The Legal Oracle(Ye_Hig Mahider)
Відкрити в Telegram
Official channel of Almaw Wolie https://www.linkedin.com/in/almaw-wolie-82775183?utm_source=share_via&utm_content=profile&utm_medium=member_android
Показати більшеКраїна не вказанаКатегорія не вказана
1 963
Підписники
+2124 години
+787 днів
+1 25830 день
Триває завантаження даних...
Схожі канали
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
серпень '26
серпень '26
+7
в 0 каналах
липень '26
+1 267
в 7 каналах
Get PRO
червень '26
+651
в 3 каналах
Get PRO
травень '26
+47
в 1 каналах
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 01 серпня | +7 |
Дописи каналу
| 2 | 2018 HoF decisions part 1.pdf | 452 |
| 3 | +1 📌 ለቻናላችን ተከታታዮች በሙሉ የተዘጋጀ መልእክት
ውድ የቻናላችን አባላት፤ በሕግ፣ በታሪክ እና በኪነ-ጥበብ መገናኛ ዙሪያ በምሁሩ ራስል ኤል. ዲዝ የተጻፈውንና በምዕራቡ ዓለም ታሪክ ውስጥ ጎልተው የወጡ ስድስት ታላላቅ የፍርድ ሙግቶችን የሚያጠናውን “Great Trials and the Law in the Historical Imagination” የተሰኘውን ድንቅ መጽሐፍ አጠቃላይ ማጠቃለያ አዘጋጅተን አቅርበንላችኋል።
በመጀመሪያ፣ የነዚህን ታሪካዊ የፍርድ ሙግቶች ዋና ዋና ጭብጦች፣ የሕግ መርሆዎችን እና ባህላዊ ትርጉሞች በአጭሩ ለመረዳት ከላይ የቀረበውን ማጠቃለያ እንዲያነቡ እንጋብዛችኋለን። በመቀጠልም የጉዳዮቹን ጥልቅ ታሪካዊ አውድ፣ የሕግ ፍልስፍናዎችን እና ዝርዝር ትንተናዎች ሙሉ በሙሉ ለማግኘት ከዚህ መልእክት ጋር የተያያዘውን (Attached) ሙሉ መጽሐፍ አውርደው እንዲያነቡ በጥብቅ እናሳስባለን።
Al.W
መልካም የንባብ ጊዜ ይሁንልዎ! | 507 |
| 4 | Creditor_Priority_in_European_Bank_Insolvency_Law_Financial_Stability.pdf | 484 |
| 5 | HUJL-Vol. 10-2026.pdf | 455 |
| 6 | HOF Decision 2018_part_two.pdf | 2 043 |
| 7 | ከላይ የተያያዘው ሰነድ በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 38 መሠረት የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የዕረፍት/የዝግ ወቅት አተረጓጎም፣ እንዲሁም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ማውጣት በሚገባው "ይፋዊ መመሪያ" (Directive) እና በውስጥ "ሰርኩላር ደብዳቤ" መካከል ያለውን የሕግ ደረጃ ልዩነት አጠር ያለ ዳሰሳ ያደረግኩበት ነው። በተለይም በፍርድ ቤቶች የዝግ ወቅት የዜጎች የፍትሕ የማግኘት መብት፣ የአስቸኳይ/ተረኛ ችሎቶች አሠራር እና የዳኞች ተረኝነት ሕጋዊ መሠረት ምን መሆን እንዳለበት አጭር ግላዊ ምልከታ የተደረገበት ስለሆነ አስተያየታችሁን እንድታካፍሉኝ በአክብሮት እጋብዛለሁ!
በተረፈ ከ01/11/2018 ዓ/ም ጀምሮ መልካም እረፍት! | 2 115 |
| 8 | +1 📢 ለተከበራችሁ የቻናላችን ተከታታዮች፣ የሕግ ባለሙያዎች እና ተመራማሪዎች!
በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ታሪክ ውስጥ ለረጅም ዓመታት ሲያካሂድ የነበረውን የንጹሕ ሆኖ የመገመት ሕገ-መንግሥታዊ መብት (አንቀጽ 20(3)) እና በወንጀል ክስ ላይ የሚጠየቀውን "ከምክንያታዊ ጥርጣሬ በላይ" የማስረዳት መስፈርት መስመር ያስያዘውን ታሪካዊ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስገዳጅ ውሳኔ እና በጉዳዩ ላይ በወፍ በረር ያዘጋጀሁትን አጠር ያለ የሕግ ግምገማ ከታች አያይዤላችኋለሁ። ይህ ውሳኔ የሥር ፍርድ ቤቶችን እና የሰበር ሰሚ ችሎትን ነባር የአሠራር ስህተቶች በማረም የሕገ-መንግሥቱን የበላይነት ያረጋገጠበትበመሆኑ፤ ለዳኞች፣ ለዐቃቢያነ ሕግ፣ ለተከራካሪ ጠበቆች፣ ለሕግ ተመራማሪዎች እና ተማሪዎች ሁሉ በእጅጉ አስፈላጊ ሰነድ ብየ አስባለሁ፡፡
ከታች የተያያዙትን ሁለቱንም ፋይሎች በማውረድ እንድታነቡአቸው፣ ለሙያ አጋሮቻችሁ እንድታጋሩአቸው እና አስተያየታችሁን
እንድታካፍሉኝ በአክብሮት እጋብዛለሁ! | 2 057 |
| 9 | 📌 ውድ የቻናላችን ተከታታዮች፤
ቀደም ሲል በሌሎች ሀገራት የሕግ ሥርዓትና በዓለም አቀፍ ደረጃ የዳኝነት ጀግንነት (Judicial Courage) ያለበትን ደረጃ፣ መገለጫዎችና የታዩ ታሪካዊ የፍርድ ውሳኔዎችን የሚዳስሰውን አጠር ላይ ጽሑፍ ማካፈላችን ይታወሳል።
አሁን ደግሞ፣ ያንን መሠረታዊ ዓለም አቀፋዊ እሳቤ ወደ እኛ ሀገር ተግባራዊ እውነታ በማምጣት፣ ጉዳዩን በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት መነጽር በጥልቀት የሚመረምረውንና “በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ውስጥ የዳኝነት ጀግንነት፡ በጎ ምግባር፣ ግዴታ እና የሕገ-መንግሥታዊ ፍትሕ አስፈላጊነቶች” (Judicial Courage in the Ethiopian Legal System: Virtue, Duty, and the Imperatives of Constitutional Justice) በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን የተሟላ የሕግ ጥናት ይዘንላችሁ ቀርበናል።
ይህ አጭር ጽሑፍ፦
- በኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥታዊና የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ለዳኝነት ነጻነት የተሰጡትን መደበኛ ዋስትናዎች፤
- በተግባር ያሉትን የፖለቲካ ጣልቃገብነቶች፣ መዋቅራዊ ድክመቶችና የታሪክ ፈተናዎች፤
- የዳኝነት ጀግንነት በጉልህ የታየባቸውን የፍርድ ቤት ውሳኔዎች (በተለይም በግል ሕግና በንግድ ክርክሮች) እና በሌላ በኩል
ደግሞ በፖለቲካዊና በሰብአዊ መብት ጉዳዮች ላይ የታዩትን ክፍተቶች፤ እንዲሁም
- የሕግ የበላይነትን እውን ለማድረግ ወደፊት ሊወሰዱ የሚገባቸውን የማሻሻያ አቅጣጫዎች በጥልቀትና በስፋት ይተነትናል።
ከቀደመው ዓለም አቀፋዊ ዳሰሳችን ቀጥሎ፣ የዚህ በኢትዮጵያ ሁኔታ ላይ ያተኮረ ምልከታ ከዚህ መልእክት ተያይዞ (Attached) የቀረበ በመሆኑ ሰነዱን በመክፈት እንድታነቡት እንጋብዛለን።
📖 መልካም ንባብ! ጽሑፉን ካነበባችሁ በኋላ ያላችሁን ሙያዊ አስተያየት፣ ጥያቄና ትች | 2 025 |
| 10 | የዳኝነት “ጀግንነት”.docx | 1 771 |
| 11 | ክቡራን ሰላም! ይህን ቻናል ሳብስክራብ ያላደረጋችሁ ሰዎች ሳብስክራይብ አድርጋችሁ ብትጠቀሙ መልካም ነው፡፡ ተደራሽነቱ የሚሰፋውም አንዱ መንገድ ሳብስክራይብ ማድረግ ይመስለኛል፡፡ ጠቃሚ ካልሆነም ምክር ለግሱ! ዋነኛ ዓላማው መረጃ መለዋወጥ ብቻ መሆኑ ይታወቅልኝ! | 994 |
| 12 | An Essay on the New Public Defender for the 21st Century.pdf | 1 040 |
| 13 | Leading Works in Legal Ethics (Julian Webb - Editor).pdf | 1 054 |
| 14 | 136047፣ ጨረታና የጉዳት ኪሳራ.doc | 1 565 |
| 15 | Tax Law in Times of Crisis and Recovery ( etc.).pdf | 1 612 |
| 16 | New_Trajectories_in_Law_Robert_Herian_Data_New_Trajectories_in_Law.pdf | 1 592 |
| 17 | የሰበር ችሎቱ ውሳኔ
የሰበር ሰሚ ችሎቱ የአመልካችን የጥፋተኝነት ውሳኔ ቢያጸናም፣ በካሳው መጠን ላይ የተሰጠውን ውሳኔ ግን እንደሚከተለው አሻሽሎታል፡-
የስም ማጥፋት ጥፋተኝነት መጽናቱ፦ የባንክ መልካም ስም የህልውናው መሠረት በመሆኑ፣ አመልካች ምክንያቱን ሳይገልጽ በጥቅሉ ከባንኩ ዋስትና አንቀበልም ብሎ መጻፉና ለሌሎች አካላት ማሰራጨቱ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2109 መሠረት መልካም ስምን የሚያጎድፍና ተጠያቂነትን የሚያስከትል ተግባር ነው።
የካሳ መጠን መሻሻሉ፦ በደረሰው ትክክለኛ ጉዳት ላይ በቂ ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ የጠየቀውን ሙሉ የካሳ መጠን መፍቀድ ተገቢ ስላልሆነ፣ ጉዳቱ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2102 መሠረት በርትዕ (Equity) ሊሰላ ይገባል። በዚህም መሠረት የካሳው መጠን ወደ 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) ዝቅ እንዲል ተወስኗል።
መሠረታዊ የሕግ ምክንያት (Ratio Decidendi)
በባንክ መልካም ስም ላይ የሚፈጸም ሕገ-ወጥ ድርጊት፦
የፋይናንስ ተቋማት (ባንኮች) ለደንበኞቻቸው በሚሰጡት አገልግሎት ላይ ያላቸው መልካም ስም የህልውናቸው መሠረት ነው። በመሆኑም፣ ያለ በቂና ግልጽ ምክንያት ከአንድ የተወሰነ ባንክ የሚቀርብ የዋስትና ሰነድ ተቀባይነት እንደሌለው በጥቅሉ የሚገልጽ ደብዳቤ መጻፍና ለሌሎች አካላት ማሰራጨት፣ የባንኩን ታማኝነትና ብቃት ጥያቄ ውስጥ የሚጥል በመሆኑ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2109 መሠረት መልካም ስምን እንደማጥፋት ይቆጠራል።
በመልካም ስም መጥፋት ወይም በሌላ ሕገ-ወጥ ተግባር ምክንያት የደረሰን ትክክለኛ የጉዳት መጠን በሒሳብ ወይም በማስረጃ ለይቶ ለማወቅ አስቸጋሪ በሆነበት ሁኔታ፣ ፍርድ ቤቶች ተጎጂው የጠየቀውን ሙሉ የካሳ መጠንመፍቀድ የለባቸውም። ይልቁንም፣ እንዲህ ዓይነቱ ካሳ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2102 መሠረት በርትዕ ሊወሰንና ሊሰላ ይገባል፡፡ | 3 371 |
| 18 | 1)ፍሬ ነገር
ተጠሪዎች በውርስ ያገኙትን ቤት አመልካች ያላግባብ ይዞብኛል በማለት ክስ አቅርበዋል። አመልካች በበኩላቸው በስጦታ ውሉ ላይ ባይፈርሙም፣ ግብር በመክፈልና በመጠገን የሟች አያታቸውን ስጦታ በተግባር መቀበላቸውንና የስም ዝውውሩ ሳይጠናቀቅ ሰጪዋ መሞታቸውን ጠቅሰው ተከራክረዋል።
2. ጭብጥ
- የስጦታ ውል በስጦታ ተቀባዩ ሳይፈረም፣ በድርጊት (ግብር በመክፈል ወይም በመጠገን) ብቻ ስጦታውን መቀበል ይቻላል?
- ስጦታ ሰጪው ከሞተ በኋላ ስጦታውን "ተቀብያለሁ" ማለት በሕግ ረገድ የሚኖረው ውጤት ምንድን ነው?
3. የችሎቱ ውሳኔና ትንተና
- የመቀበል ቃል አስፈላጊነት፦ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2436(1) መሠረት የስጦታ ውል የሚጸናው ተቀባዩ ስጦታውን መውደዱንና መቀበሉን በጽሑፍ ወይም በድርጊት ሲገልጽ ነው።
- ከሞት በኋላ መቀበል አለመቻሉ፦ በፍ/ብ/ሕ/ቁ/ 2436 (2) መሠረት ስጦታ ሰጪው ከሞተ በኋላ "ስጦታውን ተቀብያለሁ" ማለት ሕጋዊ ውጤት የለውም። አመልካች ሟች ከመሞታቸው በፊት ስጦታውን ስለመቀበላቸው የሚያሳይ እምነት የሚጣልበት ድርጊት ወይም ማስረጃ አልቀረበም።
- የስር ፍርድ ቤቶች የፍ/ብ/ሕ/ቁ/ 1723 ለስጦታ ውል ተፈጻሚ ይሆናል ማለታቸውና ፍርድ ቤት በራሱ ተነሳሽነት የክፍያ ግምትን ማንሳቱ ስህተት ቢሆንም፣ ውሳኔው በአንቀጽ 2436(2) መሠረት የጸና በመሆኑ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የለም፡፡
4. Ratio Decidendi
በፍ/ብ/ሕ/ቁ/2436(1) እና (2) መሠረት፣ የስጦታ ውል የሕግ ውጤት የሚኖረው ስጦታ ተቀባዩ ስጦታውን ስለመቀበሉ የሚያሳይ ግልጽ የየጽሑፍ ማረጋገጫ ወይም ድርጊት ስጦታ ሰጪው በሕይወት እያለ ከተከናወነ ብቻ ነው፡፡ ስጦታ ሰጪው ከሞተ በኋላ የሚደረግ የስጦታ መቀበል መግለጫ በሕግ ፊት ዋጋ የለውም። | 2 795 |
| 19 | 1. የጉዳዩ ፍሬ ነገር
አመልካች ያልተከፈለ የስልክ አገልግሎት ክፍያ እንዲከፈለው ተጠሪን ከሰሰ። የበታች ፍርድ ቤቶች "ክሱ የቀረበው የሁለት ዓመት የጊዜ ገደብ ካለፈ በኋላ በመሆኑ በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2024 መሠረት ዕዳው እንደተከፈለ ይቆጠራል" በሚል ክሱን ውድቅ አደረጉት። ሆኖም ተጠሪ በክርክሩ ሂደት "ዕዳውን ከፍያለሁ" የሚል የመከላከያ መልስ በግልጽ አላቀረበም፤ ይልቁንም በሕግ ግምቱ ብቻ ለመጠቀም ተከራክሯል።
2. የተያዘው ጭብጥ
- ባለዕዳው "ዕዳውን ከፍያለሁ" የሚል መከላከያ ባላቀረበበት ሁኔታ፣ የጊዜ ማለፉን ብቻ በመጥቀስ በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2024 ሥር በተደነገገው "ዕዳው እንደተከፈለ ይቆጠራል" በሚለው የሕግ ግምት (Presumption of payment) ተጠቃሚ ሊሆን ይችላል?
3. የሰበር ችሎቱ ውሳኔና ትንተና
- የሕግ ግምቱ ቅድመ-ሁኔታ፦ በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2024 የተደነገገው "ዕዳው እንደተከፈለ የሚቆጠርበት" የሕግ ግምት ተፈጻሚ የሚሆነው፣ ተከሳሹ የተጠየቀውን ዕዳ በተግባር የከፈለ መሆኑን በቅድሚያ ሲከራከርና ይህንኑ መከላከያ አድርጎ ሲያቀርብ ብቻ ነው።
- የዕዳ ክፍያ ክርክር አስፈላጊነት፦ ተጠሪ ዕዳውን መክፈሉን ሳይገልጽ የሁለት ዓመት ጊዜ ማለፉን ብቻ በመጥቀስ በሕግ ግምቱ ተጠቃሚ መሆን አይችልም (በሰ/መ/ቁ 47988 በተሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም መሠረት)።
4. Ratio Decidendi
በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2024 ሥር በተደነገገው "ዕዳው እንደተከፈለ ይቆጠራል" በሚለው የሕግ ግምት ለመጠቀም፣ ተከሳሹ በቅድሚያ ዕዳውን በተግባር ስለመክፈሉ የሚገልጽ መከላከያ ክርክር ማቅረብ አለበት። ዕዳውን ስለመክፈሉ ሳይከራከር፣ ክስ የመመስረቻው ጊዜ ማለፉን ብቻ በመጥቀስ የሕግ ግምቱ ተፈጻሚ አ | 2 639 |
| 20 | Digital_Economy,_Sustainability_and_International_Economic_Law_Lei.pdf | 1 134 |
