✞ኑ እንዘምር
ይህ ቻናል እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ በ 4/6/2012 ተከፈተ፤ በዚህ ቻናል የ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን ስርአት የጠበቁ መዝሙራት ይለቀቁበታል እኒህም አብዛኛዎቹ ከተለያዩ መንፈሳዊ ቻናሎት ተመርጠው የሚለቀቁ ናቸው። ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን 🙏
БільшеКраїна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
190
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
- Підписники
- Перегляди допису
- ER - коефіцієнт залучення
Триває завантаження даних...
Приріст підписників
Триває завантаження даних...
ታላቁ ሊቅ አባታችን
💕ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 💕
👉ስለ አለሙ መድሐኒት ሁሉበእርሱ ስለሆነዉ ያለ እርሱም አንዳች ስላልሆነዉ መድሐኒዓለም እንዲ ልዩ የሆነውን ፍቅሩን ሲያስተምረን እንዲህ ይገስጸናል
➕ፍቅር ሃያሉ 💕እግዚአብሔርን 💕እስከሞት አደረሰዉ ➕።
➕ወዮ እንዲ ያለ ፍቅር ምነኛ ድንቅ ና እጹብ ነዉ➕ ።
➕ፍቅር ን ከክርስቶስ እንማር ሲለን እንዲ ያስተምረናል➕ ።
👉<< ሁሉን የያዘውን ያዙት ፣
👉 ሁሉን የሚገዛውን አሠሩት ፣
👉የሕያውአምላክን ልጅ አሠሩት
👉በቁጣ ጎተቱት ፣
👉በፍቅር ተከተላቸው
👉በሚሸልተው ፊት እንደማይነገር እንደ የዋህ በግ በኋላቸው
እየተከተለ ወሰዱት።
👉ሊቃነ መላእክት በመፍራትና በመንቀጥቀጥ በፊት
የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት
👉 ኃጥአትን ይቅር የሚለውን
ኃጥኣተኛ አሉት ፣
👉በፈራጆች ላይ በሚፈርደው በእርሱ ላይፈረዱበት።
👉ለሱራፌል ዘውድየሚያቀዳጃቸውን የእሾክ ዘውድ አቀዳጁት።
👉ለኪሩቤል ግርማ ልብስ የሚያለብሳቸውን ቀይ ግምጃ
አለበሱት።
👉የመላእክት ሠራዊት በፍጹም መደንገጥ ለሚሰግዱለት
እየዘበቱበት በፊት ተንበረከኩ።
👉ይህን ያህል ትሕትና እንደምን ያለ ትሕትና ነው?
👉ይህን ያህል ትዕግስት እንደምን ያለ ትዕግስት ነው?
👉ይህን ያህል ዝምታ እንደምን ያለ ዝምታ ነው?
👉ይህንን ያህል ሰውን ማፍቀር እንደምን ያለ ፍቅር ነው?
👉ፍቅር የአምላክን ልጅ ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው”
የ 💚ቅዱስ ዮሐንስ አፍ ወርቅ💚
ሬድኤት በረከት አይለየን !!!
✞የሰው ልጅ ሁል ጊዜ✞
የሰው ልጅ ሁልጊዜ /በጣም ደስ ቢለው/(፪)
ደግሞ የጭንቁን ቀን ማሰብ ተገቢ ነው
ምንም ቢደሰቱ /ቢበዛ ምቾት/(፪)
አይቀርም በኃላ መወሰድ በሞት
ችግር ቢደራረብ /ሐዘን ቢከብን/(፪)
ከክርስቶስ ፍቅር ማንም አይለየንም
ሳናውቀው ዳቢሎስ /እንዳይነጣጥለን/(፪)
ነቅተን እንጠብቅ የእምነትን ሰይፍ ይዘን
የሰው ልጅ ሁልጊዜ /በጣም ደስ ቢለው/(፪)
ደግሞ የጭንቁን ቀን ማሰብ ተገቢ ነው
ሊቀ መዘምራን
ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ
፩ተሰ ፭፥፩-፲፩
የሰው ልጅ ሁል ጊዜ.mp33.62 MB
✟አትቁረጡ ተስፋ✟
አትቁረጡ ተስፋ 'የእግዚዐብሄር ልጆቹ/2/
ከእናንተ አይለዩም 'የፍቅር አይኖቹ/2/
ምድርና መላዋ ናትና የእግዚዐብሄር
በሰማያት አለ በቀላይ በባህር
በጥልቁ እንኻን ቢሆን ከእናንተ ጋራ ነው
ሞገዶች አትስጉ ሰላም የእግዚዐብሄር ነው
ጌታ አይረሣምና የእጆቹን ስራ
ይኸው በልጆቹ አይተናል ሲሰራ
አዝ______________
እንደ ጠላት ቢሆን እንደርሱ ጉልበት
ማን ነበር የሚኖር ዛሬን በህይወት
የሚያኖር ጌታ ነው የሚገልም ጌታ
ብርቱ እርሱ ብቻ ነው በምድር የበረታ
አዝ________________
በምስጋና ትኑር ፅኑ በፀሎት
በስሙ ታመኑ በፍፁም እምነት
ለእናንተ የምትሆን እግዚዐብሄር ቀን አለው
አትቁረጡ ተስፋ ሁሉም ሀላፊ ነው
አዝ________________
በትሆኑም ከጉድጓድ እሱ ያያችኻል
በማዳኑ ጥላ ይጎበኛችኅል
ገና ያበዛችኻል ከዚህም በላይ
ሁሉ ይቻለዋል ነውና አዶናይ
✟ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን✟
ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ
በመስቀል ሆነህ አባት ሆይ
ድምጽህን በማሰማት አባት ሆይ
ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ
ከዋክብተ ሰማይ በሙሉ ረገፉ
ጨረቃና ፀሐይ ደምን አጎረፉ
ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ
ሥጋህን በመስቀል ተገልጦ ስላዩ
አዝ_______________
ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ
አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ
ማርና ወተትን ለሚመግበው
ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው
አዝ__________________
አካሉ ሲወጋ ውኃ ደም ፈሰሰ
በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰ
የእሥራኤል ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ
ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ለአንተስ አላሰብክም
አዝ_________________
እናትህ ስታለቅስ በመስቃል ሥር ሆና
ዮሐንስን ሰጠህ ጠብቆ እንዲያፅናና
መላእክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ
የአይሁድ ሠራዊት ፈርተው ተረበሹ
@Menfesawimesmur
✟ቅያሜው ይቅርና✟
ቅያሜው ይቅርና አምላክ ሆይ ታረቀን
አንተ ስለራከን ሞት ነው የከበበን/2/
እስከ መቼ ድረስ ህዝብህ ተጎሳቁሎ
ለረከሰ መንፈስ ለርኩሰት ተጥሎ
ምድርህ እያለቀሰች ደም እየሸተታት
እባክህ አምላኬ ኢትዮጵያን ታረቃት
እባክህ አምላኬ ሀገሬን ታረቃት
አዝ____________________
የዘመኑ ጣኦት ገንዘብ እያሳተን
የደካማ ስጋ አምላክን አስተወን
ግብዝነት ሞልቶት ፈራሹ አካል
'በነፍስ በሽታ ህዝባችን ታሟል/2/
አዝ__________________
ክንፋችን ተመቶ መብረር አቅቶናል
በመቅሰፍት በሽታ ህዝባችን ታውኻል
ዕራይ የሌለው ተራ ሰው ስለሆንን
'እባክኽ ጌታችን በፍጥነት ታረቀን/2/
አዝ__________________
ፀጋ የተለየን ባዶነት የሞላን
ፍቅር የናፈቀን ሰላም የጎደለን
ሆነን ስለቀረን እግዚአብሄር አድለን
ፅድቅህን አድለን ፅድቅ እንደተመኘን
Оберіть інший тариф
На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.