uk
Feedback
ከቃሉ ማዕድ

ከቃሉ ማዕድ

Відкрити в Telegram

☀️ ክርስቶስን መስለን በመኖር ፣ ላልተደረሱት የሕዝብ ክፍሎች በመፀለይ ፣ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ የሚፈልገውን እግዚአብሔርን የሙጥኝ የምንልበት ቻነል ነው። 1ጢሞ 2:1-4 ☀️ ደግሞም አብ የሰጠንን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በልተን ደግሞም ጠትተን ዕለት ዕለት ደግሞ 💥በሁለንተናችን የሚያሳድገንን የቃሉን🎯 ማዕድ የምንቆርስበት ትምህርታዊ እና መንፈሳዊ ቤት ነው። ዮሐ6:35

Показати більше
Країна не вказанаКатегорія не вказана
322
Підписники
Немає даних24 години
+67 днів
+6630 днів
Архів дописів
ዮሐንስ 13:1 1 ኢየሱስም ይህን ዓለም ትቶ ወደ አብ የሚሄድበት ጊዜ እንደ ደረሰ ዐወቀ። በዓለም የነበሩትን፣ የራሱ የሆኑትን ወደዳቸው፤ በፍጹም ፍቅሩም ወደዳቸው።አ.መ.ት
📌የሞተላችሁ ይወዳችኋል❕ 📌የወደዳችሁ ደግሞ አይጠላችሁም❕ 🤍መልካም ቀን ይሁንላችሁ🤍 『ከ』『ቃ』『ሉ』▪『ማ』『ዕ』『ድ』 ¶Join | Follow | Share 🚩@Kekalu_Maid #ከቃሉ_ማዕድ

" የመስቀል ሞት በጥንቱ ዓለም ከሁሉ የከፋ የውርደትና የሥቃይ ሞት ነው። በደረጃ ብናስቀምጣቸው ፣ በመስቀል ላይ ከመሞት ቀጥሎ ያለው ሁለተኛው አስከፊ ቅጣት በእሳት ተቃጥሎ መሞት ነው። በሮማውያን ግዛተ ዐፄ ውስጥ ሦስተኛው አስከፊ የሞት መንገድ ለአውሬ መሰጠት እና የራስ መቆረጥ ነው። በዚህ መልኩ ሰዎች ለአራዊት የሚወረወሩት ብዙኃንን ለማዝናናት ሲፈለግ በመሆኑ፣ ሕዝባዊ በዓላት ሲታቀዱ እና ለዚህ የተዘጋጁ አራዊት ሲኖሩ ይፈጸማል። 👐 መስቀል ግን ከሁሉም የሞት መንገዶች በአዋራጅነቱና በአሰቃይነቱ ይከፋል‼️" 📖የተሰቀለው📝ጳውሎስ ፈቃዱ ▻◅▻◅▻◅▻◅▻◅▻◅▻ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች ፪:፰ --- ፰፤ በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ። ▻◅▻◅▻◅▻◅▻◅▻◅▻◅▻◅▻◅▻◅▻ 💠 አምላከ ሰው መሆኑ ሲገርመን ፣ በምድር አኛን መስሎ አስተማረን ፣ ለሞት መታዘዙ ሲገርመን ከሞት ሁሉ በሚከፋው በመስቀል ሞት ለመዋረድ እንኳ የታዘዘ ሆነ። 💥" ሀጢአት የማያውቀው የአብ ልጅ የሆነው፥👑        እርጉም የተባለው የደም ላብ ያላበው🩸        ሰቀቀን ጣር ያየው ፥ መስዋዕት የሆነው፥☦        እኔን ሲመለከት እኔኑ ሲያየኝ ነው🛐        ከዘላለም ሞት እኔን ሊያድነኝ ነው !!!"
🎙ታርዶልኛል🎼 ከሚል ዝማሬ የተወሰደ!
〰〰〰🌩 ክብር ፣ ምስጋና፣ ስግደት፧ ሁሉ፦ 💫 ልዱን እስከመስጠት ለወደደን 👉 አብ {ዮሐ፫፥፩፮} 💫 እራሱን እስከመስጠት ለወደደን 👉 የአብ ልጅ ኢየሱስ {፩ ዮሐ ፫፥፩፮} 💫 ይህንን እውነት ለገለጠልን ከአብ ሰርጾ ለመጣው 👉 መንፈስ-ቅዱስ {ዮሐ ፩፭፥፪፮} 〰〰〰🌩 ለሥሕሉሱ እግዚአብሔር ይሁን❕〰〰〰 ❤️‍🔥 ⚜⚜⚜╭ከ╮╭ቃ╮╭ሉ╮◂▸╭ማ╮╭ዕ╮╭ድ╮⚜⚜⚜ #የተሰቃየው_ኢየሱስ #ከቃሉ_ማዕድ

Let's Do Telegram story!!! Telegram ላይ Repost እናድርግ!!!

🧨🎇🧨    Breaking News   🧨🎇🧨 🏵 ኑ ወደ ኢየሱስ 🏵 ጌታን መቀበል አማራጭ አይደለም⚠️ ⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻ የዮሐንስ ወንጌል ፩:፲፪ ፲፪፤ ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ 1 ተሰሎንቄ 5:9 9 እግዚአብሔር ድነትን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት እንድናገኝ ነው እንጂ ለቍጣ ወስኖ አላስቀመጠንምና። ⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻ "ሰው በምድር ላይ ብዙ ነገር ሊኖረው ይችላል፤ ኢየሱስ ከሌለው ግን ሁሉንም ነገር አጥቷል። ኢየሱስ ካለው ግን ምንም ባይኖረውም ሁሉንም አግኝቷል።" 📢 አባባ ዋንዳሮ ዳባሮ ◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸ 🎯 በመንግስተ-ሰማይ አብ ልጁን አርዶ ድግስ አዘጋጅቷል። 🎯 በጉ አባላትን በስሙ መዝግቧል 🎯 መንፈስ ቅዱስ ለበጉ ሰርግ ሽክ ያደርገናል። ◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸◂▸ @Kekalu_Maid #Digital_mobilization #ከቃሉ_ማዕድ

🫟  ምን እናድርግ❔ 🎯 የእግዚአብሔር ቃል ፥ በሙላት እንዲኖርብን ◦◦◦ ምን እናድርግ??? ⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
ቆላስይስ 3:16 16 የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ። በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ።
✔️   ቃሉን መራብ {የቃሉ ረሀብተኛ መሆን}1ኛ የጴጥሮስ መልእክት ፪:፩-፫ --- ፩፤ እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥ ፪-፫ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ። 🔅አንድ ወዳጄ ብዙ ጊዜ የሚጠቀመውን ምሳሌ በመሰጠት ልጀምር ፦ 👉 "እንግዲህ መራብ ያለ ነውና... አንድ ቀን እንዲሁ ቢርባችሁ ምሳ በደንብ በላችሁ 🍔🍜🍝🍛🍲🍔 በደንብ ጠገባችሁ፤ ምግብ ድጋሚ የሚያስፈልጋችሁ እንኳ አትመስሉም። ይገርማችኋል ግን ለብዙ ሳምንታት ምንም ባትበሉም🍽 ምንም አራባችሁም!!!".... አይገርምም?😲 ብላችሁ... እናንተ ደግሞ 'ይሄ ሰው ጤነኛ አይደለም እንዴ? ለምንድነው? የማይርበኝ🤔 ካራበኝም ለመብላት እሞክራለሁ ሐኪም ቤት እታያለሁ።ወዘተ ' ትሉኛላችሁ። መቼስ ለኑሮ ውድነቱ ጥሩ መላ ነው ጌታ ሆይ ተመስገን😊 እንደማትሉ ተስፋ አደርጋለሁ። ለምን? ቢባል አለመራብ በራሱ ሙሉ ጤንነት ስላይደለ❕ የወስፋት መቆለፍም ሊሆን ይችላል ሳምንት አይቆይም እንጂ። 💥 የእግዚአብሔርም ቃል ልክ እንደዚሁ ነው። ቃሉን አለመራብ "መንፈሳዊ በሽታ/Spiritual disorder" ነው‼️ ስለዚህም ነው " እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ። " ቃሉ የሚለን። ገና የተወለደን ሕፃን የእናት-ጡት መጥባት አታስተምሩትም ምክንያቱም? ወተት ምግቡ ነው ፣ መጥባት ደግሞ 'by default' የተሰጠው ሰለሆነ። ልክ እንደዛው የእግዚአብሔርንም ቃል መመኘት እንድንችል የተገለጠ የእግዚአብሔር ጸጋ አለ። ✥ ከእግዚአብሔር ቃል የሚነጥሉንን ነገሮችን ግን ማስወገድ ይጠይቃል። ለምሳሌ፦ ➪ ክፋትን ➪ ተንኰልን ➪ ግብዝነትን ➪ ቅንዓትን ➪ ሐሜትንም ሁሉ ማስወገድን ይጠይቃል። ✔️   የቃሉ ደጅ እንዲከፈትልን መፀለይ ቆላስይስ 4:3 3 በዚያን ጊዜም ስለ እርሱ ደግሞ የታሰርሁበትን የክርስቶስን ምሥጢር እንድንነግር እግዚአብሔር የቃሉን ደጅ ይከፍትልን ዘንድ ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ። 💫ሐዋሪያት ከነበራቸው አንድ ትልቅና ጥልቅ ሀብት መካከል📌 የእግዚአብሔር ቃል ዕውቀት ነበራቸው። ጳውሎስ እና ሌሎች አዕማድ የሆኑ ሐዋሪያት እና ደቀመዛሙርት "እግዚአብሔር የቃሉን ደጅ ይከፍትልን ዘንድ ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ" ብለው ከተናገሩ እኛ ለእራሳችን ብሎም አንዳችን ለአንዳችን የቃሉ ደጅ ይከፈትልን ዘንድ የማንጸልይበት ምንም ምክንያት የለንም።⚠️ ✔️   ⓷ ቃሉን በሙሉ ልብ ጆሮ ሰጥቶ ማድመጥ ነህ ፰:፫-፱ --- ፫፤ በውኃውም በር ፊት ባለው አደባባይ ላይ ቆሞ፥ ወንዶችና ሴቶች የሚያስተውሉም ሲሰሙ፥ ከማለዳ ጀምሮ እስከ ቀትር ድረስ አነበበው የሕዝቡም ሁሉ ጆሮ የሕጉን መጽሐፍ ለመስማት ያደምጥ ነበር..... ፱፤ ሐቴርሰታ ነህምያም ጸሐፊውም ካህኑ ዕዝራ ሕዝቡንም የሚያስተምሩ ሌዋውያን ሕዝቡን ሁሉ፦ ዛሬ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ቀን ነው፤ አታልቅሱ እንባም አታፍስሱ አሉአቸው፤ ሕዝቡ ሁሉ የሕጉን ቃል በሰሙ ጊዜ ያለቅሱ ነበርና 💥 አሁን ላይ ለቃሉ ያለን ልብ እንኳን ግማሽ ቀን አይደለም... 30 ደቂቃ ለመቆየት እረ ስንቱን ተፈተንን⁉️ ነገርግን ቃሉ ተሰምቶ የሚወደድ ብቻ ሳይሆን ለሰሙት የሚያስለቅስ መልዕክት አለው። መስማት ብቻ ሳይሆን ልብ ሰጥቶ ማዳመጥ ያስፈልገናል። ✔️   ⓸ በእግዚአብሔር ቃል ጸንቶ መኖር 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ ፫:፲፬-፲፮ --- ፲፬፤ አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤ ፲፭፤ ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል። ፲፮፤ የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል። ❇️ በተማርነው ቃል ጸንተን መኖር ለምን ይጠቅመናል? ✦ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ይሰጠናል ✦ መንፈሳዊ ፍፅምናን(ብስለትን) ይሰጠናል ✦ ለበጎ ሥራ ያዘጋጀናል ✦ የእግዚአብሔር መንፈስ የሚገኝበት መጽሐፍ ነው ✦ ለትምህርት ይሆነናል ✦ ልባችንን ያቀናዋል ✦ በፅድቅ እንድኖር ይመክረናል። ═════════════════════════════════ ☣ የመንፈስን ሰይፍ (የእግዚአብሔርን ቃል) የታጠቀ ወንጌልን ተጫምቶ የቆመ ጦረኛ ያድርገን🙏🙏🙏 ═══════╰ከ╯╰ቃ╯╰ሉ╯▪╰ማ╯╰ዕ╯╰ድ╯═══════ #የእግዚአብሔርን_ቃል_በልብ_ማኖር ¶Join | Follow | Share 🚩@Kekalu_Maid #ከቃሉ_ማዕድ

ትንቢተ ኢሳይያስ ፶፫:፩-፲፪ ═══════════════════════════ --- ፩፤ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል? ፪፤ በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል፤ መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም። ፫፤ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም። ፬፤ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። ፭፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። ፮፤ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ። ፯፤ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። ፰፤ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ? ፱፤ ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ፤ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም ነበር። ፲፤ እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል። ፲፩፤ ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሸከማል። ፲፪፤ ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ። ✧ ባነበብኩት ቁጥር ፥ 12 ቁጥር መሆኑ እስከሚገርመኝ ድረስ በነብዩ ኢሳይያስ በ 8ኛው ሴንቸሪ ከ700BCE (ከክርስቶስ ልደት በፊት) የተፃፈው የእኛ ታሪክ❕ 1 ቆሮንቶስ 1:23 23 እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ይህም ለአይሁድ መሰናክል፣ ለአሕዛብ ደግሞ ሞኝነት ነው። 🚩ሰዎች ሲያፌዙበት እኛ ግን ዳንበት❤️‍🔥 🚩 #በእርሱ_ቁስል #ከቃሉ_ማዕድ

https://youtu.be/IuEOIXrSCj4?si=zP--qTqje5337xUt #Encounter ¶Join | Follow | Share #ከቃሉ_ማዕድ

https://youtu.be/O_uVe97MPpw?si=tsfQQzLtkpvbUorg #Encounter ¶Join | Follow | Share #ከቃሉ_ማዕድ 📌

✦✦✦ እስኪ እንሟገት ✦✦✦ 🎯"ልንኖረው የተጠራንበት ክርስቲያናዊ ሕይወት ምን አይነት ነው?" ❄️'የክርስትና ሕይወት ዛሬ ብዙዎች ከሚኖሩት ሕይወት በፍጹም የተለየ ነው። የእግዚአብሔርን ቃል ልብ ብለን ስናጠና ለዚህ ጥያቄ የምናገኘው መልስ ፤ የእግዚአብሔር ልጅ ራሱ የኖረው ሕይወት የሚል ይሆናል።' 🎯' ትክከለኛው የክርስትና ሕይወት ምን አይነት እንደሆነ በገላ 2፥20 " ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ፤ ከእንግዲህ እኔ አልኖርም፤" ይህም ማለት እግዚአብሔር ሁልጊዜ የሚሰራው በእኛ ፈንታ ክርስቶስን በማስቀመጥ ነው። እኛ ይቅርታን እናገኝ ዘንድ የእግዚአብሔር ልጅ ሞተልን፣ አርነት እንወጣም ዘንድ እርሱ በእኛ ፈንታ የእኛን ሕይወት ይኖራል። '
◎ ከዋችማን ኒ 📖Normal Christian life{ክርስትና እንዲህ ነው} የተቀነጨበ!
🔅እንደ እውነታው ግን እኛ ያለን ሕይወት ክርሰቶስ በእኛ የሚኖርና የክርስቶስ ልብ ያለን ሰዎች እንመስላለን? 🎯 የእኛስ ክርስትና እንዴት ሆኖ ይሆን??? ♨️ የጥሞና ጊዜ ስለሌለን በልማድ ወይም በአዕምሮ ብቻ የሚደረግ አገልግሎት ወስጥ ገብተን ፀሎት ፣ የእግዚአብሔርን ቃል አለማጥናት የህይወታችን አንድ ገፅታ ሆኗል። 👉 አንተ ግን ስትጸልይ፥ ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።ማቴ 6:6 የሚለው መርህ(principle) ተቀይሮ ጓዳችን Social Media ተጠቃሚ ነን፤ ቸርችም ከባድ መንፈሳዊ ነንî ውጊያውን ግን እየተረታነን እንደሆነ የዘነጋን ይመስላል። ♨️ የዚህ ውጤት ደግሞ መቀደስ አንፈልግም ኢየሱስን ሳይሆን ዓለማዊነትን እናንጸፀባርቃለን።በነገራችን "#Illuminati" የሚለው የቃሉ ትርጉም ከዚህ የተለየ ፍቺ የለውም። ለዚህም የእኛ የቅርብ ጓደኞቻችን እንኳ መንፈሳዊ ከሚሆኑ #ለዘብተኛ አማኞች ይመቹናል። ♨️ ቤተሰብ ፣ ጓደኛ ፣ ቤተክርስቲያን በማያውቁት አይነት የኃጢአት እስራት ውስጥ ሆነን ግን ቤተክርስቲያን መተን ለበሽታችን መድኀኒት እንደመፈለግ ፤ #ታሞ_አስታማሚ የደረቀ አማኝ ሆነን በአስመሳይ ማንነታችን በጣም የጸሎት ሰው ፣ በጣም ዘማሪ ፣ ጎበዝ ሰባኪ እንደ እኛ ማን አለ??? ደጅ የማያውቀው sexual impurities (ቪዲዮዎች ፣ ንግግሮች ፣ ስውር ኃጢአቶች) የእኛን ቤት አተራምሰውታል። ♨️አንዳንዶቻችን ቸርች ስንሄድ መፅሐፍ ቅዱስ ይዘን ከሄድን እንኳ ሰንበትበት ብሏል። የሚገርመው ይዘን አለመሄድ የተጋነነ ችግር ሆኖ ሳይሆን ይዘን መሄድ የምንችል ይመስለናል ነገርግን ብንሞክረው የሚያቅተን ስንቶቻችን ነን? 🔆ጉራማይሌ ሕይወት ያለው እንደ እኛ ማን አለ?🔆 🏵 በአንድ መድረክ አገልጋይ በጋሻው እንዲህ ሲል ተናገረ ፦ << "ንጉሡን ክርስቶስን ለማክበር ምንም ዓይነት ጋጋታ ምንም ዓይነት ሌላ ትርዒት አያስፈልግም፤ ህይወት ብቻውን በቂ ነው። የእኛ መራራ አንደበት የእኛ መራራ ህይወት ነው ብዙዎች ጌታን እንዳይቀበሉ የሚያደርገው ፤ እኛን ስለጠሉ ክርስቶስንም ደርበው ጠልተውታል! 'ክርስቶስን ያልተቀበላችሁ ፥ እኛን አትዩ የእኛን መራራነት አትዩ  እርሱ ፍቅር፣ እርሱ ሰላም ነው ፧፦ እርሱ እንደ እኛ ገዳይ፣ ዘረኛ ፣ አሳዳጅ ፣ በገንዘብ ፍቅር የሰከረ አይደለም። ኢየሱስ ፍቅር ነው።" ብሎ ነበረ። " ማደግህ በነገር ሁሉ እንዲገለጥ ይህን አስብ፥ ይህንም አዘውትር። " 1ጢሞ 4:15 👉 በህይወታችን ለውጥ እንዲገለጥ እግዚአብሔርንም ሐሰተኛ ሳናደርግ <1ዮሐ1:9> ወደጌታ የጸጋ ዙፋን እንደገና #መደፋት🛐 ያዋጣናል። ◄►◄►◄►◄►◄►◄►◄►◄►◄►◄► ዕብራውያን 4:16 16 እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበልና በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ፣ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ። ◄►◄►◄►◄►◄►◄►◄►◄►◄►◄► ☀️ ክርስትናን ተናግረን ሳይሆን ኖረን ማለፍ ይሁንልን .🙏. °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ይቀጥላል◦◦◦ #ክርስትናን_መኖር ¶Join | Follow | Share #ከቃሉ_ማዕድ

🎯ከታላቁ ሚስዮናዊና አሳሽ ዴቪድ ሊቪንግስተን (David Livingstone)  ምን እንማር? ከክፍል_አንድ የቀጠለ.....👇    
   ከደብዳቤው_ክፍል_3
​“...በሕይወቱ ትልቁ ዓላማዬ እርሱን ብቻ መምሰል ነው።”          
📌የሊቪንግስተን ትልቁ የሕይወት ግብ ስምና ዝናን ማግኘት፣ ወይም አዳዲስ ቦታዎችን ማግኘት ብቻ አልነበረም። ዋናውና የመጨረሻው ማረፊያው "ክርስቶስን መምሰል" ነበር። 👉እኛም በሕይወታችን የምናደርጋቸው ነገሮች ሁሉ (ትምህርታችን፣ ሥራችን፣ አገልግሎታችን) ስኬታማ የሚሆኑት ከመጨረሻውና ከዋናው የሕይወት ግባችን ጋር ሲገናኙ ብቻ ነው። ስለዚህ ከዚህ ታሪክ የምናገኘው ጭብጥ፦👇 💫ይህ የዴቪድ ሊቪንግስተን ሕይወት እውነተኛ ስኬት የሚለካው በምናገኘው ምድራዊ ስምና ዝና ሳይሆን፣በምንኖርለት ዘላለማዊ ዓላማ መሆኑንያረጋግጥልናል። 👉 በሕይወታችን የምናደርጋቸው ዕለታዊ እንቅስቃሴዎች ሁሉ ትርጉም የሚኖራቸው ከዋናውና ከማይናወጠው የሕይወት ግባችን ጋር ሲገናኙ ብቻ እንደሆነና ትልቁ የሕይወት መደምደሚያም ክርስቶስን መስሎ መገኘት መሆኑን የሚያስተምር ታላቅ ምስጢር ነው። 📍በነገራችን ላይ በጣም ትኩረት መስጠት ያለብን ለ ራዕይ በለን መራደት ላይ ነው። 👉ራዕይ ማለት የምንደርስበት ምድራዊ ቦታ ብቻ ሳይሆን፣ በጉዟችን ሁሉ ውስጥ የምንሆንበት ማንነት ነው፤ ስኬታችንም ሙሉ የሚሆነው ምድራዊ ተግባራችን ከሰማያዊው ግባችን ጋር ሲናበብ(አንድ) ሲሆን ብቻ ነው። 🎯ከታላቁ ሚስዮናዊና አሳሽ ዴቪድ ሊቪንግስተን (David Livingstone)  ምን እንማር? ይቀጥላል...👇 https://t.me/onegodtruthሥላሴያዊ ነኝ( Trinitarian🎯) #Mission_Mindset 👉@onegodtruth👈 #ከቃሉ_ማዕድ📌

🎵 አስር ጊዜ ባይህ -10 gize bayih-ዮሴፍ አስቻለው/Yosef Aschalew 👤 خواننده: Yosef Aschalew 💿 آلبوم: نامشخص 📅 انتشار: نامشخص 🔗 لینک اصلی: https://www.youtube.com/watch?v=-ZOFfRhmQMQ ❤️ دانلود شده با @YtbAudioxBot

◌◌◌መ‌ነካት እ‌ሰ‌ከ-ም‌ን‌❓ ⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
ዘሌዋውያን 25:39-40 ⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻ 39 ወንድምህም ቢደኸይ ራሱንም ለአንተ ቢሸጥ፥ እንደ ባሪያ አድርገህ አትግዛው። 40 እንደ ምንደኛና እንደ መጻተኛ ከአንተ ጋር ይሁን፤ እስከ ኢዮቤልዩም ዓመት ያገልግልህ።
👉 እንግዲህ አንድን ዕብራዊ ሰው ባሪያ/አገልጋይ/ ለማድረግ ዕብራዊው ባሪያ የጌታው ወዳጅ የነበረ ነገርግን በድህነት ምክንያት ለእርሱ ባሪያ ሊሆን የፈለገ ቢሆን በኦሪት ሕግ አይፈቀድምና እንደ ሠራተኛ ወይንም እንደ እንግዳ አድርጎ እስከ ኢዮቤልዩ ዓመት ሊያቆየው ይችላል። 🎯ስለሆነም ይህንን ሕግ ባልተጣረሰ መልኩ የባሮቹ ጌታ ዕብራዊውን ወይም ዕብራዊቱን ቢገዛ ስድስት ዓመት ካገለገሉት፤ በሰባተኛው የዕረፍት ዓመት ነፃ እንዲወጡ ያደርጋቸዋል።{ዘዳ15:12-17} ስለሆነም አርነት ባወጣው ጊዜ ባዶውን አይሰደደውም። ነገር ግን ከመንጋው ፣ ከአውድማው፣ ከወይን መጥመቂያው ሁሉ ይሰጠዋል። "አምላክህ እግዚአብሔር እንደ ባረከህ መጠን ትሰጠዋለህ" ይላልና። ለምን? ብንል "አንተም ራስህ በግብፅ ባሪያ እንደ ነበርህና አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እንደ ተቤዠህ አስታውስ፤ ይህን ትእዛዝ ዛሬ የምሰጥህም በዚሁ ምክንያት ነው። " ይላቸዋል። 🔆 ነገር ግን አንድ ነገር አለ 👉🏼 ባሪያው/አገልጋዩ/ የጌታውን ቤተ-ሰብ ከመውደዱና ከእርሱም ጋር ደስተኛ ሆኖ ከመኖሩ የተነሣ፣ “ከአንተ መለየት አልፈልግም” ቢል👇 📌 ጆሮውን በወስፌ ይበሳዋል። ከዚያም ዕድሜ ልኩን አገልጋዩ ይሆነዋል። በሴት አገልጋዩም ቢሆን እንደዚሁ ያደርጋል።
📌አሁን ግን ከኃጢአት አርነት ወጥታችሁ ለእግዚአብሔርም ተገዝታችሁ፥ ልትቀደሱ ፍሬ አላችሁ፤ መጨረሻውም የዘላለም ሕይወት ነው። ሮሜ 6:22
═════════════════════════════════ ☀️ እኛ የአዲሱ ኪዳን ሰዎች ደግሞ እግዚአብሔር ልጁን በመስቀል ጠርቆ የኃጢአት ባሪያ ፣ የዓለም አገልጋይ ከሆንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሰት የፈለስን ደግሞም ለወደደንና ከኀጢአታችንም በደሙ ነጻ ላወጣን፣ አምላኩንና አባቱን እንድናገለግል መንግሥትና ካህናት ላደረገን በናገለግለው ፣ ብንሮጥለት ምንም ባይመጥነውም ተገደን ሳይሆን ወደን ለጊዜው ሳይሆን ዕድሜ ልክ ልንገዛለት ጆሮአችንን በስተን መኖር ይሁንልን። ═════════════════════════════════ ✴️በክርስቶስ ፍቅር ተነድፎ ጆሮውን በስቶ የሚኖር አማኝ ያድርገን!!! ═════════════════════════════════ #እስከሞት_መነካት #ከቃሉ_ማዕድ

"እግዚአብሔርን ለምንድን ነው የምንፈልገው? ለፈቃዱ ወይንስ ለሀይሉ?"... 👉"በእግዚአብሔር ፈቃድ ውሰጥ ስናልፍ ሀይሉ አብሮን እንዲኖር መፈለጋችን እንዳለ ሆኖ የኃይሉ መዳረሻ የሆነውን ፍጹም ፈቃዱን ግን ሁሌም ማሰብ አለብን።" 📖የፈቃዱ መንገድ ✍ዮናታን አክሊሉ #ከቃሉ_ማዕድ