የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service
Відкрити в Telegram
.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
Показати більшеКраїна не вказанаКатегорія не вказана
509
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 день
Архів дописів
ከዘጠና አመታት በፊት በነበሩ አዝማሪዎች እና የባህል ሙዚቃ ተጫዋቾች የተቀረጹ የሙዚቃ ስራዎች ከጥንታዊ ፎቶ ግራፎችና ከሙዚቃዎቹ ታሪክ ጋር ተካቶ የተዘጋጀው ልዩ አውደ ርዕይ ተጠናቀቀ።
በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከሚያዝያ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አሥር ቀናት ለተመልካች ክፍት የነበረው ላለፉት ዘጠኝ አስርት ዓመታት በዝምታ ተውጠው የቆዩት የኢትዮጵያ የሙዚቃ ቅርሶች አውደ ርዕይ በስኬት ተጠናቋል።
አውደ ርዕይ በጣሊያን ወረራ ወቅት (ከ1928-1933 ዓ.ም) በአዲስ አበባ በኮሎምቢያ ሪከርድስ አማካኝነት ተቀርጸው የነበሩ በዘመናዊ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ታድሰው የቀረቡ ከ350 በላይ ብርቅዬ የሙዚቃ ቅጂዎች ነበሩ፡፡
የተዘጋጀውን አውደ ርዕይ በተመለከተ አስተያየታቸውን የሰጡት ጎብኚ ሳሙኤል ወርቅዬ እና ደሳለኝ በጋሻው እንዲህ ዓይነቱ አውደ ርዕይ ተዘጋጅቶ በሰው ሀገር ውስጥ የሀገራችን ንብረት ተጠብቆ ዛሬ በዚህ መልክ አውደ ርዕይ ተዘጋጅቶ እንዲታወቅ ማድረጋችሁ "እጅግ በጣም ጥሩ ነው በዚሁ በመቀጠል ለተተኪው ትውልድ የሚሆኑ ስራዎች የተሠሩበት የሸክላ ማጫወቻ ዘፈኖች በዲጂታል አድርጎ በማሰራጨት ለዜጎች በቀላሉ እንዲሰሙ ለማድረግ ያደረጋችሁት ጥረት እጅግ በጣም የሚያስመሰግን በመሆኑ በዚሁ ቀጥሉ በተጨማሪም ታሪኮችን በፎቶግራፍ በማሳየት መልካም ሥራ በመሥራት ላይ እንዳላችሁ ይህ ምስክር ነው" በማለት ምስጋናቸውን ሰጥተዋል፡፡
የኢንስፓርክ ዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰር የሆኑት ሚውዚኮሎጂስት ጂያንፓኦሎ ኪሪያኮ Gianpaolo Chiaraco እነዚህን ከዘጠና አመታት በፊት በኮሎምቢያ ሪከርድስ የተቀዱ ስራዎችን በማሰባሰብና በማደራጀት ከኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ጋር በመቀናጀት በልዩ ሁኔታ ለአውደ ርዕይ እንዲበቃና ለሕዝብ ተደራሽ በማድረጋቸው እንደሀገር ምሥጋናችን ከፍ ያለ ነው፡፡
አውደ ርዕዩን በኦንላይን (በበይነ መረብ) የጎበኙትን ሳይጨምር በአካል በተቋሙ በመገኘት ከአራት ሺህ በላይ ጎብኚዎች ጎብኝተውታል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
ግንቦት 03/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመፃሕፍት አገልግሎት የመጀመሪያውን የሰኞ ንጋት “እንገናኝ እንሰናኝ” መድረክ አካሄደ፡፡
“እንገናኝ እንሰናኝ” የተሰኘው መድረክ የባለሙያዎችን ትስስር ለማጠናከር እና የተቋሙን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፋጠን ታልሞ የተዘጋጀው የሰኞ ንጋት የየኹለት ሳምንት መርሐ ግብር የመጀመሪያ መድረክ በብላቴን ጌታ ህሩይ ወልደሥላሴ አዳራሽ ተካሂዷል።
ከአዲስ አበባ መስተዳድርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚገኙ ተቋማት በመነሳት በተቋሙ መልክና አቋም የተቀረጸ መልካም ተሞክሮ እንደሆነ የገለጹት የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት “ሁላችንም የየራሳችን ልዩነቶች ቢኖሩንም ሃሳቦቻችንን በጥበብ በማገናኘት አንድ በሚያደርገን ተቋም ስር እንድንኖር ያስችለናል” በማለት “እንገናኝ እንሰናኝ” በየሁለት ሳምንቱ የሚቀርብ የሰኞ ንጋት መርሃ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል።
“ናሂሊ” የተሰኘውን መጽሐፍ በዚሁ አዳራሽ አስመርቀው ለንባብ ያበቁት ደራሲ ናትናኤል ከበደ “የቱ ጋር ነው የተለያየነው?” በሚል ርዕስ ሰፊ ገለጻ ለታዳሚያን አጋርተዋል።
ደራሲው ያቀረቡት ዳሰሳ መነሻውን በኦሮሚያ ክልል አድርጎ በጥናትና ምርምር በኢትኖግራፊክ የልብ-ወለድ አጻጻፍ ስልት የከተቡትን “ናሂሊ” የተሰኘ መጽሐፋቸውን መሰረት ያደረገ ሲሆን “እርግጥ ነው ቋንቋችን ይለያያል የፖለቲካ አስተሳሰባችንም እንደዛው ወደ ማህበረሰባችን ወርጄ ሳየው ግን እጅጉን አንድ ነን፤ እንዋደዳለን፤ አንደበታችን ቢለያይም ነፍሳችን አንድ ነው” የሚል መደምደሚያ ያለውን ሃሳብ የያዘ ነው።
ይህ መድረክ የሃሳብ ተግባቦትን በሚያጎልብትና ጥሩ የስራ መነቃቃትን በሚፈጥር መልኩ ባህል ሆኖ እንደሚቀጥል የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት አመላክተዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
“እንገናኝ እንሰናኝ!” የሠራተኞች የሰኞ ንጋት መድረክ ሊጀመር ነው፡፡
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ሠራተኞች የሰኞ ንጋት መድረክ የምክር ሃሳብ በየኹለት ሳምንት በብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ አዳራሽ ከግንቦት 3/2018 ዓ.ም ጀምሮ መካሔድ ይጀምራል፡፡
የዚሁ የምክር ሃሳብ አመንጪው የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት የእንደነዚህ ዓይነት የምክር ሃሳብ መድረክ መዘጋጀቱ በማንኛውም ተቋም ውስጥ የሠራተኛው የሥነ ልቦና ዝግጁነት፣ የቡድን ስሜት እና የመቀራረብ ባህል ተቋማዊ ውጤታማነት ወሳኝ ሚና እንዳለው እና የተቋሙም ሠራተኞች የዕለት ተዕለት የሥራ ጫናን በመቀነስ፣እርስ በእርስ በመተዋወቅ፣ልምድ በመለዋወጥ እንዲሁም የግል ሕይወታቸውን የሚያበለጽጉ ክህሎቶችን እንዲቀስሙ የሚያስችል መሆኑን ባዘጋጁት ፕሮፖዛል መግቢያ አስፍረዋል፡፡
የዚህ ምክረ ሃሳብ ዓላማዎች፡-
• የሠራተኞችን እና የማኔጅመንቱን ግንኙነት ለማጠናከር፤
• የተቋሙን ሠራተኞች የቤተሰባዊነት ስሜት ለማጠናከር፤
• የግል ሕይወት ማነቃቃት (Motivation) እና የዕውቀት ሽግግር መድረክ ለመፍጠር፤
• በየ15 ቀኑ የምትመጣውን ሰኞ ለሠራተኛው በናፍቆት የምትጠበቅ በማድረግ አዎንታዊ የሥራ አካባቢ ለመፍጠር ያለመ ነው፡፡
“እንገናኝ እንሰናኝ!” መድረክ የሠራኞችን የሥራ ተነሳሽነት ከመጨመሩም በላይ ተቋሙን እንደ አንድ ቤተሰብ የሚያስተሳስር ወሳኝ መድረክ ሊሆን እንደሚችል ታምኖበት የተዘጋጀ የምክር ሃሳብ ፕሮፖዛል ነው፡፡
ይህ ዓይነቱ የምክር ሃሳብ በከተማ ደረጃ በተሞከሩ እና ውጤታማነታቸው በተረጋገጡ መድረኮች ላይ የተመሰረተ የመድረክ ሃሳብ በመኾኑ በተቋችንም ተመሣሣይ ውጤት እንደሚያመጣ ይታመናል፡፡
በዚህ መልክ ቤተሰብአዊ ትሥሥርን ፈጥሮ ተቋሙን ከመለወጥ አንጻር ሥራዎችን ለማሳካት የጀመረ፤ ከሰራንበትም እንደ ፌደራል ተቋም የመጀመሪያው ያደርገናል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
ታሪካዊው የሙዚቃ ቅርስ አውደርዕይ ተካሄደ ።
ሚያዝያ 29/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ላለፉት ዘጠኝ አስርት ዓመታት በዝምታ ተውጠው የቆዩት የኢትዮጵያ የሙዚቃ ቅርሶች ዛሬ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በደመቀ ሁኔታ ለድምጫ አውደ ርዕይ በቅተዋል።
ይህ አውደርዕይ በጣሊያን ወረራ ወቅት (ከ1928-1933 ዓ.ም) በአዲስ አበባ በኮሎምቢያ ሪከርድስ አማካኝነት ተቀርጸው የነበሩ ከ350 በላይ ብርቅዬ የሙዚቃ ቅጂዎች በዘመናዊ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ታድሰው ለታዳሚ የቀረቡበት ነው።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ዕለቱ ለዘጠኝ አስርት ዓመታት ተቀብሮ የቆየ የታሪክ ቅርስ ትንሳኤ የሚበሰርበትና የታሪክ ስብርባሪዎች ሙሉ ሥዕል የታየበት መሆኑን ለኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ ለሙዚቃ አፍቃርያንና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አብስረዋል።
በወቅቱ ቅጂዎቹን ከያዘው ከኮሎምቢያ ሪከርድስ በስተቀር ሙሉ ስብስቦቹ በማንኛውም ተቋም በማይገኙበት ሁኔታ በጥልቅ ጥናትና ምርምር አሰባስበው ለኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በስጦታ ያበረከቱት የቱሪን ዩኒቨርሲቲ ሚውዚኮሎጂስት ፕሮፌሰር Gianpaolo Chiaraco ናቸው። ፕሮፌሰሩ በንግግራቸው "ሙዚቃ ታሪክን ይነግረናል፤ ከነዚህ ድንቅ ስብስቦችም ታሪክን እንማራለን" ብለዋል።
ተቋሙ በውጭ ሀገር የሚገኙ ማህደሮችን በማፈላለግ የድምፅ ቅርሶችን ወደ ሀገር ቤት በመመለስና ለትውልድ እንዲተላለፉ በማድረግ በወቅቱ የነበረውን የታሪክ ስብራት ወደ ታላቅ የባህልና የኪነ-ጥበብ ምርምር እንዲቀየር ላደረጉት ለጣሊያናዊው ፕሮፌሰር Gianpaolo Chiaraco የምስጋና የምስክር ወረቀት አበርክቶላቸዋል።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት እነዚህን በዋጋ የማይተመኑ ቅርሶች በቋሚነት እንዲጠበቁና ለጥናትና ምርምር ክፍት እንዲሆኑ የሚያደርግ መሆኑንም አስታውቋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
የዘጠና ዓመታት ዝምታ ተሰበረ!
የኢትዮጵያ የሙዚቃ ቅርስ ከታሪክ ማኅደር ሲወጣ።
ለሙዚቃ አፍቃሪያን፣ ለታሪክ ተመራማሪዎች እና ለባህል ባለሙያዎች በሙሉ፤
ከዘጠና ዓመታት በፊት በጣሊያን ወረራ ወቅት (1928-1933 ዓ.ም.)፣ በኹለተኛው የዓለም ጦርነት ዋዜማ በዐዲስ አበባ ከተማ እንድ ታሪካዊ የሙዚቃ ቅጂ ተከናወኖ ነበር፡፡ ወደ 350 የሚጠጉ ኢትዮጵያዊ የሀገር ባህል ሙዚቃዎች በኮሎምቢያ ሪከርድስ (Columbia Records) ተቀድተው ነበር። ነገር ግን፣ የኹለተኛው የዓለም ጦርነት በመቀስቀሱ እነዚህ ውድ የሙዚቃ ቅጂዎች ለገበያ ሳይቀርቡ ለዘጠኝ ዐሥርት ዓመታት በዝምታ ውስጥ አለፉ። ከራሱ ከኮሎምቢያ ሬከርድስ በስተቀር እነዚህ ሙዚቃዎች ተሟልተው የሚገኙበት ተቋምም አልነበረም፡፡
ዛሬ፣ ይህ ዝምታ ሰብሯል!
የቱሪን ዩኒቨርሲቲው ፕሮፌሰር ሚውዚኮሎጂስት Gianpaolo Chiaraco እነዚህን የጠፉ የሙዚቃ ሀብቶች በጥልቀት በማጥናት እና በማሰባሰብ፣ ለኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) በሥጦታ አበርክተዋቸዋል። ለድምጫ ዐወደ ርእይም አቅርበዋቸዋል፡፡
በዚህ ልዩ ዐውደ ርእይ ምን ይጠብቅዎታል?
• የድምፅ ጉዞ: ከዘጠና ዓመታት በፊት በነበሩት አዝማሪዎች እና የባህል ሙዚቃ ተጫዋቾች የተቀረጹ ድምፆችን በኤግዚቢሽኑ ላይ በድጋሚ ያዳምጡ።
• የታሪክ ምሥል: የሙዚቀኞቹን ታሪክ፣ የሙዚቃዎቹን አመጣጥ እና የጥንታዊ ፎቶግራፎቻቸውን በልዩ ኹኔታ የተዘጋጀ የዕይታ ጉዞ ያድርጉ።
• የኢትዮጵያን የዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክ ከምንጩ ይረዱ።
የዝግጅቱ ዝርዝር:
📅 ቀን: ኀሙስ፣ ሚያዝያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም.
🕒 ሰዓት: ከሰዓት ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 ቦታ: የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር)
"ታሪክን በድምፅ እና በምስል እንቃኝ"
ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ እንዳያመልጥዎ በክብር ተጋብዘዋል፡፡ --------------------------------------------------------------------------------
Silence Broken After 90 Years: A Lost Chapter of Ethiopian Musical Heritage Returns Home
To all music lovers, historians, and cultural enthusiasts:
Ninety years ago, on the eve of the Second World War, a historic musical endeavor took place in Addis Ababa. During the Italian occupation (1936–1941), nearly 350 traditional Ethiopian musical pieces were recorded by Columbia Records. Due to the outbreak of the war, these precious recordings were never released to the public, remaining lost in the archives for nine decades—until now.
The silence has finally been broken.
Professor Gianpaolo Chiaraco, a dedicated musicologist from the University of Turin, has meticulously researched, recovered, and compiled these lost treasures. In a monumental act of cultural preservation, he has donated the entire collection to the National Archives and Library of Ethiopia (NALE), where they are now being unveiled to the public.
What to Expect at This Exclusive Exhibition:
A Journey in Sound: Listen to the original, restored recordings of the Azmaris and traditional musicians from nine decades ago.
A Visual History: Explore a specially curated exhibition featuring the stories behind the music, the origins of these compositions, and rare historical photographs.
Rooted in History: Gain a deeper understanding of the origins of modern Ethiopian music.
Event Details:
📅 Date: Thursday, May 7, 2026 (Miazia 29, 2018 E.C.)
🕒 Time: 3:00 PM (9:00 Local Time)
📍 Venue: National Archives and Library of Ethiopia (NALE)
"Rediscovering History Through Sound and Image"
"የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የሕጻናት የንባብ ቀን በስኬት ተጠናቀቀ።
ሚያዝያ 22/ 2018ዓ.ም
አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በመላው ኢትዮጵያ ሲካሄድ የቆየው የንባብ ባህል ማዳበር ንቅናቄ አካል የሆነ የህፃናት የንባብ ቀን "የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል በተቋሙ ቅጥር ግቢ ውስጥ በሕጻናት ቤተ መጻሕፍት በደመቀ ሁኔታ አካሂዷል።
በመርሐ ግብሩ ከሜጀር ጀነራል ኃያሎም አርአያ እና ከዕድገት በህብረት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል የሚገኙ ተማሪዎች የተሳተፉበት ነበር።
ተማሪዎች ዕውቀትን የሚያገኙባቸውን መንገዶች በማብራራት ተቋሙ ለንባብና የትውልድን አዕምሮ ለማበልጸግ እንደሚሠራ እንዲሁም ማንበብ ለምትፈልጉ በሩ ክፍት ነው ሲሉ የተቋሙ የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው በመክፈቻ ንግግራቸው ተናግረዋል፡፡
የንባብ ክበባት በት/ቤቶች መመስረት ለሀገር ችግር መፍትኤ የሚሆን በዕውቀት የዳበረ ትውልድ ለመፍጠር ያለውን ፋይዳ የአብያተ መጻሕፍት አገልግሎት መሪ ስራ አስፈጻሚ ተወካይ ወ/ሮ ቅድስት ጌታቸው ለተማሪዎቹ ገለጻ አድርገዋል፡፡
በዚሁ መርሐ ግብሩ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ሀገሬ መኮንን የቀድሞ የመምህርነት ሙያ ጉዟቸውንና የልጆች አስተዳደግ ልምዳቸውን ለተማሪዎችና ለመምህራን አካፍለዋል።
ትምህርትና ንባብ የማይለያዩ መሆናቸውን የተናገሩት ትምህርት ቤቶቹን ወክለው የመጡ መምህራን “ተማሪ ሰነፍ አይደለም!” የማንበብ ፍላጎት አለው፤ ነገር ግን መንገዱን የሚያሳየው ይፈልጋል ተቋማችሁም ለሀገር የሚሰራና ከትምህርት ጎን የቆመ በመሆኑ በቀጣይ ለዚሁ ተግባር የሚያግዝ ስልጥናና ሁነት በት/ቤት እንዲዘጋጅ የአብረን እንስራ ጥሪ አቅርበዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ ለተሳተፉ ት/ቤቶች ተቋሙ ያዘጋጀውን የምስክር ወረቀት የአብያተ መዛግብትና ያብያተ መጻሕፍት ስልጠናና ምክር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ መኮንን ከፍያለ እና የአብያተ መጻሕፍት መረጃ ሀብቶች አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ስለሺ ሽፈራው ት/ቤቱን ወክለው ለመጡ መምህራን አስረክበዋል።
ዝግጅቱ በትምህርት አዘል ተረቶች፣በጥያቄና መልስ፣በመጽሐፍት ሽልማት እንዲሁም በጉብኝት የታጀበና የተማሪዎች ንቁ ተሳትፎ የታየበት ነበር።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት “የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!” በሚል መሪ ቃል የሕጻናት የንባብ ሳምንት መርሐ ግብር ሐሙስ ሚያዝያ 22/ 2018ዓ.ም በተቋሙ ቅጥር ጊቢ ለማካሔድ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
በንባብ ሳምንቱ ታዳሚዎች የሜጀር ጀነራል ኃያሎም አርአያ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት /Major General Hayalom Araya Primary School/ እና የእድገት በህብረት ቅድመ አንደኛ፤አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት /Ediget Behibret pre primary,primary and middle Level School/ (ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል) ተማሪዎች ናቸው፡፡
በዝግጅቱ ፡-
📌. የንባብ ክበባት በት/ት ቤቶች መመስረት ስለሚኖረው ጠቀሜታ በባለሙያዎች ግንዛቤ ይሰጣል፡፡
📌. የንባብ ጥቅምን በተመለከተ ጽሑፍ ይቀርባል፡፡
📌. ትምህርት አዘል የማነቃቂያ መዝሙር ይቀርባል፡፡
📌. አነቃቂ ተረቶች በባለሙያዎች ይቀርባል፡፡
📌. ከተነበቡ ጽሑፎች ላይ ጥያቄዎችን ይጠየቃሉ፡፡
📌. አሸናፊ ለሆኑ ተማሪዎች የመጽሐፍ ሽልማት ይበረከታል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
አርባዕቱ ወንጌል በ14ኛው ክፍለ ዘመን ተጻፈ
በ14ኛው መቶ ክ.ዘ የተጻፈው አርባዕቱ ወንጌል በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር)
በጥንታውያን ሥነ-ጽሑፍ ክፍል ከሚገኙና በዩኔስኮ የዓለም የሥነ-ጽሑፍ ቅርስነት ከተመዘገቡት 12 የጽሑፍ ቅርሶች መካከል አንዱ መሆኑን ምን ያህላችን እናውቃለን?
በብራና ላይ ያለው እያንዳንዱ ቀለም በጥንቃቄ ያረፈበት፣ የኢትዮጵያውያን የሥነ-ጥበብ እና መንፈሣዊ ቅርሶች ማሳያ የሆነ፤ በ14ኛው መቶ ክ.ዘ (ክፍለ ዘመን) የተጻፈውን አራቱን ወንጌላት የያዘ ብራና ጥልቅ ውበት እንድትመረምሩ እንጋብዛችሁ፡፡
ግሩም በሆነ የእጅ ጽሕፈት አጣጣል የማቴዎስ፣ የማርቆስ፣ የሉቃስና የዮሐንስ ወንጌላትን ሙሉውን ጽሑፎች ይዟል፡፡
ከጣና ቂርቆስ ገዳም ለንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ-ሥላሴ በስጦታ የተበረከተ ሲሆን ንጉሱ በ1936 ዓ.ም ‘’የሕዝብ ቤተ-መጻሕፍት ወመዘክር’’ ብለው የዛሬውን የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎትን ሲመሰርቱ ከሰጧቸው የመጻሕፍት ስጦታዎች መካከል የሚጠቀስ ነው፡፡
ይኸው ከበግ ቆዳ የተሠራው ብራና 30 ሳ.ሜ * በ21 ሳ.ሜ ስፋት ያለው ሲሆን ፣ 651 ቅጠል (1,302 ገጽ) ብዛትን በውስጡ ይዟል፡፡
በዋናነት የተጻፈው በግእዝ ቋንቋ ቢሆንም የአረብኛና የኮፕቲክ ቋንቋንም አካቷል፡፡ የላይኛው ሽፋኑ ከእንጨት የተሠራ ፣ ያልተደጎሰ ገበታ ያለው ነው፡፡ በውስጡ የተሳሉት ሥዕላት እና ሐረጋት የጽሑፉን ግልጽነትና ውበት ያጎሉታል፡፡
ይኸው ብራና ከእድሜው ባሻገር በኢትዮጵያ ውስጥ ቀጣይነት ያለውን የእምነትና የእውቀት ሰንሰለት የሚወክል መሆኑ ልዩ ያደርገዋል፡፡
ሀገራችን የክርስትናን እምነት በቀደምትነት የተቀበለች ሀገር እንደመሆኗም የ14ኛውን መቶ ክ.ዘ የኪነ-ጥበብ ልምዶች ፣ ሥነ-መለኮታዊ መረዳትና የጸሐፍትን ክህሎት ለማጥናት በዋጋ ሊተመን የማይችል ማስረጃን ይሰጣል፡፡
የብራናውን ሽፋን በማስተዋል ብቻ እንኳን በዘመኑ የነበሩትን ፈጠራዎች እንዲሁም የባህል ተጽኖዎች ሊገልጽ መቻሉ ከጠቢባን የተደበቀ አይደለም።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
tiktok.com/@wemezekrnals
ብቻችንን እየሮጥን ነው ወይስ የሀገርን ትልቁን ርዕይ ለማሳካት እየሮጥን ነው? የሚለው በትኩረት ሊታይ እንደሚገባ ተገለጸ::
13/08/2018
አዲስ አበባ
የተከናወኑ ተግባራት የተቋሙን ግብ ማሳካታቸውን የሚፈትሽና ያልተከናወኑ ተግባራት ደግሞ በቀሩት ጥቂት ወራት ለመፈጸም የሚያስችል የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ቀረበ::
መሪ ስራ አስፈጻሚ ክፍሎች እያንዳንዳቸው ያከናወኗቸውን ተግባራትና ያጋጠሟቸውን ተግዳሮቶች በጥልቀት ማቅረባቸው ሪፖርቱን በአቀራረብ አካሄድና ይዘት ከቀድሞው የተሻለ እንደሚያደርገው ተገልጿል::
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት በንግግራቸው በየስራ ክፍሉ በተከናወኑ ተግባራት ብቻችንን እየሮጥን ነው ወይስ የሀገርን ትልቁን ርዕይ ለማሳካት እየሮጥን ነው? የሚለው በትኩረት ሊታይ እንደሚገባ ገልጸው
👉🏻በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በሚገኙ ሰነዶች
👉🏻በብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት በሚገኙ የኢትዮጵያን የ50 ዓመታት የፓርቲ ታሪክ የሚያሳዩ ሰነዶች ላይ የተሰራው የዲጂታይዜሽን፣ የምዝና፣ የመረጣና የውገዳ ስራ
👉🏻የቤተመጻሕፍት፣ የሰነድና የመዛግብት አስተዳደር ሙያዎቸ ላይ በሀገሪቱ በሚገኙ የተለያዩ ቦታዎች ላይ የሚሰጡ ስልጠናዎቸ ከተከናወኑ ተግባራት መካከል ለሀገር ባላቸው ፋይዳ ማሳያ ከሆኑት መካከል ጥቂቶቹ እንደሆኑ ገልጸዋል።
በተጨማሪም በግዥና በአዋጅ ከተሰባሰቡ በርካታ የመረጃ ሀብቶች በተጨማሪ ብሔራዊ ቤተ መጻሕፍት የትውስታ ተቋም (Memory institution) መሆኑን በጉልህ የሚያሳይ የፊት አውራሪ አመዴ ለማ ፣ የፕ/ር ተወልደ ገ/እግዚአብሔርና የአቶ ያየህይራድ አላምረው የግል ስብስቦች ባለፉት ዘጠኝ ወራት በስጦታ ወደ ተቋሙ ከተዛወሩ የመረጃ ሀብቶች መካከል እንደሆኑ ፣ የአቡነ ገሪማ ወንጌልን እና የሐረር የባቡር ዝርጋታ ዶክመንትን በአለም የጽሑፍ ቅርስነት ለማስመዝገብ የተሄደው ረጅም ርቀት በቀረው ሩብ ዓመት እንድሚጠናቀቅ በቀረበው ሪፖርት ተመላክቷል።
የቀሩ ያልተከናወኑ ተግባራትን በመጨረሻው ሩብ ዓመት በቁርጠኝነት፣ በዕለት ተዕለት ትጋት እና ፈጠራ በተሞላው የስራ አፈጻጸም ሊጠናቀቅ እንደሚገባው የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት አሳስበዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
tiktok.com/@wemezekrnale
ለተቋሙ የቴሌግራም ተከታታዮቻችን ዘጠነኛው አገር አቀፍ የግእዝ ጉባዔ ከሚያዝያ 15-17 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በደብረ ብርሃን ለማካሔድ ዝግጅቱ የተጠናቀቀው የግእዝ ጉባዔ ለተወሰነ ግዜ መራዘሙን እናሳውቃለን።
ዘጠነኛው አገር አቀፍ የግእዝ ጉባኤ ሊካሔድ ነው።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት፤ ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ የባህል፣ታሪክ እና ቋንቋ ልማት ማዕከል እና የአማራ ክልል ባህል፣ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር "ጥበበ ግእዝና የዘመን ስሌት!" በሚል መሪ ቃል ዘጠነኛውን አገር አቀፍ የግእዝ ጉባዔ ከሚያዚያ 15-17/2018 ዓ.ም ጀምሮ
በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ የባህል፣ታሪክ እና ቋንቋ ልማት ማዕከል ለማካሔድ ዝግጅቱን አጠናቋል።
የዝግጅቱ ተሳታፊዎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ የጥናትና ምርምር ተቋማት፣ ባለድርሻ አካላት እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት እንደሆኑ ተጠቁሟል።
የዝግጅቱ ዓላማም ህብረተሰቡና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በግእዝ ላይ ጥናት እና ምርምር የማድረግና ቋንቋውንም በማልማት መጠቀም ያለውን ፋይዳ ለማስገንዘብ እንደሆነ ተጠቁሟል።
📌በጉባዔው እና በዐውደ ርእዩ አማካይነት ባለድርሻ አካላት እና ዋነኛ ተዋናዮቹ ለግእዝ ቋንቋና በቋንቋው በተፈጠሩ የመረጃ ሀብቶች ጥናት እና ምርምር እንዲሁም ቋንቋውን መልሶ ለማልማት (ሪቫይታላይዜሽን) በመዋቅር፣ በአደረጃጀት እና በስትራቴጂ የሚመራበትን አቅጣጫ ይመላከታል፡፡
📌.በቋንቋው የተፈጠሩ ዘርፈ ብዙ የመረጃ ሀብቶች በሀገራችን ይገኛሉ፡፡
📍የመረጃ ሀብቶች ለሀገር ሁለንተናዊ ልማት ያላቸውን ፋይዳ ለማስገንዘብ እና በአግባቡ ተጠብቀው ለጥናትና ምርምር ተደራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው፡፡
ግብ
📌.አገልግሎቱ ከተቋቋመባቸው ዓላማዎች አንዱ በሀገሪቱ የሚገኙ የጽሑፍ ሀብቶቻችንን ማሰባሰብ፣ ማደራጀት መንከባከብ እና ጥበቃ ለማድረግ የያዙትንም እውቀት ለማጥናት፣ ለጥናትና ምርምር እንዲውሉ ለማድረግ እና ለዘመናዊው ኑሮ ጥቅም ላይ ለማዋል እና ለማስፋፋት፤
📌ቋንቋ ከመግባቢያነቱ ባለፈ የማንነት መገለጫ እንደመሆኑ በኑሮ ሥርዓታችን በቋንቋዎቻችን ውስጥ ባሉ መድብለ ቃላት ለተገቢው አገልግሎት እና ነገር ስያሜ ለመስጠት እንደማንኛውም ያደጉ የዓለም ቋንቋዎች ከጥንታዊ ቋንቋዎቻችን ለስያሜ ለመጠቀም፤
ከዝግጅቱ የሚጠበቅ ውጤት፦
📌 ቋንቋው የሚጠናበትና የሚለማበት በቋንቋው የተፈጠሩ የመረጃ ሀብቶች ጥበቃና እንክብካቤ ለማድረግ ዘላቂ አቅጣጫ መቀየስ፤
📌 የተረጋገጠ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ፤
📌የተፈጠረ ትብብር እና ትስስር፤
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
