Brook Fekadu
Відкрити в Telegram
1 815
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 день
Архів дописів
1 815
መዲና ዉስጥ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ።
ታላቅየዉ ሀብታም ሲሆን ታናሹ ምንም አልነበረውም።
ታናሹ ወንድም ነብያችን (ሠዐወ) ጋር ቁጭ ብሎ ለመማር እንደሚፈልግ ለታላቅ ወንድሙ ይነግረዎል። ታላቅየዉም ይስማማና እሱ ጋር እየኖረ መማር እንዲችል ይፈቅዳል። ጊዜ እየሄደ ሲመጣ Complaint ማድረግ ጀማመረ። እኔ ቤት ተቀምጦ፣ የእኔን ምግብ እየበላ ብሎ ወቀሳ ለማቅረብ ረሱል (ሠዐወ) ዘንድ ሄዶ የእኔ ቤት ዉስጥ ፣ የእኔን ገንዘብ ፣ የእኔን ምግብ ብሎ አለቃቀሰ፤ ነብያችን (ሠዐወ) እንዲህ አሉት :-
አላህ እኮ ይሄንን ሁሉ ሀብት የሰጠክ በታናሽ ወንድምህ ሰበብ ነዉ። አሉት
ከዚህ ምን እንረዳለን አላህ ሀብትም ሆነ ፀጋ ሲሰጠን ስለሚገባንና ስለለፋን ብቻ ላይሆን ይችላል ፤ አንዳንዴም እኛ ጋር ጠጋ ባሉ ሠዎች ሊሆን ስለሚችል የእኔ የእኔ አንበል።
1 815
س/هل يجوز التطبيع عند عدم القدرة ؟
ጥያቄ/ አቅም ያነሰን( ደካማ) ከሆንን ከፅዮናዊቷ ወራሪ ጋር ግንኙነታችን (እንደ ሉኣላዊ ሀገር ቆጥረናት) ማስማማትና አብረን መቀጠል እንችላለን?
ج/ الجواب: لا ؛ لأن من لا يستطيع الزواج لا يجوز له الزنا
መልስ/ አይቻልም። ምክንያቱም ማግባት ላልቻለ ሰው ዝሙት አይፈቀድለትምና።
سيدي الشيخ الشهيد أحمد ياسين رضي الله عنه
ሸሂድ ሸይኽ አህመድ ያሲን (ረህመቱላሂ ዐለይሂ)
1 815
የሳዑዲን መንግስት መተቸት አልያም መንቀፍ ለመካና መዲና ክብር መንሳት አይደለም።
መካ፣ መዲና አቅሳ የዓለም ሙስሊም ሀብቶች እንጂ የመንግስት ቱሪስት መስዕቦች አይደሉም!!!
1 815
ዱዓ ማለት አንተ በፈለከዉ እና ባሰብከዉ መንገድ ብቻ ይሳካልክ ዘንድ አላህን መጠየቅ አይደለም።
ዱዓ ባርነትህን ይበልጥ ያስታዉስሃል ፤ ባሪያ ደግሞ ጌታዉን ሲጠይቅ በአዛዥ ስነልቦና ከሆነ መታረም ይገባዋል።
እንደዉም Nouman Ali khan "Revive your Heart" የሚል መፅሀፉ ላይ እንዲህ ይላል።
" ዱዓ ካፌ ገብተክ እንደምታዘዉ ምግብ አይደለም ፤ ለምግብክ ገንዘብ ከፍለሃል ለዱዓ ግን ምንም ሳትከፍል እንዲሰጥክ የከፈልከዉን ነገር ጥያቄ ማቅረብ ብቻ ነዉ።'' ይላል
በጋዛ ጉዳይ የዓለም ሙስሊም ዱዓ ስላደረገ ብቻ የፈጠነ ድል መጠበቅ ሞኝነት ነዉ።
አላህ የራሱ ተርቲብ እና ስርዓትን ለዱንያ ዘርግቷል። እኛ እሱን መጠየቅ ፣ መለመን፣ ድፍት ብለን ዱዓ ማድረግ ሃላፊነታችን ነዉ።
ቀጥሎም አላህ ዉጤቱን ያሳምረዉ ብለን እንጠብቃለን።
1 815
አላህ ሆይ አንተን በመገዛቴ ደስተኛ ነኝ፤በሰጠሀኝ ፀጋዎች አመሰግንሃለሁ።ልቤ ያንተ ቤት ብቻ ትሆን ዘንድ እማፀንሃለዉ።ዓለም ፊት ቆሜ ስላንተ ቸርነት ለማዉራት አላፍርም። የኔ ወዱድ ባንተ እርዳታ እዚህ ደርሻለሁ፤ ባንተም እዝነት ወደ ተሻለው እሄዳለሁ።
በአላህ አምላክነት ፣በእስልምና ሀይማኖትነት ፣በሙሃመድ(ሰ.ዐ.ወ) መልዕክተኝነት ፍፁም ደስተኛ ነኝ!!
1 815
ጋዛ ከኛ ምን ትፈልጋለች?
የኛ መንፈሳዊነት ለጋዛ ትልቅ ስንቅ ነዉ!
የኛ እገዛ በእስቲግፋር
የኛ እገዛ በትክክለኛ ተዉበት
የኛ እገዛ በዱዓ ቢሆን አትጠራጠሩ የናፈቅንለት ድል ቅርብ ይሆናል።
ሙሳ(ዐ.ሰ) ህዝባቸዉ ዝናብ ተከልክሎ፤ በአንድ ሰው ተዉበት ዝናብ እንዳገኙ እናዉቃለን።
ሁላችንም የዚህ ሁሉ ችግር መነሻ ''እኔ'' ነኝ ብለን ወደ ኃያሉ አላህ ፊታችንን እዙረን እናልቅስ።
ዘከሪያ (ዐ.ሰ) ነጭ ፂም ወሯቸዉ፣ አጥንታቸው ዝሎ በእድሜያቸው የመጨረሻ ክፍል ላይ አላህ ልጅ የሰጣቸው በአንዲት ዱዓ ነው።
ዱዓ ሰናደርግ ዉስጣችን ማመን ያለበት ጉዳይ አላህ ምንንም ነገር ማድረግ ቻይ መሆኑን በማሰብ ይሁን!!!
1 815
አላህ ይቅር ባይ ነዉ!!
ወንጀልህ ከባህር ዐረፋ በላይ ገዝፎ በፀፀት ወደ ቻዩ ጌታህ ጠጋ ስትል የእዝነቱን በር ከፍቶ ባርያዬ እንኳን ተመስክ ብሎ ወደ ምህረቱ ጓዳ ይሸሽግሃል።
ምንም ሰርተህ ፤ ምንም ሰርተሽ ይሆናል!! ግን ተመለስ/ሺ።
ምክንያቱም የፈጠረን ታላቅ አምላክ እየጠበቅን ነው ☺️።
አላህ ይቅርታቸዉን ከተቀበላቸው
ወንጀል ሰርተዉ ወደ እርሱ ለመመለስ ካልኮሩት
በሁሉም የህይወት መስክ ስኬት ከተላበሱት ያድርገን።
1 815
ሁሉም ቀን ያልፋል!!
መጥፎ መሆን የስስት እና ምቀኝነት ምልክት ነዉ። የሰይጣን ትልቅ ትግል በሰዎች ልብ ዉስጥ እነዚህን ቆሻሻ ባህሪዎች መዝራት ነዉ። ኮትኩቶ የማብቀሉን ሀላፊነት ደግሞ መልሶ ለኛ በመስጠት ይፈትነናል።
የሰዉ ልጅ ክፉ የመሆን ብቃቱ አያስገርመኝም፤ ክፉ ሆኖ በመልካም እንዲነሳ መፈለጉ ግን ያስደንቃል።
በጋዛ የደረሰው ግፍ የክፋት ዉሃልክ ሆኖ ሲያበቃ ምዕራባዉያን ይመጡና ስለ ሰብዓዊነት ይሰብኩካል።
እርግማኑ ሁሉ ለእናንተ የተገባ ይሁን!!!
1 815
Today I was so Happy SubhanAllah
ይሄን ምላችሁ በጣም የተለየ ነገር ተፈጥሮ አይደለም ... ነገር ግን Normal የሆነውን ነገር Simply ስላገኘሁት ነዉ።
ሰሞኑን ስልጠና ላይ ነኝ እና ብዙ ጊዜ ከሚገጥሙኝ ችግሮች መካከል የሶላት ቦታ የት ነዉ ማገኘዉ የሚለዉ አንዱ ነዉ??
በዚህ ስልጠና ላይ ግን ደስ የሚለው ድርጀቱ እራሱ የመስገጃ ቦታ የተመቻቸለት በመሆኑ ሀሳቤን ሁሉ ቀለል አድርጎልኛል።
ታድያ ዛሬ ምን ተፈጠረ መሰላችሁ? ዝሁር ሶላት ለመስገድ ወደ መስገጃዉ ሳመራ ብዙ ሰዎች ስብሰባ ላይ ነበሩ። እናም የረበሽኳቸዉ መስሎኝ መለስ ብዬ ወደኃላ ስሄድ አንድ ሠዉ ከኋላ ልጄ ብሎ ጠራኝ!!
መለስ ብዬ አቤት ስል
3ተኛ ፎቅ ላይ የእኔ ቢሮ አለ፤ የዶክተር ቢሮ የቱ ነዉ ብለህ ግባ አዛ መስገጃ ተነጥፏል። እዛ ስገድ እሺ ብሎ በፈገግታ መራኝ
እኔም ወደ 3ተኛ ፎቅ ወጣሁና የዶክተር ቢሮ የቱ ነዉ ብዬ ገብቼ ሰገድኩ እላቹሀለዉ።
የተፈጠረው ነገር Of course normal ነዉ!!
ደስ ያለኝ ግን የዶክተር ትህትና እና Normalize መደረጉ ይበል ሚያሰኝ ነዉ።
1 815
አሁን የጀነት በር አጠገብ ቆመዉ እስኪከፈትልዎ ድረስ እየጠበቁ ነው።
በሚከተለው መልኩ ፊት ለፊትዎ የሚከናወነውን ትዕይንት እየተመለከቱ ነው። በዱኒያ ላይ አሳዛኝ ኑሮ ሲገፋ የነበረ ሠዉ እንዲመጣ ይደረግና ጀነትን አየት አድርጎ እንዲወጣ በማድረግ - የዱኒያ ሕይወትህ መጥፎ ነበርን? አሳዛኝ ነገር ገጥሞህ ያዉቃልን? ተብሎ ይጠየቃል። እርሱም እንዲህ ሲል ይመልሳል።
- "በጌታዬ እምላለሁ! ምንም ዓይነት መጥፎ ነገር ገጥሞኝ አያዉቅም።"
From #ጉዞ_ወደ-ጀነት Book
