ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
Відкрити в Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
Показати більше1 719
Підписники
Немає даних24 години
-77 днів
-1830 день
Архів дописів
Shifta presents Gitem Sitem an open mic circle of fun and poetry.
Happens on every first Wednesday of the month with your hosts Heran and Seife.
We have very simple rules:
1. Sign up online https://forms.gle/oEbMTixhnKu4HKox7 or by the gate prior to the event
2. 5 minute per performer
3. Be respectful to the performers and all beings around you
4. Be you
5. Make sure you follow all the precaution measures for Covid 19
https://www.facebook.com/gitemsitem
ሽፍታ የግጥም ሲጥምን የክፍት መድረክ ክበብ አቀረበላችሁ!
ረቡዕ, መጋቢት 29 ከ 1 ሰዓት ጀመሮ በሽፍታ
ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ የቁም ኩምክና፣ ስዕል እና ሌሎችም አዝናኝ የጥበብ ስራዎች ይቀርባሉ።
ስራችሁን ለማቅረብ ማስፈንጠሪያውን ተጠቅማችሁ በምታገኙት ቅጽ ተመዝገቡ! https://forms.gle/WveKjAsZ5PBx9MVr9
ሠላም ሠላም ግጥማዊ ቅዳሜያውያን ወርሃዊውን የጥበብ ድግሳችንን እንዲሁም የ5ኛ ዓመት የምሥረታ በዓላችንን የምናከብርበት ፕሮግራማችንን ይዘን መጥተናል!
ቅዳሜ መጋቢት 25 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በፈንድቃ የባህል ማዕከል ተገናኝተን አብረን እናክብር፡፡
አዲስ በወጣው የኮቪድ-19 የጥንቃቄ መመሪያ ምክንያት የታዳሚያችንን ቁጥር ቀድመው ለተገኙ 50 ሰዎች ብቻ ልንገድበው ተገድደናል፡፡
የመግቢያ ዋጋ፡ 100 ብር ብቻ
አዳዲስ እና የራስዎን ፈጠራ ብቻ እንዲያቀርቡ ይመከራል
ለእያንዳንዱ አቅራቢ 5 ደቂቃ ብቻ ቢፈቀድም የፈለገውን ያህል ማቅረብ ይችላል።
ምንም አይነት የቋንቋ እና የይዘት ገደብ የለውም
ምንም አይነት የጥበብ ስራ ይበረታታል
ይምጡና የጥበብ ቤተሰባችንን ይቀላቀሉ!
*** ጀማሪ እና አዳዲስ ፀሐፊያን ይበረታታሉ! ***
*Do not forget your mask!*
Hi Creative Addis, Poetic Saturday will be on this Saturday, April 3rd, 2021 at Fendika Cultural Center to celebrate our 5th Year Anniversary!
Due to the latest COVID-19 safety guidelines, we are forced to limit our audience to the first 50.
Entrance Fee: 100 Birr
As usual, we will start registration at 2: 00 pm.
Only perform YOUR ORIGINAL work. The audience is there to listen to your truth!
Each performer gets 5 minutes total. You can perform as many times but respect the time limit.
All languages welcome.
Shifta Lounge will host a book launch event on Saturday 27 March 2021. The event will feature book excerpt readings, music and poetic performance by all-female talents. Doors will open at 3:00pm. Entrance is for free but a green dress is a must. @linkupaddis
They say
a picture is worth a thousand words
But
a word creates thousands of wounds
They say
every picture tells a story
But they don't really know
how every word in a poem is stony
They say
words are powerful
They can create or they can destroy
They don't really know
how pictures create words in our head
how words can picture
what pictures can't capture
...
But in deed,
a picture is worth a thousand words
a word is worth a thousand words
if words were not invaluable
©Seife Temam
"እንዴት ነው ግን ሳይንስ ተንሰራፋ በተባለበት አካባቢ አሉባልታ እግዜርን፣ ተፈጥሮንና ተጠየቅን የምትዘርረው?
ታዲያ ሰኞ ተከራክረዋቸው ሐሙስ የስም ማጥፋት ዘመቻ ሰለባ ይሆናሉ።
በዚያን ጊዜ ፖለቲካ ይደረጋል እንጂ በመረጃና በጥናት የተደገፈ ሳይንሳዊ ውይይት የለም።
ይፃፋል ይባላል እንጂ የሚረባ አይደለም።
በስነ-ፅሁፍ በኩል የነበረው የደሃነት መጠን አይጣል ነው። በኢኮኖሚክስ፣ በሶሲዎሎጂ እና በአንትሮፖሎጂ በሌሎችም መስኮች እጅግ ሰፊና ጥልቅ የሆነ የጥሬ መረጃ ጉድለት አለ።
አገሪቱ ችግር ቢያጋጥማት የነሲብና የአውቃለሁ ባይነት ውጤቶች ናቸው።
የዋሸሁ ከመሰለሽ ዪኒቨርሲቲ ሄደሽ የተጠናውን የጥናት መረጃ እዪ። ያሉት ጥናት ተብዬዎች እርስ በእርሳቸው ግማሽ እውነት፣ ቅጥፈትና ስህተት እንደ ማሚቶ የሚቀባበሉ እንደሆኑ መገንዘብ ትችያለሽ።
እነዛን መረጃዎችና ከዛም የጠለሉትን ፅንሰ ሀሳቦች ለመፈተሽ አዲስ መረጃ ካመጣሽ ወይም ይኑር ካልሽ ነባሩ ሀሳብ ስለሚፈርስባቸው አይፈልጉሽም።
በስህተታቸው የተዝናኑ ነበሩ።
ያልተስተካከለ መረጃ ከያዙ የባዕድ መፅሀፍት ላይ ሃሳቦችና ቃላት ተለቃቅመው ብዙ ግድፈት ይሰራል። ተሟጋች ጥሬ መረጃ ይዞ ካልቀረበ ሌሎችን መምሰሉ ከአሉባልታ የተለየ አይደለም።
'እንትና የተባለው የዚህ ሀገር ፕሮፌሰር እንትን በተባለ መፅሀፉ ስለ ኢትዮጵያ እንትን አለ' ማለት ምንም ማለት ነው። ከእንትን እና እንትን ብዛት ምን ትጠብቂያለሽ? የተፃፈ አሉባልታ እንጂ።
ስለዚህ አሉባልታ ስለምፈራና የስነ ዕውቀታቸውን መልክዓ ምድር (epistemological landscape) ስለምጠራጠር ለማናቸውም ግድ አልነበረኝም።
***
የስንብት ቀለማት
የያዘች ይመስል
ምድርን በካስማ
ከመንደሩ አንስቶ
እስከ ዳር ከተማ
ያደናንቋታል
ሰው እየተሻማ
እንደደብሩ ማህሌት
ያለችው ሚሰማ
ማማውን ምታስንቅ
ከረባዳው ቆማ
ኧረ ማነሽ ልጅት
የማነሽ ኮረዳ
ያላወቀሽ አለ
ለቀየው እንግዳ
ድንገት ፊቴ ቆመሽ
እንዳትገቢ እዳ
ይሏታል
እንዝርቱን አሹራ
ይሏታል
ፈትላ ያንን ጥጡን
ይሏታል
ለሰራችው ሸማ
ይሏታል
ሸጠላት እርስቱን
ይሏታል
ባፈላችው ቡና
ይሏታል
በጣለችው ጠጅ
ይሏታል
ከሚስቱ አጣላችው
ይሏታል
ቀምሶት አንድ ወዳጅ
እቴጌ እቴጌ
ገብያም አትውጪ
አትምጭ ከቀብሩ
ዕቁቡም ይቅርብሽ
እድር ማህበሩ
ባይንሽ ሰዋይሙትብሽ
አዛኝ ሁኚ ሩሩ
ይላላክልሻል
ጠቅላላ ሰፈሩ
ኤፍሬም ገነነ©
ጠረንህ አሰረኝ
መአዛ አሰከረኝ
ተንገዳገድኩ ፣
ናፈቅኩህ
እንደ እናት እቅፍ
እንደመንሰፍሰፍ
እንደ መንዘፍዘፍ ፣
እንዲ መሆንን መች ተማርኩት?
ከእውነትህ ስር ነው ገባኝ ያደኩት ::
ከእምነት ወንጌል
ከህይወት ላይ ቃል፣
ይፈሳል ደጅህ
አበጃጀኝ ፣
ሰው አርጎ ሰራኝ
መንገዴን መራኝ ::
ናፍቆት አሰከረኝ
ተንገዳገድኩ
ናፈቀኩህ
እንደ መንሰፍሰፍ
እንደመንዘፍዘፍ
እንዲ መሆንን መቼ ተማርኩት???
መች ለት አወቅኩት ?
ቅፅበት ለዘላለም
ዘላለም ለቅፅበት ምንና ምን ናቸው?
ሳውቅህ አወቅኳቸው ::
©መቅደስ ሞገስ
Calling all Ethiopian artists: travel from Addis to Jinka for 10 days in May 2021 all-expenses paid and meet, connect, learn, exchange, aspire and empower with those residing in the towns we travel through. Astrobus 2021
www.bruhclub.com deadline is 12th April 2021
@artsmailinglist
Hey guys
We are sorry to inform you that the ጠላ አለ series tomorrow have been postponed to a later date.
Please stay tuned @huletegna
The organizers send their apologies and will inform you about the new date, stay tuned
አንጎራጉራለሁ ለነፍሴ
እስቅበታለሁ ለጥርሴ
ነፍስ መክተሚያ አለው ሲሽትበት
ውበት ያጠምዳል እተገኘበት
አይንም ማረፊያውን ይሻገራል
ኮከብ አድማሱን ይማትራል ::
ለሁሉም አለው መሆን
ዝምታዬን ምን ይሁን !
©መቅደስ ሞገስ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
