም። በእግዚአብሔር እንተወደደች እንደ ውድ ዕንቁ ሴት ራስሽን ቁጠሪ ፤ ☞ እግዚአብሔር በልጁ ሞት ሕይወት የሰጠሽ የከበርሽ ልጁ ነሽ  ! ☞ እግዚአብሔር በዓላማ ፈጥሮሻል! ☞  ከእግዚአብሔር ሐሳብ ወደ ግራም ወደ ቀኝም እንዳትይ ተጠንቀቂ ! ☞ በሰይጣንና በሰው የሚሰጥሽን መደለያ ፈጽሞ አትቀበይ ወጥመድ ነውና ! ☞ ክብርሽ ስኬትሽ ደስታሽ ያለው በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ ነው ! ☞ ለገንዘብ ራሳቸውን የሸጡትን ምክር አትስሚ ! ለሁለት ጌቶች መገዛት አትችይምና ! አምላኬ ገንዘብ ሳይሆን እግዚአብሔር ነው በያቸው ! ☞ ሁል ጊዜ ነፍሱን ሰጥቶ ያዳነሽን ጌታ ፍቅር አስቢ ! ☞የእግዚአብሔርን የፀጋ ክብር በሙላት ይግባሽ፤ ☞ሰይጣን በላከው ተራ ወንድ አትሸወጂ ስላንቺ ያለው እይታ ከቤት ዕቃ አያልፍምና !  (የቤቱን እቃ አሟልቶ አሁን ደግሞ ሚስት ብሎ ከሚያቅድ ነገ እንደ ቁምሳጥን፣አንደ መኪና የቤት እቃ አድርጎ ሊቆጥርሽ ከሚችል እይታው ከጠበበ ወንድ ተጠበቂ)፤ ☞እግዚአብሔር ፀጋውንና የክርስቶስን ልብ ሰጠን እንጂ ለእባብ የሚስቅ የሄዋንን ልብ አልሰጠንምና የቀረበሽ ወንድ ሁሉ ያንቺ አይደለምና ተጠንቀቂ።☞ፍቅር የዘኝ ብሎ ለሚፈጥነውም  ረጋ በል ብሎ መመርመር ይገባል። ወዲያው አፈቀርኩ አበድኩ ነደድኩ ብሎ የሌለን አለም ታሪክ ዲስኩር ከሚቀድ ወንድ ተጠበቂ ተጠንቀቂ ውድቀትሽን ስብራትሽን ሐዘንሽ ለማፈጠን ከሰይጣን የተላከ የስሜት ፈረስ ጋላቢ ሊሆን ይችላልና። ☞አበድኩ አፈቀርኩ ብሎ ኃላ የጥላቻ ቁንጮ የሆነውን አሲድ ከሚደፋ ወንድ ጋር ህብረት አታድርጊ አሲድ ባይደፋም  በእርኩሰቱ  ወደ ሲኦል የሚመራሽ ከዚያ ይብሳልና ተጠበቂ ! ☞ከማታውቂው መልአክ የምታውቂው ሰይጣን ይሻላል አየተባለ ከሚደሰኮር   ተረት ራቂ  ለሞትና ለጥፋት የሚያዘጋጅ ነውና። ☞ ይልቅ ለፈጠረሽ አምላክ ለእግዚአብሔርን የተሰጠ እውነተኛ ወንድም ከእግዚአብሔር እጅ ለመቀበል ጸልይ ከአምላክሽ ጋር የጠበቀ ሕብረት ይኑርሽ ! በጸሎት በአምልኮ በቃል ጥናት በመንፈስ ቅዱስ ሙላትና ምሪት የተቃኘ ሕይወት ይኑርሽ ! ☞ የተፈጠርሽበትን ዓላማ ለማሳካት ጌታን በሚያስከብር ሕይወት የአገልግሎት ጸጋሽን በመለየት አገልግይ! ☞ የሚገርመው ጌታ በውስጥሽ ያስቀመጠው የሚገርም የተዳፈነ ፀጋ አለሽ በጸሎት በቃሉና በመንፈሱ ሙላት ይገለጣልና ቀድሞ ከነበረሽ ይልቅ በጌታ ፊት ወድቆ የመጮህ ጊዜ ይብዛልሽ !  ☞ጸጋው በተገለጠ ጊዜም ለሰጪው ክብር በማብዛት በስርዓት ወደ መድረክ ይዘሽው ውጪ ለብዙዎች መዳን ምክንያት ትሆኛለሽና ! ☞በትንቢት ቃል አትታሰሪ/ትዳር/ አትመስርቺ ለነብይ የነገረው አባትሽ እግዚአብሔር ከሆነ ላንቺ በቀጥታ ይነግርሻል ልጁ ነሽና እንደ ነጎድጓድ የሚነገር ልሳን አትፍሪ አትደንግጪ ! ☞አንቺ ልባም ሴት ልጅ ነሽ የክርስቶስ ልብ ያለሸ፤ ☞አንቺ ከመውለድ ልጅ ከማሳደግ ንብረት ከመሰብሰብ ያለፈ መለኮታዊ ፕሮግራም ያለብሽ በደሙ የተገዛሽ ዕንቁ ልጁ ነሽ ! ☞ የአምላክሽ ዋና ዓላማና ግብ ማግባት ብቻ አይደለም ለዘላለም ሕይወት ክብር በክርስቶስ መመረጥሽ እንጂ ! በምድር ከሚሆንልሽ እና ከሚደረግልሽ ያለፈ ክብር አለሽ ! ☞ የሰርጉ ሆታ ጭፈራ እልልታና ሽብሸባ የአንድ ቀን ነው። በክርስቶስ የተዘጋጀው ክብር ግን የዘለዓለም ነው ! ☞  በአምላክሽ የታሰበልሽን ግብና የተሰጠሽን ተስፋ አስቢ ! ☞በጊዜው የሚመጣ ክብርሽ የሚሆንልሽ የትዳር አጋር ዘውድ የምትሆኚለት ወንድ በእግዚአብሔር እንደተወሰነልሽ አስቢ፤ ☞☞☞ይህ ከሆነ በእውነት ልባሟ ሴት አንቺ ነሽ ! ተባረኩልኝ። ✍Alex                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

የዝሙት ጀብዱ ••• ዝሙት በግዕዝ በአማርኛ በዕብሩም በአርመንም ያው ያየኃት ሴት ሁሉ የኔ ትሁን ማለት ነው። ••• በአንድ ሚስቱ ያልተደሰተ ሺህ ሚስትም ቢመጣ አይደሰትም። ዝሙት በማድረግ የተደሰተ ክርስቲያን በርክቷል። ••• ወዳጄ የተፈጥሮ ፆታዊ ስሜትህም ማጥፋት አትችልም። ይህ ስሜት ሲንርባቸው የገዛ እፍረተ ስጋቸውን ቆርጠው ለማጥፋት የሞከሩ ሰዎችንም አስታውሳለው። ዝሙት በሽታ ነው [ መሸሽ ደግሞ መድሀኒቱ ነው። ] ••• የዝሙት መንፈስ ይነቀል እየተባለ ይገሰፃል መልካም ግን አየሩን ከመገሰፅ ፍቃድን መገሰፅ ይሻላል። ••• አንዳንድ መንፈሶች በኢየሱስ ስም ብቻ አይገሰፁም። ለምሳሌ √ አንዲት ሴት አንተን በዝሙት ለማጥመድ እንዳወቀች ካሰብክ በኢየሱስ ስም ብለህ አትገስፃት ሚስቴ እኮ ፍቅረኛዬ እኮ ብለህ ስትጀምር ያኔ ተመናቅራ ትጠፋለች። ••• ደሞ ከሰማኸኝ ልንገርህ ቃል ከዝሙት ሽሽ እያለ ከአንዲት ልጅ ጋር ለፀሎት ብለህ ባዶ ቤት የምትገባ ዋ ዋ ዋ  ይልቅ ፈርጥጥ!!                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ድብርት [ Boredom ] እንደ ክርስቲያን ብዙ የማይወራበት እንዲሁም ብዙዎቻችን እጅግ ከመላመዳችን የተነሳ ችግር መስሎ የማይታየን ነገር ድብርት ነው። ••• ድብርት በብዙ ክርስቲያኖች ዘንድ የተለያየ ስም ተሰቶት ከችግርነት አልፎ በጭንቀት ውስጥ የመዝናናት አለም ፈጥሮ ከጌታ እቅፍ ትውልድን ብዙ እያራቀ ያለ ነገር ሆኗል። ••• ብቻችን መሆን የድብርት ዋና መገለጫ ባይሆንም ነገር ግን ብዙዎቻችን ለድብርት የምንጋለጥበት ዋነኛ ምክንያት ነው። ••• ጭንቀት፣ውጥረት በድብርት ክልል ውስጥ የሚካተቱ ባህርያት ሊሆኑ ይችላሉ። የድብርት መንስኤ 1. በሰው መጎዳት   - ይህ ለድብርት እንደ ዋና ምክንያት የሚነሳ ነው። በፍቅር ህይወቷ አንድን ወንድ አምና ንፅሁ ፍቅሯን ስትሰጥ የነበረች እህት ድንገት በአጋሯ በሚደርስባት ጉዳት "አይ ወንድ ልጅን ማመን!" የሚል አቋም ላይ ትደርሳለች።በዚህ ምክንያት ወንድ ካለማመን በተጨማሪ ወንድ ባለበት ላለመገኘት ልትወስን ትችላለች።በዚህ ምክንያት ብቻዋን መሆን ከማብዛቷ የተነሳ ልትወጣው ወደማትችልበት የጭንቀት እና የድብርት አለም ልትገባ ትችላለች።   - ብዙ ጊዜ ቀን ቀን ደስተኛ እየመሰለ የሚያስቀና አይነት ፈገግታ በዙርያው ላሉ ሰዎች እያሳየ የሚውል ወጣት ማታ ማታ የበደሉትን ሰዎች ብዛት እየቆተረ ምሽቱን ድብርት ደግሶ የሚያሳልፍ ወንድ ጥቂት የሚባል አይደለም። 2. ፀፀት   - ፀፀት የትላንት ስህተታችን ውጤት ነው።ትላንት በሞኝነት(ባለማወቅ) በወሰንናቸው ስህተቶች ዛሬን ድብርት በሚባል መርዝ እያበላሸን የምንኖር ብዙ ነን።   - ሁሌም ግን ሰው እንደሆንን እና ስህተት ሊኖርብን እንደሚችል ማሰብ መልካም ነው። እንደ ክርስቲያን ደግሞ የኋላችንን እየረሳን መጓዝ መገለጫችን እንደሆነም አንዘንጋ።   3.ሀዘን   - የሚወደውን ወዳጁን በሞት ያጣ ክርስቲያን በድብርት ሲጠቃ ይስተዋላል።ከድብርት ባለፈ ለብዙ አይነት ሱሶች የሚጋለጥም ብዙ ነው። 4.ብቸኝነት   - በአስተዳደጉ ብዙ ከሰው ጋር የመግባባት ልምድ ያላሳደገ ሰው ብቸኝነት ኖርማል መስሎት ሊሰማው ይችላል(ከሰው የማያስጠጋ እና በበታቸኝነት ስሜት የሚያስጠቃ ብቸኝነት)። ከጊዜ በኋላ ግን አከባቢያቸውን እያስተዋሉ ሲመጡ በድብርት በትር ይመታሉ። የድብርት መዘዝ - በእግዜአብሔር እምነት ማጣት - የሱስ እስረኛ ያደርጋል - ራስን መጥላት - ራስን ማጥፋት(ሞት) --> ከዚህ በተጨማሪ ብዙ ምክንያቶች ሊዘረዘሩ ይችላሉ ግን ከመንስኤው በላይ እንዴት እንደ ክርስቲያን ድብርትን እናስወግድ እና መፅሐፍ ቅዱሳችንስ ምን ይላል በሚለው ላይ እናተኩር። ••• በድብርት ሱስ እየተጠቃችሁ ከሆነ አይዟችሁ እናንተ ብቻ አይደላችሁም በዚህ ስሜት የተለከፋችሁት።መፅሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ ብዙ ቅዱሳን በብዙ ምክንያት ድብርት እና ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ተዘፍቀዋል። ከሁሉም ጭንቀት ግን የጌታ በላይ ነውና ካሉበት ነገር ተላቀው በምስጋና ቆመዋል። °°° እነዚህን ነገሮች ከድብርታችሁ ለመላቀቅ እንደ መነሻ ብትይዟችው መልካም ነው። 1. ብቻችሁን እንዳልሆናችሁ እወቁ   - የድብርት ትልቁ ክፋት ቃሉን እንዳናነብ እና እንዳንፀልይ ማድረጉ ነው።በዚህም ምክንያት ከአብ ከልጁም ከኢየስሱስ ክርስቲስ ጋር ያለንን ህብረት ማስተዋል ይሳነናል። - የእግዜብሄር ባርያ ኤርሚያስ በህይወቱ እንዲህ አይነት ሁኔታ ገጥሞት ያውቃል። "አቤቱ፥ አታለልኸኝ እኔም ተታለልሁ፥ ከእኔም በረታህ አሸነፍህም፤ ቀኑን ሁሉ መሳቂያ ሆኛለሁ፥ ሁሉም ያላግጡብኛል። በተናገርሁ ቍጥር እጮኻለሁ፤ ግፍና ጥፋት ብዬ እጮኻለሁ፤ #የእግዚአብሔር_ቃል_ቀኑን_ሁሉ_ስድብና_ዋዛ_ሆኖብኛልና።"           ትንቢተ ኤርምያስ 20፡7-8 2. የእግዜአብሔር ፍቅርና ታማኝነት በእንናንተ ሁኔታ አይወሰንም።   -ድብርት ከክርስትና ጋር የተያያዙ ነገሮችን እንድንፀየፍ ያደርጋል።በዚህም ምክንያት አንዴ ፈጣሪን በድየዋለው ስለዚህ ከነ ሀጢያቴን ፊቱ አልቀርብም በሚል አቋም ብዙዎች ከቤቱ ኮብልለናል።ግን ነገሩ ፈፅሞ ከዛ የተለየ ነው። ውዳችሁ ከየትኛውም ጊዜ በላይ አሁን ነው ሰፍፍ. . . ብሉ ደጅ ደጁን እያየ የሚጠብቃችሁ። 3.ከምንም በላይ ለመንፈስ ቅዱስ ግልፅ ሁኑ።ነገሮችን በሀይሉ እንዲለውጥ ፍቀዱለት። ሰው ሰውን ሊሸውድ ይችላል እግዜአብሔርን ግን እንዴት ይሸውዳል ስለዚህ ለውዳችሁ ግልፅ ሁኑ። "እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው፥ መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል።" መዝ 34፡18                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

ወሲባዊ_ቴክስት [Sex_Chat] ጥያቄ : እኔና እጮኛዬ እስከዛሬ በአካል ስንገናኝ እጅ ለእጅ ከመያያዝ ያለፈ ምንም ነገር ባናደርግም በቴክስት ግን በጣም ወጣ ያሉ ነገሮችን( ስለ ሴክስ ጭምር) በጣም እናወራለን::ከጋብቻ በፊት ወደምንም ነገር መግባት እንደሌለብን በግልፅ አውርተናል::ነገር ግን አንዳንዴ በቴክስት የምናወራው ነገር በእውን ያን ነገር የፈፀምኩ እስኪመስለኝ ፀፀት ውስጥ ይከተኛል:: ይህ ነገር ችግር ይኖረው ይሁን? መልስ:- ከእጮኛሽ ጋር በግልፅ ስለ ወደፊታቹ አውርታቹ በየጊዜው ስትገናኙ ራሳቹን መጠበቃቹ የሚያኮራ ተግባር ነው:: ቃላቹን ለመጠበቅ ያላቹ ቆራጥነትም አስደንቆኛል:: ነገርግን የቴክስታቹ ነገር ግራ አጋብቶኛል::እንደሚመስለኝ ራሳቹን እያሞኛቹ ነው::ሁሉንም ነገር ከጋብቻ በፊት ላለመፈፀም ወስናችሁ ነገር ግን በቴክስት እንደዛ ማውራታቹ የፍቅር ግንኙነታቹን ንፁ የሚያደርገው አይመስለኝም::ይህ ድርጊት ከሴክስ ውጪ ከጋብቻ በፊት ምንም ነገር ብናደርግ ጣጣ የለውም ከሚሉት ጎራ እንዳስቀምጣቹ አድርጎኛል ያ ደግሞ ጤናማ እና መፅሐፍ ቅዱሳዊ አይደለም:: ስለ ሴክስ አብዝታቹ ማውራታቹ በግንኙነታቹ ውስጥ ትልቁን ስፍራ ከክርስቶስ ይልቅ የምታወሩት ነገር እንዲነግስ ያደርጋል::በነገርሽኝ አይነት ፍጥነት ከቀጠላቹ ከጋብቻ በፊት አናደርግም ያላቹት ቃል ላለመፍረሱ ምንም ዋስትና የላቹም:: አዕምሯን ከየትኛውም የሰውነት ክፍል በላይ ለሴክስ sensetive ነው::ስለዚህ በሀሳባቹ አዕምሯቹን ስለዚህ ነገር ሞላቹ ማለት የበለጠ አደጋ ላይ ናቹ:: ኢየሱስ ክርስቶስ ሲያስተምር በሀሳብ የፈፀምናቸው ሀጢያቶች በተግባር ከምንፈፅመው ጋር አቻ እንደሆነ ነው:: እስቲ ይህን ክፍል በማስተዋል ተመልከቺ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 (የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 5) 27፤ አታመንዝር እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 28፤ እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ወደ ሴት ያየ ሁሉ የተመኛትም ያን ጊዜ በልቡ ከእርስዋ ጋር አመንዝሮአል። 29፤ ቀኝ ዓይንህም ብታሰናክልህ አውጥተህ ከአንተ ጣላት፤ ሙሉ ሰውነትህ በገሃነም ከሚጣል ይልቅ ከአካላትህ አንድ ቢጠፋ ይሻልሃልና። 30፤ ቀኝ እጅህም ብታሰናክልህ ቆርጠህ ከአንተ ጣላት፤ ሙሉ ሰውነትህ በገሃነም ከሚጣል ይልቅ ከአካላትህ አንድ ቢጠፋ ይሻላልና። 👉 ስለዚህ አስተውሉ!!                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

SOZO YOUTH - Статистика та аналітика Telegram каналу @sozo_youth