ከቃሉ ማዕድ
Відкрити в Telegram
☀️ ክርስቶስን መስለን በመኖር ፣ ላልተደረሱት የሕዝብ ክፍሎች በመፀለይ ፣ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ የሚፈልገውን እግዚአብሔርን የሙጥኝ የምንልበት ቻነል ነው። 1ጢሞ 2:1-4 ☀️ ደግሞም አብ የሰጠንን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በልተን ደግሞም ጠትተን ዕለት ዕለት ደግሞ 💥በሁለንተናችን የሚያሳድገንን የቃሉን🎯 ማዕድ የምንቆርስበት ትምህርታዊ እና መንፈሳዊ ቤት ነው። ዮሐ6:35
Показати більшеКраїна не вказанаКатегорія не вказана
322
Підписники
Немає даних24 години
+67 днів
+6630 днів
Архів дописів
322
◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌የፀሎት ጥሪ ◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌
🔆ወንጌል አማኝ ለሆነ ሁሉ🔆
⚠️ለ 10/40 መስኮት⚠️
2 ቆሮንቶስ 5:18-19 18 ይህ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፤ እርሱ በክርስቶስ አማካይነት ከራሱ ጋር አስታረቀን፤ የማስታረቅንም አገልግሎት ሰጠን፤ 19 እግዚአብሔር በክርስቶስ ዓለምን ከራሱ ጋር ሲያስታርቅ የሰዎችን በደል አይቈጥርባቸውም ነበር፤ ለእኛም ደግሞ የማስታረቅ ቃል ሰጠን።🎯 እግዚአብሔር በክርስቶስ ከራሱ ጋር አስታርቆናል። ነገርግን ከክርስቶስ የማስታረቅ ስራ ባሻገር 'ከክርስቶስ የጎደለውን እኛ እንድንፈጽም' እግዚአብሔር የማስታረቅን ቃል በእኛ አኖረው። 🎯 የሚመስለው የሌለው ራሱን ለአሕዛብ ሁሉ የሚያሳውቀው እና የሚገልጠው እግዚአብሔር ለሌሎች እንድንጸልይ ዕድልን ሰቶናልና...ከሐምሌ 6-12 ድረስ በ10/40 መስኮት ላሉ የሕዝብ ክፍሎች እንፀልያለን።🙏 👉 በመሆኑም ለሚከተሉት ዋነኛ ሀይማኖት ተከታዮች የምንጸልይ ይሆናል፦ ⓵ Tribal 📿 religions 📌 ለጎሳ እምነት ⓶ Hinduism 👳♂️ 📌 ለሒንዱ እምነት ተከታዮች ⓷ Un-religious peoples 📌 ሀይማኖት የለሽ ሰዎች ⓸ Muslims 🕋 📌 ለእምስልምና እምነት ተከታዮች ⓹ Buddhism ☸️ 📌ለቡዲስም እምነት ተከታዮች ...በምልጃ ጸሎት በእግዚአብሔር ፊት የምንቀርብ ይሆናል። ☀️ሐምሌ 6-12 (ከሰኞ-እሁድ) ☀️ዛሬ ከምሽቱ 3:00-4:00 እንገናኝ።
"Notify Me" የሚለውን button click🤏 አድርጉት👉@Kekalu_Maid👈 #ቅድሚያ_ላልተደረሱት #ለ10_40_እፀልያለሁ #Little_Update
322
" የመስቀል ሞት በጥንቱ ዓለም ከሁሉ የከፋ የውርደትና የሥቃይ ሞት ነው። በደረጃ ብናስቀምጣቸው ፣ በመስቀል ላይ ከመሞት ቀጥሎ ያለው ሁለተኛው አስከፊ ቅጣት በእሳት ተቃጥሎ መሞት ነው። በሮማውያን ግዛተ ዐፄ ውስጥ ሦስተኛው አስከፊ የሞት መንገድ ለአውሬ መሰጠት እና የራስ መቆረጥ ነው። በዚህ መልኩ ሰዎች ለአራዊት የሚወረወሩት ብዙኃንን ለማዝናናት ሲፈለግ በመሆኑ፣ ሕዝባዊ በዓላት ሲታቀዱ እና ለዚህ የተዘጋጁ አራዊት ሲኖሩ ይፈጸማል። 👐 መስቀል ግን ከሁሉም የሞት መንገዶች በአዋራጅነቱና በአሰቃይነቱ ይከፋል‼️"
📝ጳውሎስ ፈቃዱ
#የተሰቀለው📖
@Kekalu_Maid
322
Repost from ከቃሉ ማዕድ
2 ጴጥሮስ 3:9 9 ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።💥አስፈሪው ሃይማኖታዊ የዓለም ክልል💥 🔆 በብዙ የዓለም ክፍሎች ያልተደረሱ ሕዝቦች ከኢየሱስ ተከታዮች ጋር የሚገናኙበት ያልተቋረጠ ዕድል አላቸው። ሆኖም እነዚህ ያልተደረሱ ሕዝቦች በብዙ የተከማቹትና ከክርስቶስ ተከታዮች ጋር ለመገናኘት ያላቸው ዕድል አናሳ የሆነበት የዓለም ክፍል አለ። ይህም የዓለም ክፍል 10/40 መስኮት በመባል ይታወቃል። ይህ ጂኦግራፊያዊ የአሰላለፍ መስመር ከምዕራብ አፍሪካ ተነስቶ መካከለኛው ምስራቅ አቋርጦ እስከ እስያ ደረስ የሚዘልቅ ነው። ይህ መስመር በአብዛኛው የአለማችንን ታላቅ የሃይማኖት ክፍል ተከታዮችን ማለትም ሙስሊሞችን፣ ሂንዱዎችንና ቡድሂስቶችን የሚጨምርና የሚያጠቃልል ነው። በአጠቃላይ ሲታይ እነዚህን ሕዝቦች በወንጌል ለመድረስ አመቺ የሚባሉት በብዛት ባለው የዓለም ክፍል የሚገኙ ባህል አቀፍ የወንጌል ሠራተኞች ናቸው። እነዚህ የወንጌል ሠራተኞች ከመልክዓ ምድር፣ ከኢኮኖሚ፣ ከቋንቋም ሆነ ከባህል አንጻር ሲታይ ቅርበት ያላቸው ናቸው። 📌 እነዚህ በጥቂቱ በተደረሱ ሕዝቦች መካከል የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ከአንድም አማኝ ጋር ሳይገናኙና ስለድነት ሳይሰሙ ዕድል ሳያገኙ ኖረው ያልፋሉ። እነዚህ ሰዎች ወንጌል እንዲሰሙ ለማድረግ የወንጌል ሠራተኞች እንቅፋቶቻቸውን አልፈው ለመድረስ በሚያስችል መልኩ ዝግጁ መሆን አለባቸው። በተለይም ከእነዚህ ሃይማኖቶች ወደ ኢየሱስ የሚመጡ ሰዎች ለባህላቸው በሚስማማና በሚመጥን መልኩ እንዲመለኩ ፍላጎታቸውን ማስተላለፍ ፈቃደኝነት ሊኖራቸው ይገባል። 📌እነዚህን እና መሰሎች በሚገባ ያልተደረሱ ሕዝቦች በአብዛኛው ፦ 👉 ድሆችና ጉዳተኞች 👉 የማህበረሰብ ልማት የሌላቸው 👉 ማህበራዊ ፍትህ የተጓደለባቸው 👉 የተሰደዱና የታሰሩ ሰዎች የሚበዙበት 👉ህገወጥ የሰዎች ዝውውር የሚበዛበት 👉የሴቶች እየያዝ ኢ-ፍትሐዊ የሆነበት እና ለችግር የተጋለጡ ልጆች የሚበዙበት፤ ስፍራ በመሆኑ አለማቀፋዊ አስፈሪ ስፍራ እንዲሆን አድርጎታል። 💥 ምን ያህሎቻችን ለእነዚህ ሕዝቦች እንፀልያለን❓ በዚህ አከባቢ የሚገኙ ፦ THUMB(Tribal belief,Hinduism, Un-religious, Muslims, Buddhism) በመባል የሚታወቁት የሀይማኖት ክፍሎች ኢየሱስን ሳያውቁ እንዳይሞቱ ልንፀልይ #ስምህ_ይቀደስ ልንል ይገባናል።🙏🙏🙏
ራእይ 7:9 9 ከዚህ በኋላ አየሁ፥ እነሆም፥ አንድ እንኳ ሊቆጥራቸው የማይችል ከሕዝብና ከነገድ ከወገንም ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ነጭ ልብስም ለብሰው የዘንባባንም ዝንጣፊዎች በእጆቻቸው ይዘው በዙፋኑና በበጉ ፊት ቆሙ፤💥የኢየሱስ ስም ይቀደስ። አሜን! #አስር_አርባ_መስኮት #ኢየሱስ_ስምህ_ይቀደስ ¶Follow | Join | Share #ከቃሉ_ማዕድ
322
📌 በክርስቶስ የሆነ ልብ ሁሉ ሚስዮናዊ ነው። ክርስቶስ የሌለበት ልብ ሁሉ የሚስዮናውያን መስክ ነው።
🎯ኒኮላስ ዚንዘርዶርፍ
#Missionary_Quotes
@Kekalu_Maid
322
ብስለት ማለት፦ የእኛን ደካማ ጎንና የሰውን ብርቱ ጎን #ማመን፥ የእኛን ብርቱ ጎንና የሰውን ደካማ ጎን ደግሞ #መረዳት ወደ መቻል ማደግ ማለት ነው።
💫👉የእኛን ደካማ ጎን ስናምን ልኩን በእኛ ስህተት ለማረም አይቃጣንምና፥ የእድገት መንገድ ላይ መሆናችንን እናረጋግጣለን።
💫👉የሰውን ብርቱ ጎን ስናምን ትግላችንን ሁሉ እኛን ከሰው ሳይሆን ከእኛ ጋር ማወዳደር ይሆንልናል። በሰዎች መካከል ሁሌ የበላይ ለመሆን ከሚጥር ሰው በላይ በበታችነት ስሜት የተጠቃ ሰው የለምና!!!
💫👉የእኛን ብርቱ ጎን ስንረዳ መረባችንን ለመጣል አሳዎቹ የሚገኙበት ቦታ እንደተነገረው ሰው ያህል ደፋር እንሆናለን!!!
💫👉በስተመጨረሻም የሰውን ደካማ ጎን ስንረዳ በሀሜታችን ጣታችንን እነርሱ ላይ ከመጠቆም ይልቅ በጸሎታችን እነርሱን ወደ እግዚአብሔር መጠቆም ያምረናልና በህብረት መኖር እየጣፈጠን ይሄዳል።
ለሁሉም መልሱ መብሰልና ማደግ ነው!🙏
322
"መስቀል☦ የሽንፈት ምልክት ቢሆንም ፣ የኢየሱስ መስቀል ግን የድል ምልክት ሆኗል።የተሰቀለው ጌታ ሕያው ነውና።ትንሣኤና ሕይወትም እርሱ ነውና።"
📖የተሰቀለው 📖
✍ ጳውሎስ ፈቃዱ
¶Follow | Join | Share @Kekalu_Maid
322
"ማክስ ሎክድ የተባለ ዕውቅ ፀሐፊ የልጁን መልክ መምሰል በሚል መፅሐፋቸው አንድ ምናባዊ ጥያቄን ያቀርባሉ። አንድ ቀን ለ24 ሰዓታት ኢየሱስ አንተን መሆን ቢፈልግ እና ሁሉ ነገር እንዳለ ሆኖ ልብ ብቻ ብትቀያየሩስ? ይህ ምን ማለት እንደሆነ በጥያቄዎቹ ሲያብራራ በዚያን ቀን ያንተ ልብ ዕረፍት ወስዶ ህይወትህ በእርሱ ልብ ቢመራስ? የዕለት ባህርይህ ሁሉም የቀኑ ውሳኔዎች በዚህ ልብ ቢንቀሳቀሱ ምን ይፈጠር ይሆን?በዙሪያህ ያሉ ወዳጆችህስ ምን ለውጥ ያዩ ይሆን?በዚያ ዕለት ለማድረግ አቅደህ የነበረውን ሁሉ ታደርገው ነበር? ወደ ያዝካቸው ቀጠሮዎች ታቀና ነበር?ወይስ ልብህን ኢየሱስ ስለያዘው የሚቀየሩ አስተሳሰቦች እና እርምጃዎች ይኖሩ ይሆን? በማለት የልጁን መልክ መምሰል ይህ መሆኑን ያስረዳል።ፊል2:5 በመጥቀስ ሲያብራራ #እርሱ ኢየሱስ እንደማያስብ ማሰብ እራሱ እንደሚያደርግ ማድረግ ነው ይላል። በማስከተልም እግዚአብሔር ባለህበት ሁኔታ ይወድሃል ባለህበት ሁኔታ ግን ሊተውህ አይፈልግም። ኢየሱስንም እንድትመስል ነው የሚፈልገው።"
📖መንፈሳዊ ብስለት📝ማሙሻ ፈንታ(ዶ/ር)#Spiritual_maturity ¶Join | Follow | Share 🚩@Kekalu_Maid
