Law studies ⚖️
Відкрити в Telegram
Welcome to Law studies telegram channel ⚖️ This channel is dedicated to helping law students succeed. ✔️ Simple & clear law notes ✔️ Past exam questions & answers ✔️ Key articles & case summaries ✔️ Exam tips & important topics
Показати більшеКраїна не вказанаКатегорія не вказана
347
Підписники
+224 години
+37 днів
+330 день
Архів дописів
በሌሉበት የተሰጠ ፍርድን ስለማንሳት ✍️
( Setting Aside an Ex _ Parte Judgment )
⚫️ አንድ ሰው መጥሪያ ሳይደርሰዉ ወይም በበቂ ምክንያት ሳይቀርብ ቀርቶ ዉሳኔ ከተላለፈበት ፣ ፍርዱ ተነስቶ ክርክሩ ከዜሮ እንዲጀምር የመጠየቅ መብቱ " የመሰማት መብት " ( Right to be Heard ) አካል ነው ።
⚫️ ፍርዱ እንዲነሳ የሚጠየቅባቸው ምክንያቶች ✍️
ፍርድ ቤቱ ፍርዱን አንስቶ ክርክሩን እንደገና እንዲጀምር ለማድረግ ተከሳሹ ከሚከተሉት ምክንያቶች አንዱን ማሳየት አለበት ፦
👉 መጥሪያው በአግባቡ አለመድረሱን ፦ ለተከሳሹ መጥሪያ በሕግ በተደነገገው መሠረት ( በአካል ፣ በቤተሰብ ወይም በጋዜጣ ) ሳይደርሰዉ ቀርቶ ከሆነ ።
👉 በበቂ ምክንያት መቅረት ፦ መጥሪያው ደርሶት ቢሆንም ፣ በፍርድ ቤት ቀን ለመቅረብ የሚያግድ " በቂ ምከንያት " ካጋጠመዉ ለምሳሌ ከባድ ሕመም ፣ ድንገተኛ አደጋ ወይም ከቁጥጥር ዉጪ የሆነ ምክንያት ።
⚫️ ሂደቱና የጊዜ ገደቡ ✍️
👉 ማመልከቻ ማቅረብ ፦ ተከሳሹ ፍርዱን የሠጠው ፍርድ ቤት ድረስ በመሄድ " በሌለሁበት የተሰጠው ፍርድ ተነስቶልኝ መከላከያዬን ላቅርብ " የሚል ማመልከቻ ማቅረብ አለበት ።
👉 የጊዜ ገደብ ፦ የፍትሐብሔር ጉዳይ ከሆነ ፣ ፍርድ መኖሩን ካወቀበት ቀን ጀምሮ በ 30 ቀናት ዉስጥ ማመልከቻቸውን ማቅረብ ይኖርበታል ።
⚫️ በአጋጣሚ በቁጥጥር ሥር ከዋለ ( በወንጀል ጉዳይ )
ግለሰቡ በሌለበት ተፈርዶበት በኋላ በፓሊስ የተያዘ ከሆነ ፣ ግለሰቡ ለፍርድ ቤቱ በመቅረብ " መጥሪያ አልደረሰኝም ወይም የቀረሁት በበቂ ምክንያት ነው " የሚል ማመልከቻ ያቀርባል ።
⚫️ ፍርድ ቤቱ ምክንያቱን ካመነበት ፣ ቀደም ሲል የሰጠውን ዉሳኔ በማንሳት ክርክሩ ገና ከጅምሩ ( ከክስ ንባብ ጀምሮ ) በድጋሚ እንዲሰማ ያዛል ።
⚫️ በዚህ ጊዜ መከላከያውን የማቅረብ ፣ ምስክሮችን የማሰማት እና ጥያቄ የመጠየቅ ዕድል ያገኛል ።
⚫️ ዓላማው ፦ የፍትህ መጓደልን መከላከል ✍️
ሕጉ ይህን ዕድል የሰጠው ፣ አንድ ሰው ሳይሰማና ሳይከላከል በመፈረዱ የሚደርሰውን የፍትህ መጓደል ለማስቀረት ነው::
#ExitExamProtocols
የ2018 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ሊከተሏቸው የሚገቡ የስነ-ምግባር መመሪያዎች፦
➫ ተፈታኝ ተማሪዎች በመፈተኛ ክፍል ውስጥ የሞባይል ስልክ፣ ሚሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት፣ ሳይንቲፊክ ካልኩሌተር፣ የራስ ያልሆነ መታወቂያ እንዲሁም ማንኛውም አይነት የጦር መሳሪያ ይዘው መገኘት አይችሉም፡፡
➫ ተፈታኝ ተማሪዎች ከ3ዐ ደቂቃ ቀድመው በተመደቡበት ክፍል መገኘት አለባቸው፡፡
➫ ተፈታኞች ከተመደቡበት ክፍል ውጪ መፈተን ውጤት ያሰርዛል፡፡
➫ ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና አስፈጻሚን ትዕዛዝ ማክበር ይጠበቅባቸዋል።
➫ ተፈታኞች የፋይዳ መታወቂያ እንዲሁም ራሳቸውን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
➫ በሌላ ሰው ስም፣ መለያ ቁጥር እና የይለፍ ቃል መፈተን አይቻልም፡፡
የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ አወጣጥ፣ የቴክኒክ እርማትና የሕትመት ሂደት ላይ የተሰጠ አስተያየት
***
በዳንኤል ፍቃዱ / ጠበቃና የህግ አማካሪ/
የፌዴራል ፍትሕ ሚኒስቴር ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ያወጣውን የፕሬስ መግለጫ እና አዲሱን የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ (አዋጅ ቁጥር 1410/2018) ማፅደቅን ተከትሎ በሕግ ባለሙያዎች ዘንድ እየተነሱ ያሉ አወዛጋቢ ጉዳዮችን መነሻ በማድረግ፣ ይህ የባለሙያ ትንተናዊ አስተያየት ከሕግ ማርቀቅ ሥርዓትና ከሕግ እርግጠኝነት መርሆዎች አንፃር ተዘጋጅቷል።
1. ከሕግ አፅዳደቅ በኋላ የሚከናወኑ የአርትኦት ሥራዎች ሕጋዊ ወሰን
ምክር ቤቱ ሕጉን ካፀደቀና ሰነዱ ለኢፌዴሪ ፕሬዚደንት ተልኮ ፊርማ ከተቀመጠበት በኋላ፣ በሕጉ ቁም-ነገር ወይም ይዘት (Substance) ላይ ማሻሻያ ማድረግ በፍፁም አይቻልም። በአሁኑ ወቅት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ ክፍልና በፍትሕ ሚኒስቴር እየተከናወነ ያለው ሥራ (በፍትህ ሚኒስቴር እንደተገለጸው) ምክር ቤቱ ያፀደቀውን የቋሚ ኮሚቴውን የውሳኔ ሐሳብ ከዋናው ረቂቅ ጋር የማዋሃድ (Consolidation) እና ለሕትመት የማዘጋጀት የቴክኒክ ሥራ ነው።
የዚህ የአርትኦት (Editorial Works) እና የቋንቋ ማስተካከያ ሥራዎች ሕጋዊ ወሰን የሚከተሉትን ጉዳዮች ብቻ ያጠቃልላል፦
የሚፈቀዱ የቴክኒክ እርማቶች፦የፊደላት፣ የስርዓተ-ነጥብና የሰዋስው ስህተቶችን ማረም፤ የአንቀጾች ቅደም-ተከተል ሲቀየር የሚመጡ የቁጥር ለውጦችንና የውስጥ ማጣቀሻዎችን (Cross-references) ማስተካከል። እንዲሁም በአማርኛና በእንግሊዝኛ ትርጉሞች መካከል ያሉ የቃል በቃል አለመጣጣሞችን፣ የሕጉን መሠረታዊ ፍቺ ሳይቀይሩ ማረቅ።
የማይፈቀዱ ለውጦች፦ የአንድን ድንጋጌ ሕጋዊ ውጤት፣ መብት፣ ግዴታ ወይም ቅጣት የሚቀይሩ የቃላት ለውጦችን ማድረግ (ለምሳሌ "ይችላል" የሚለውን ወደ "ይገደዳል" መቀየር)። አዳዲስ የወንጀል ዓይነቶችን፣ የስነ-ስርዓት ደረጃዎችን ወይም የፍርድ ቤት የሥልጣን ወሰኖችን መጨመርም ሆነ መቀነስ ሙሉ በሙሉ የተከለከለ ነው።
2. ከምክር ቤቱ የውሳኔ ሐሳብ ጋር ያለውን መጣጣም ስለማረጋገጥ
ሕጉ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ሲወጣ፣ የተደረጉት የቴክኒክ እርማቶች ምክር ቤቱ ካፀደቀው ወሰን ማለፋቸውንና አለማለፋቸውን ለማረጋገጥ ብቸኛው መንገድ የንፅፅር ምርመራ (Comparative Analysis) ማድረግ ነው።
ባለሙያዎች የታተመውን የመጨረሻ አዋጅ ምክር ቤቱ ሕጉን ሲያፀድቅ ከተጠቀመበት የቋሚ ኮሚቴው የውሳኔ ሐሳብ ሰነድ (Committee Report) እና በእለቱ ከተመዘገበው የምክር ቤቱ ቃለ-ጉባኤ (Parliamentary Minutes) ጋር ማነጻጸር ይኖርባቸዋል። በታተመው ሕግና በምክር ቤቱ ውሳኔ መካከል መሠረታዊ የትርጉም ልዩነት ከተገኘ፣ ያ ክፍል ከሥልጣን በላይ (Ultra Vires) እንደተደረገ እርማት የሚቆጠር ሲሆን፤ ስህተቱ በድጋሚ በእርማት መልክ (Corrigenda) በነጋሪት ጋዜጣ ሊታተም ወይም ምክር ቤቱ ማሻሻያ አዋጅ ሊያወጣበት ይገደዳል።
3. ያልታተሙ የረቂቅ ሰነዶችን የመጠቀም ሕጋዊና ሙያዊ ስጋቶች
ምንም እንኳ ምክር ቤቱ ያፀደቀው ሰነድ በእጅ ላይ ቢገኝም፣ በነጋሪት ጋዜጣ ሳይታተም ለሥልጠናም ሆነ ለሙያዊ አገልግሎት መጠቀም ከፍተኛ የሕግ ስጋት ያስከትላል። ፍትሕ ሚኒስቴር በመግለጫው ላይ ይህንን አጠቃቀም ያስጠነቀቀው በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው፦
አንደኛ፦ የሕጋዊነት መርህ (Principle of Legality)
> በኢትዮጵያ ሕግ አወጣጥ ሥርዓት መሠረት፣ አንድ ሕግ አስገዳጅ ሆኖ በሥራ ላይ የሚውለውና ይፋዊ የሕግ መረጃነቱ የሚረጋገጠው በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣ በኋላ ብቻ ነው።
ሁለተኛ፦ የንቃተ-ሕሊና ብዥታ (Cognitive Noise)
> የመጨረሻው የአርትኦት ሥራ ያልተጠናቀቀበትንና ያልተዋሃደውን ሰነድ መጠቀም፣ በቃላት አጠቃቀምና በአንቀጽ ቁጥሮች ላይ አለመጣጣምን ስለሚፈጥር፣ ባለሙያዎች በኋላ ላይ ትክክለኛው የታተመ ሕግ ሲወጣ ድጋሚ ለመማር (Re-learning) እንዲገደዱ ያደርጋል። ይህ ደግሞ በፍትሕ ሥርዓቱ አፈጻጸም ላይ ትልቅ መደናገርን ይፈጥራል።
4. ማጠቃለያና የባለሙያ ምክረ-ሐሳብ
ሁለቱን ተቃራኒ ሐሳቦች (ሕጉ በፍጥነት እንዲወጣ መፈለግንና በጥንቃቄ ታይቶ እንዲታተም መሻትን) ከፍትሕ ሚኒስቴር መግለጫ ጋር አዋህደን ስንመዝነው፣ የሚከተለው ሙያዊ መደምደሚያ ላይ እንደርሳለን፦
ይህ አዲስ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ እጅግ ግዙፍ፣ የሰው ኃይልና የተቋማት ማሻሻያን የሚጠይቅ፣ እንዲሁም በርካታ ደንቦችና መመሪያዎች (Secondary Laws) እንዲወጡ የሚያስገድድ ነው። በመሆኑም፣ የተጠቃለለና ያለቀለት ሰነድ ሳይዘጋጅ ዋናውንና የማስተካከያ ሰነዱን ለየብቻ አቅርቦ ማፅደቅ የፈጠረውን ብዥታ ለማጥፋት፣ አሁን እየተሠራ ያለው የቴክኒክ ውህደት ሥራ ወሳኝና የማይታለፍ ደረጃ ነው።
ሕጉ ባለበት ሁኔታ በጥደፊታ ታትሞ ቢወጣ ኖሮ፣ ለተለያዩ አላስፈላጊ ትርጉሞች በር በመክፈት የሰበር ሰሚ ችሎትን እንደሚያጨናንቅና የሕግ ማሻሻያን በአጭር ጊዜ ውስጥ የግዴታ እንደሚያደርግ መገመት አያዳግትም። ስለዚህ፣ የሕግ እርግጠኝነትን (Legal Certainty) ለማረጋገጥና ጠንካራ የፍትሕ ሥርዓት ለመዘርጋት ሲባል፣ የምክር ቤቱ የሕግ ክፍል ሥራውን በጥንቃቄ አጠናቆ ሕጉ በነጋሪት ጋዜጣ (ወይም በብርሃንና ሰላም) ታትሞ እስኪወጣ ድረስ በትዕግሥት መጠበቁ ሙያዊ ግዴታና ተገቢ አካሄድ ነው።
#EthiopianLaw #CriminalProcedure #EvidenceLaw #MinistryOfJusticeEthiopia #Proclamation1410 #LegalAnalysis #LawReformEthiopia #LegislativeProcess
+3
ምክር ቤቱ የአየር አገልግሎት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጸደቀ
---------------------
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ በካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባው ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያደረገቻቸውን የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል፡፡
የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ፈትሂ ማሕዲ ( ዶ/ር ) የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆችን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳቦች ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡
የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆቹ ኢንቨስትመንትን በማሳብና የአየር ትራንስፖርት መዳረሻዎችን በማስፋት ለአገራችን የአየር ትራንስፖርትና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ያላቸውን ሚና ወሳኝ መሆኑን ምክትል ሰብሳቢው አስረድተዋል፡፡
ከአየር አገልግሎት ስምምነቶቹ መካከል በኢትዮጵያ መንግሥትና እና በሴራሊዮን ሪፐብሊክ መንግሥት በኩል የተፈረመው አንዱ ሲሆን ስምምነቱ ለአየር መንገዶች ወደ ተመረጡ መዳረሻዎች በቀጥታ ለማረፍና ምቹ የአቪዬሽን አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
ይህን የአየር አገልግሎት ረቂቅ አዋጅ ምክር ቤቱ አዋጅ ቁጥር 1417 /2018 አድርጎ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡
በመቀጠል በአንጎላ ሪፐብሊክ ፤ እና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል የተፈረመው የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጅ ለምክር ቤቱ የቀረበ ሲሆን ስምምነቱ በአገራቱ መካከል ያለውን ረዥም ዘመናት ያስቆጠረ ግንኙነት ለማሳደግ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የተከበሩ ፈትሂ ማሕዲ( ዶ/ር ) አስረድተዋል፡፡
በተመሳሳይ ምክር ቤቱ ይህን ረቂቅ አዋጅ፤ አዋጅ ቁጥር 1418 /2018 አድርጎ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡
ሙሉ ዜናው 👇👇👇
https://www.facebook.com/share/p/1Bbxft3jcC/
Repost from Exit Exam Support - Verification
Please note the following:
1) Gender mismatch will not be an issue as long as the other fields are correct. You can proceed with verification even if the gender does not match.
2) Phone number mismatch will not be an issue. If you submitted an incorrect phone number but the other details are correct, you may continue with the verification.
3) Minor spelling errors are acceptable. As long as there is no major name mismatch, you can proceed with verification.
4) If your record is not found using the FAN number, please try the second option (Bio Data). If the record is still not found, contact your institution for the corrected.
Video guide :https://youtu.be/L1QsX82yyZ8
ህግ ማጥናት ለሚፈልጉ ሰዎች አስፈላጊው ሁኔታ ምንድነው?
#በኢትዮጵያ ህግ እና የህግ ትምህርት አውድ ህግ ማጥናት ማለት የፍርድ ቤት ክርክር መማር አይደለም። ህግ ማለት ፍትሕን፣ ስርዓትን፣ መብትን፣ ግዴታን እና ማህበራዊ ሰላምን የሚጠብቅ ስርዓት ነው። ስለዚህ ህግ ለማጥናት የሚፈልግ ሰው በትዕግስት፣ በሥነ-ምግባር፣ በአስተሳሰብ ጥራት እና በእውነት ፍቅር መዘጋጀት አለበት።
1. የህግ ትምህርት ቤት ዋና አላማ
የህግ ትምህርት ቤት ዋና አላማ ፍትሕን የሚያከብሩ ባለሙያዎች ማፍራት፤ህግን በትክክል የሚተረጉሙ ሰዎች ማዘጋጀት፤የህዝብ መብትን የሚጠብቁ ባለሙያዎች ማፍራት፤ሀገር ውስጥ የህግ የበላይነት (Rule of Law) ማጠናከር እና ማህበራዊ ግጭቶችን በህግ መፍታት ነው።
#ምሳሌ፦ አንድ ዳኛ ህጉን በትክክል ካልተረዳ ንፁህ ሰው ሊቀጣ ይችላል።ስለዚህ የህግ ትምህርት አላማ የሰው መብትን ከስህተት መጠበቅ ጭምር ነው።
2. ህግ ለማጥናት የሚያስፈልጉ መርሆች
(ሀ). ትዕግስት
ህግ ብዙ ንባብ ይፈልጋል።ህጎች፣ ፍርዶች፣ መፅሐፍት እና ህጋዊ መርሆች በብዛት ይነበባሉ።
ምሳሌ፦አንድ ጉዳይ ለመረዳት የፍትሐ ብሔር ህግ፤የወንጀል ህግ
የማስረጃ ህግ፤የፍርድ ሥነ-ሥርዓት ህግ፤የወንጀል ስነ ስርዓት ህግ፤ ሌሎችም ጠቅላላ እና ልዩ ህጎችን እንዲሁም ደንቦችን ማወቅ እና ሁሉንም አንድ ላይ ማንበብ ሊያስፈልግ ይችላል።
(ለ). እውነትን መውደድ
#ጥሩ የህግ ባለሙያ ማለት ውሸትን በቃላት የሚያሸንፍ ሰው አይደለም።እውነትን በህግ የሚያረጋግጥ ሰው ነው።
#ምሳሌ፦ጠበቃ ደንበኛው በውሸት ሰነድ እንዲጠቀም ቢጠይቀው፣ በህግ ሥነ-ምግባር እሱን መከልከል ይጠይቃል።
(ሐ). የመተንተን ችሎታ
ህግ ማለት “ምን ተፈፀመ?” ብቻ አይደለም።“ለምን ተፈፀመ?” “ህጉ ምን ይላል?” “ፍትሕ ምን ይጠይቃል?” ብሎ ማሰብ ነው።
#ምሳሌ፦ አንድ ሰው ሰውን ቢመታ፣ራሱን ለመከላከል ነበር
በድንገት ነበር? ሆን ብሎ ነበር? ይህ ሁሉ በህግ ትርጉም ይለያያል።
3. የህግ ትምህርት ጥቅሞች
(ሀ). የመብት ግንዛቤ ይሰጣል
ህግ የተማረ ሰው መብቱን እና ግዴታውን ያውቃል።
#ምሳሌ፦ ህግ የተማረ ሰው ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ንብረቱ ሲወሰድ መቃወም እንዳለበት ያውቃል።
(ለ). የመናገር እና የክርክር ችሎታ ያዳብራል
#የህግ ተማሪዎች ማስረጃን በሥርዓት ማቅረብ ይማራሉ።
#ምሳሌ፦በፍርድ ቤት፣ “እኔ እንዲህ አስባለሁ” ብቻ አይበቃም።
ማስረጃ እና የህግ ድጋፍ ያስፈልጋል።
(ሐ). የማህበረሰብ ክብር ያመጣል
ጥሩ የህግ ባለሙያ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ እምነት ያገኛል።
(መ). የስራ እድል ያሰፋል
.ጠበቃ
.ዳኛ
.ዐቃቤ ህግ
.የህግ አማካሪ
.የሰብዓዊ መብት ባለሙያ እና የዲፕሎማሲ ባለሙያ ወዘተ መሆን ይቻላል።
4. የህግ ትምህርት ችግርና ጉዳቶች
(ሀ). ከፍተኛ ጫና
ብዙ ንባብ፣ ምርምር እና ክርክር ይፈልጋል።
#ምሳሌ፦ አንድ የፍርድ ቤት ውሳኔ ለመረዳት 50 ገፅ በላይ ማንበብ ሊያስፈልግ ይችላል።
(ለ). የሥነ-ምግባር ፈተና
አንዳንድ ጊዜ ገንዘብ ወይም ግፊት ህግን እንዲጣስ ሊያደርግ ይችላል።
#ምሳሌ፦ ሰው የሀሰት ምስክር እንዲያቀርብ ቢጠይቅህ፣ የህግ ሙያ ሥነ-ምግባር እምቢ ማለትን ይጠይቃል።
(ሐ). ሰዎች ሁሉ ህግን አይወዱም
አንዳንድ ጊዜ እውነትን መናገር ጠላት ሊያበዛ ይችላል።
#ምሳሌ፦ ህገ-ወጥ ነገርን ስትቃወም አንዳንድ ሰዎች “አስቸጋሪ ሰው” ሊሉህ ይችላሉ።
5. ህግ ማጥናት ለሚፈልጉ ሰዎች ዋና ምክሮች
①. ንባብን ልመዱ
በየቀኑ ማንበብ ካልቻላችሁ ህግ ከባድ ሊሆን ይችላል።
②. ጥያቄ መጠየቅን አትፍሩ
ጥሩ የህግ ተማሪ “ለምን?” ብሎ ይጠይቃል።
③. ህግን ለፍትሕ ተጠቀሙበት
ህግ ሰዎችን ለማስፈራራት ሳይሆን ለመጠበቅ ነው።
④. ሥነ-ምግባራችሁን ጠብቁ
የህግ ባለሙያ ስም በአንድ ስህተት ሊበላሽ ይችላል።
⑤. ፍትሕን ከገንዘብ በላይ አድርጉ
#ህግ ትልቅ ኃይል አለው፤ ነገር ግን ያ ኃይል በእውነት እና በሥነ-ምግባር ሲመራ ብቻ የተከበረ ይሆናል።
ማጠቃለያ
#ህግ ማጥናት ቀላል መንገድ አይደለም።ነገር ግን ፍትሕን ለማገልገል፣ መብትን ለመጠበቅ፣ ማህበረሰብን ለማሻሻል ከፍተኛ ዕድል ያለው ሙያ ነው።
#ጥሩ የህግ ባለሙያ ማለት ህግን ብቻ የሚያውቅ ሰው ሳይሆን፣ ፍትሕን የሚያከብር ሰው ነው።
መኪና በውክልና ለምትሻሻጡ ወገኖች:-
==============
የተሽከርካሪ ሽያጭ ውል ህጋዊነት እና ማስረጃ አቀራረብ በሰበር መ/ቁ 283524 በቀን 27/05/2018 ዓ.ም በሰጠው ውሳኔ
መኪና ሲገዙ ወይም ሲሸጥ በውልና ማስረጃ በኩል ሳያረጋግጡ በመንደር ውል መደረጉ ያለው እጣ ፈንታ በተለይም ግለሰቡ (ተጠሪ) ከአንድ ሻጭ (አመልካች) ጋር የመኪና ሽያጭ ውል ተፈራርመው፣ ከፊል ክፍያ ፈጽመውና መኪናውን ተረክበው ለዓመት ያህል ሲጠቀሙ ይቆያሉ ። ነገር ግን ሻጭ መኪናውን በሌላ ቁልፍ ከፍተው በመውሰድ "አልሸጥኩም፣ እንዲያስተዳድሩልኝ ውክልና ነው የሰጠኋቸው" በማለት በመካድ ተከራክረዋል ። በሰበር ሰሚ ችሎትም መኪና እንደ ተራ ንብረት ሳይሆን እንደ "ልዩ ተንቀሳቃሽ ንብረት" የሚቆጠር በመሆኑ፣ ዝውውሩ በህግ ፊት እንዲጸና በሚመለከተው የመንግስት አካል ዘንድ መመዝገብና መረጋገጥ አለበት ። በተጨማሪም የመኪና ሽያጭ መኖሩን ለማረጋገጥ በሚመለከተው አካል የተረጋገጠ የሽያጭ ሰነድ ማቅረብ እንጂ በሰው ምስክር ብቻ ማረጋገጥ የማይቻል ስለመሆኑ ተወስኗል
ይገባል፤ ይህም ችሎቱ የተደነገጉትን መስፈርቶች በተመሳሳይ ሀረጎች/ቃላት የሚገባ ስሕተት ብቻ ሊጨምር እንደሚችል የሚያረጋግጥ መርህ ነው።
5. የልዩነቶቹ ሕጋዊና ተግባራዊ አንድምታዎች
5.1. የልዩ ህግ መርህና የተግባራዊ ቅድሚያ
በሕግ ትርጓሜ ጠቅላላ መርሆዎች መሠረት፣ ልዩ ሕግ (lex specialis) በአጠቃላይ ሕግ (lex generalis) ላይ ቅድሚያ ይኖረዋል። ስለዚህ በወንጀል ጉዳዮች ላይ የሚቀርቡ የሰበር አቤቱታዎች በዋነኛነት በወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ አንቀጽ 345 ላይ መመሥረት የሚገባቸው ሲሆን፣ በሲቪል፣ ንግድና አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ግን የፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጅ አንቀጽ 2(4) ተግባራዊ ይሆናል። ሆኖም፣ የፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጁ ራሱ "የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ሁሉንም ጉዳዮች የሚመለከት" መዋቅራዊ ሕግ በመሆኑ፣ የሁለቱ ድንጋጌዎች መስተጋብር አንዳንድ ጥያቄዎችን ያስነሳል። ለምሳሌ፣ አንድ የወንጀል ሰበር አመልካች የፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጁ ላይ ብቻ የተደነገጉ መስፈርቶችን - ለምሳሌ "የአስተዳደር ድርጊት" የሚለውን - መጥቀስ ይችል ይሆን ወይ? ወይም በወንጀል ጉዳይ ላይ የተሰጠ የሰበር ቅድመ-ውሳኔ በፍትሃ ብሔር ጉዳዮች ላይ አስገዳጅ ሊሆን ይችል ይሆን ወይ? የመሳሰሉት ጥያቄዎች በወደፊት የሰበር ችሎቱ ስነ ህግና አሰራር (jurisprudence) ምላሻቸውን የሚያገኙ ጥያቄዎች ናቸው።
5.2. የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ሚዛን
የወንጀል ስነ ስርዓት እና የማስረጃ ሕግ በተራ ቁጥር ሦስት ስር "የወንጀል ሕግ መርሆዎች መጣስ" ድንጋጌ ብቻውን አስፈላጊ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ድንበር ሆኖ ያገለግላል። ይህ ድንጋጌ የሕጋዊነት መርህ፣ የተከሳሽ ጥቅም/መብት መከበር መርህን፣ ለአንድ እና ለተመሳሳይ ጉዳይ በድጋሚ ያለመከሰስና ያለመቀጣት መርህ፣ እንዲሁም የማስረጃ መመዘኛ መርሆዎች ሲጣሱ ለሰበር ብቁ መሆኑን የሚያረጋግጥ መሆኑን ግልጽ ያደርጋል። በዚህም ምክንያት የወንጀል ስነ ስርዓት እና የማስረጃ ሕጉ የሰብዓዊ ነፃነት ጥበቃን ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ያስቀመጠና ችሎቱም ጥልቅ መርመራ እንዲያደርግ የህግ ማዕቀፍ የሚሰጥ መሆኑ ይታያል።
5.3. የፍርድ ቤቶች ተግባራዊ ሂደት
ይህ ድርብ የሰበር ሥርዓት (dual-track cassation system) በተግባር ሲታይ የራሱ የሆኑ ችግሮችን ይዞ ይመጣል። በመጀመሪያ ደረጃ ጠበቆች በትክክል የጉዳዩን ዘርፍ መለየትና አግባብነት ያለውን ድንጋጌ መጥቀስ ይኖርባቸዋል፤ ይህ ደግሞ የሕግ ሙያዊ ጥንቃቄንና ጥልቅ ግንዛቤን ይጠይቃል። በተጨማሪም፣ ሰበር ችሎቱ ራሱ በተለያዩ ድንጋጌዎች ላይ ወጥ የሆነ ትርጓሜ መስጠት ይኖርበታል፤ አለበለዚያ የሕግ ትርጓሜ ግጭት ሊፈጠር ይችላል። በመጨረሻም የሕግ አስተማሪዎች ሁለቱን የህግ ማዕቀፎች በሚያነፃፅር መንገድ ማስተማር የሚገባቸው ሲሆን፣ ይህም ተማሪዎች የሁለቱን የህግ ማዕቀፎችች ጥቃቀን ልዩነቶች በደንብ እንዲረዱ ለማድረግ አስፈላጊ ነው።
5.4. የሕግ ማሻሻያ አስፈላጊነት
ከላይ የተገለጹት ጉዳዮች ሕግ አውጪው የተለያዩ ማሻሻያዎችን እንዲያደርግ የሚጠይቁ ናቸው። በመጀመሪያ የሁለቱ የህግ ማዕቀፎች ድንጋጌዎች ጥቅል የመግቢያ ልኬት ቋንቋ ማለትም “ፍትህን የሚያዛባ” (grossly distresses justice) እና "በሕግ ሥርዐቱ ላይ መናጋት የሚፈጥር"(disrupt the legal system) የሚሉትን ማመሳሰል ይገባል። በተጨማሪም የ"ተመሳሳይነት መስፈርት" በሁለቱም የህግ ማዕቀፎች ላይ በግልጽ ማስቀመጥ የሕጋዊ እርግጠኝነትን የሚያሳድግ ሲሆን፣ የፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጁ ስር ያሉ መስፈርቶች በወንጀል ስነ ስርዓት እና ማስረጃ ህጉ ውስጥ ከተቀመጡት መስፈርቶች ውስጥ የተግባራዊነት ሁኔታን በማብራራት ድንጋጌ ማስተካከል ለድርብ-ሰበር ሥርዓቱ ግልጽነት ወሳኝ ጉዳይ ነው የሚል እምነት አለኝ።
6. ማጠቃለያና ምክረ-ሀሳቦች
ከላይ እንዳየነው ህጎቹ ተመሳሳይ የሆኑ መስፍርቶችን የተጠቀሙበት አጋጣሚ አለ፡፡ ሁለቱም ህጎች በሕገ-መንግሥት ጥሰት፣ በተሳሳተ የሕግ ትርጓሜ፣ በጭብጥ ስሕተት፣ በዳኝነት መከልከል፣ በፍርድ አፈጻጸም ስሕተትና በሥልጣን ጉድለት ላይ የጋራ መሠረት ያላቸው መሆኑን ሰነዶቹ ያሳያሉ። በሌላ በኩል በተወሰኑ መስፈርቶች ላይ ልዩነት የሚያሳዩ ሁነው ይታያሉ፤ የፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጁ የአስተዳደር ሕግን ሲጨምር፣ የወንጀል ስነ ስርዓት እና የማስረጃ ሕጉ የወንጀል መርሆዎችን፣ የተዛባ ትርጓሜን እና የሥልጣን ክፍፍልን ያካተተ ሁኖ ይገኛል። ከዚህም በተጨማሪ ህጎቹ ወደ ሰበር የክርክር ሂደት የመግቢያ ልኬት የቋንቋ ልዩነት የሚያሳዩ ሁነው ይገኛሉ፡፡ የፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጅ "ፍትህን በጉልህ ማዛባት" የሚል ሀረግ ሲጠቅም አዲሱ የወ/መ/ስ/ስርዓትና የማስረጃ ህጉ ደግሞ "በሕግ ሥርዐቱ ላይ መናጋት መፍጠር" የሚለውን ሀረግ ያስቀመጠ ሲሆን እነዚህ ሁሉት ወደ ስርዓቱ መግቢያ ልኬቶች የተለያየ የፍልስፍና አቅጣጫን የሚያመለክቱ ናቸው። ህጎች ከዝርዝር መስርቶቹ ሕጋዊ ባህሪ አንፃር ሲታዩ ሁለቱም ዝርዝሮች አመላካች (indicative) እንጂ አሳሪ (exhaustive) አለመሆናቸውን ያረጋግጣል፤
የ"መሠረታዊ የሕግ ስሕተት" ፅንሰ-ሀሳብ የኢትዮጵያ የሰበር ሥርዓት ልብ ነው ለማለት ይቻላል። ከላይ በወፍ በረር የታየው የሁለቱ ህጎች ሂሳዊ ትንታኔ የሚያሳየው፣ ይህ ጽንሰ-ሀሳብ በዝግመተ-ለውጥ ላይ ያለ ሕጋዊ ግንባታ መሆኑን ነው። የሕግ አውጪው፣ የፍርድ ቤቶችና የሕግ ማህበረሰቡ ጥምር ጥረት የሰበር ሥርዓቱን ሕገ-መንግሥታዊ አላማ ማለትም የሕግ ትርጓሜ ወጥነት ማረጋገጥና የፍትህ መሠረታዊ መዛባቶችን ማረም፣ ለማሳካት አስፈላጊ ሲሆን፣ ድርብ-ሰበር ሥርዓቱ ውስብስብነት ሲኖረው የእያንዳንዱ የሕግ ዘርፍ ልዩ ባህሪን ለማስተናገድ የተቀረጸ ሕጋዊ ምላሽ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል የሚል እምነት አለኝ።
ማስታወሻ (Disclaimer)
ይህ ጽሑፍ ለትምህርታዊና ለሕግ-አካዳሚካዊ የውይይት ዓላማ ብቻ የተዘጋጀ ሂሳዊ ትንታኔ እንጂ የሕግ ምክር (legal advice) ወይም የፍርድ ቤት መመሪያ አይደለም። ትንታኔው የተመሠረተው በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁ. 1234/2013 አንቀጽ 2(4) እና በወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ አንቀጽ 345 ፊደላዊ ይዘት ላይ ሲሆን፣ የተወሰኑ የፍርድ ቤት ቅድመ-ውሳኔዎችን፣ የሕግ ጽሑፎችንና ዝርዝር የግብረ-መልስ ማጣቀሻዎችን ማካተት ይገባ ነበር። በማንኛውም ተግባራዊ የሰበር አቤቱታ ወይም የሕግ ሙግት ላይ የተመረጠ የሕግ ባለሙያ ማማከር አስፈላጊ መሆኑን አይርሱት!!
በቀጣይ ፅሁፍ አዲሱ የወንጀል ስነ ስርዓት እና የማስረጃ ህጉ ከሰበር ስነ ስርዓት መመሪያው ቁጥር 17/2015 ጋር ያለውን አንድነትና ልዩነት እንዲሁም ተግባራዊ አፈፃፀሙን ለማቅረብ ይሞክራል!
Credit to Elias Kassa
አንድ ተከሳሽ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎለት ክስ የቀረበበት ስለመሆኑ እውቋል የሚል ግምት ሊወሰድ የሚገባው አገር አቀፍ ስርጭት ባለው ጋዜጣ ጥሪ የተደረገለት መሆኑ በተረጋገጠ ጊዜ እንጂ በአንድ ክልል ብቻ ተደራሽ በሆነ ጋዜጣ ብቻ ጥሪ መደረጉን መጥሪያ እንዳደረሰው ማረጋገጫ አድርጎ በመውሰድ እና መጥሪያ ደርሶታል የሚል ግምት በመውሰድ ጉዳዩን ተከሳሹ በሌለበት አይቶ ውሳኔ መስጠት በሕገ-መንግሥቱ ለተከሰሱ ሰዎች የተረጋገጠላቸውን መሠረታዊ መብት የሚጥስ ስለመሆኑ ።
@የሰ/መ/ቁ፦ 173967 ቅፅ.24
🇫🇮 Traineeship Opportunity: Embassy of Finland in Addis Ababa 🇪🇹
Are you a proactive student or recent graduate? Gain first-hand experience in diplomacy and development!
⏳ Duration: 6 months (Starting June 2026)
📍 Location: Addis Ababa (Must currently reside in Ethiopia)
🚀 Key Responsibilities:
• 🤝 Support AU partnership & diplomatic duties
• 📝 Political, economic, and humanitarian reporting
• 📱 Social media & communications
• 📅 Organizing high-level visits & events
• 🔍 Analytical research & media monitoring
🎓 Eligibility & Skills:
• 🎓 Student/Grad in IR, PolSci, Econ, Law, or Comms
• 🗣️ Excellent English (written & spoken)
• 🌍 Ability to thrive in a multicultural team
• 💡 Strong analytical & organizational skills
📩 How to Apply:
Submit your CV, Cover Letter (with salary expectation), and 3 References in English to:
📧 rekry.add@gov.fi
⏰ Deadline: May 24th, 2026
Step into the world of international affairs! 🌍✨
Success, According to Billionaires:
• Warren Buffett: It's consistency
• Elon Musk: It's bold risks.
• Jeff Bezos: It's long-term thinking,
• Richard Branson: It's having fun.
• Bill Gates: It's persistence
• Steve Jobs: It's vision.
• Mark Zuckerberg: It's building connections
• Ray Dalio: It's learning from mistakes
• Larry Page: It's relentless curiosity.
• Jack Ma: It's never giving up
Some times we need motivation
@Law8studies
