7 369
Подписчики
-524 часа
+267 дней
+35130 день
Архив постов
7 372
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
ልብ በሉ፦
ይኽ የግፍ ግፍ የሚፈጸመው፦
👉አልቃይዳ በሚንቀሳቀስባቸው በኢራቅ በረሃና ኮርብቶች አይደለም
👉ቦኮሃራም በሚንቀሳቀስባቸው በናይጄሪያ ተራሮችና ኮረብቶች አይደለም
👉 መንግሥት በማይደርስባቸው ISIS በሚንቀሳቀሱባቸው በሊቢየ በረሃ አይደለም
👉ISIS በተቆጣጠራቸው በፑንትላንድ ተራሮችና ኮረብቶች አይደለም
👉አልሸባብ በሚንቀሳቀስባቸው በሶማሊያና በሶማሊንድ ኮረብቶች አይደለም ፦
እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው።ሥርዐቱስ ኦርቶዶክሳውያን ማጽዳት የተቋቋመበት ዋና ዓላማው ነውና ዝም ቢል አያስገርምም የእኛ ዝም ማለት ግን ያናድዳል።
ወያኔ ወያኔ እያሉ እሬሳውን የጎተቱትም ሆነ በግድ ማዕተባቸውን በጥሰው እንዲሰልሙ የተደረጉ ኦርቶዶክሳውያን በነፍስ የሚጠብቃቸው፦
👉 ቤተ ክህነት የሚባል መዋቅር አላቸው
👉ሲኖዶስ የሚባል የጳጳሳት ጉባኤ አላቸው
👉ፓትርያርክ አላቸው
👉የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አለ
👉የወረዳው ቤተ ክህነት አለ
👉የአጥቢያው አስተዳዳሪ አለ
👉ወንጌል የሚያስተምራቸው መምህር አላቸው
👉የንስሐ አባት አላቸው
👉 በጥቅቀት የሚመስለው ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ አለ
ከእነዚህ ሁሉ ግን ለምን ብሎ የጠየቀ የተቆጣም የለም።እኛም ምዕመናን መከራን ተለማመድነው።
መፍትሔው ምንድን ነው?
👉ነጻ ሊያወጣን የሚችል ምድራዊ ኀይል እንደሌለ ማወቅ
👉 ከቤተሰብ ጀምረን ስለ ኅልውናችን መወያየትና ተደራጅቶ ራስን መከላከል
https://t.me/Eyo21e
7 372
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
+4
ለኦርቶዶክስ ሲሆን "Oromoon Oromoo hin Ajjeesu(ኦሮሞ ኦሮሞን አይገድልም)"የሚለው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ርዕዮተዓለም አይሠራም።ለምን? በሥርዐቱ ብያኔ ኦርቶዶክስ የኦሮሞነትን መስፈርት አያሟላምና።የኦሮሞነት መስፈርቱ ሙስሊምም፣ፕሮቴስታንት፣ካቶሊክ እና ዋቄፈና መሆን ነው።ይኽን አስታወሳችሁት አይደል? በ2013ዓ.ም በወለጋ ደምቢ ዶሎ በመንግሥት ወታደሮች በአደባባይ በግፍ የተረሸነው ዲያቆን አማኑኤል ወንድሙ።ይኽን እንደምሳሌ አተሳሁት እንጂ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ነፍጠኛ ተብለው የተገደሉ በሺህ የሚቆጠሩ ኦርቶዶክሶች አሉ ።
7 372
ከምድረ ገጽ እንድትጠፋ የተፈረደብህ ሕዝብ ሆይ፦
👉በጅምላ ታርደህ በጅምላ መቀበርህ
👉 ከርስት ጉልትህ ተሰደህ ሀገር አልባ መሆንህ፦ካላስማማህና በአንድነት ካላቆመህ ሌላ ምን ሊያስማማህ ነው?ምንስ በአንድነት ሊያቆምህ ነው? በአራቱም አቅጣጫ ጠላቶችህ ተከበህ ዛሬም፦
👉ታንቀላፋለህን?
👉በጥልቅ ድንዛዜ ውስጥ ተመላለሳለህ?
👉 ዘር ትቆጥራለህ?
👉በጎጥና በመንደር ተደራጅተህ ትነካከሳለህ?
👉 ኅልውናህ ወደ ጎን ብለህ ግለሰብ ታጀግናለህ?
👉 በሥልጣንና በዝና ጥማት ትቃጠላለህ?
መጽሐፍ እንዲህ እንዲህ ይላል፦
እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁላ ትጠፋለች፥ እርስ በርሱ የሚለያይ ከተማም ሁሉ ወይም ቤት አይቆምም።ማቴ 12:25
7 372
ምሥራቅ አርሲ #ጢቾ ወረዳ
በምሥራቅ አርሲ ዞን ጢቾ ወረዳ በሶሌ መደሮ ቀበሌ <<መደሮ>> በምትባል ታዳጊ ከተማ ትናንት ማለትም በ 14/07/2018ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። በጥቃቱ አቶ መኩሪያ ዉቤ የተባላ ኦርቶዶክሳዊ በአሰቂቂ ሁኔታ የታረደ ሲሆን ለጊዜው ስማቸው ያልተጠቀሰ ሥስት ኦርቶዶክሳውያን ታግተው ተወስደዋል። ከተማዋ ላይ ያለው የአገዛዙ ኀይል ነው ነገር ግን ኦርቶዶክሳውያን ላይ ጅሃድ ሲፈጸም ሊደርስና ሊታደግ አልቻለም። ይኽ በእንዲህ እንዳለ በአከባቢውና በሽርካ ወረዳ ስር ያሉ በአጎራባች ቀበሌዎች ያሉ ኦርቶዶክሳውያን ለከፍተኛ ስጋት እንደተዳረጉ ከቦታው የደረሱኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከአጥፊዎች የሚታደግ መዋቅርና እረኛ ባይኖርም ከምድረ ገጽ እንዲጠፉ የተፈረደባቸው ኦርቶዶክሳውያን ግን ዛሬም "የድረሱልን" ጥሪ በማሰማት ላይ ናቸው።
https://t.me/Eyo21e
ኢዮሳፍጥ ጌታቸው
7 372
<<በሚዲያ ጫካ የጠፋውን ትውልድ በሚዲያ ኀሰሳ እንፈልግ>>
✍️ሚድያውን ለቤተ ክርስቲያን መጠቀም ያስፈልጋል።
✍️በእጅህ ላይ፣በእጅሽ ላይ ያለውን ሞባይል ከመደዋወያነት እና ከተራ ተግባሮች ባሻገር ምን እየሠራህበት ነው?ምን እየሠራሽበት ነው?
👉ከእጃችን ላይ ባለው ሞባይላችን የዕቅበተ እምነት፣የኦርቶዶክሳዊ ድምጽ ኅብረት ማስተጋቢያ፣የዶግማ፣የቀኖና፣የትውፊት መጠበቂያ፣የኦርቶዶክሳዊነት አስተሳስብ ማስረጫ..ማድረግ ያስፈልጋል።
👉ዓለም አንድ ለሆኑ፣ለብዙኃን እና ለሚድያ አካላት የተገለጠች ናት።
ቀድመው አየሩን የያዙ አካላት የሰውን አእምሮ ቀድመው መያዛቸው አይቀሬ ነው።ዘግይቶ ከደረሰ እውነት ቀድሞ የደረሰ ውሸት ጉልበት ይኖረዋል።እውነተኛ ሀሳብ ሲዘገይ ሥሁት ሀሳብ ቀድሞ ጥልቅ ብሎ የሰውን አእምሮ ይበክለዋል።
👉አሁን ሁሉም ነገር የሚቀዳው ከርዕዮተ ሀሳብ አምራቾችና የዕለት አጀንዳ ሰጪዎች ሁኗል፡፡ያ አጀንዳ ደግሞ በእግዚአብሔርና በሰው መካከል፣በሰውና በሰው መካከል፣በሰውና በተፈጥሮ መካከል ያለው መስተጋብር የዘነጋ ነው።
👉ስለዚህ፦ኦርቶዶክሳዊነት ከእግዚአብሔር የተሰጠ ለቅዱሳን የተሰጠ እውነት ነውና ይሄንን እውነት መስተጋብሩን ለረሳው ዓለም በኅብረት ሁኖ የእውነት ምንጭ ለሌለው ዓለም ቀዳሽ ሀሳብ አድርጎ ማሳየትና ማቅረብ ያስፈልጋል።
👉አሁን ባለው ዓለም በህልውና መኖራችም ሆነ የሰው ንቃተ ህሊና እና ተሳትፎ የሚታየው በአየሩ ላይ ባለን ከባቢ ኅብረት ልክ ሁኗል።
ስለዚህ የኦርቶዶክሳውያን ሐዋርያዊ የተሳትፎ ድምጻቸው አንድ ሁኖ ማስተጋባት፣ርቱዕ ኦርቶዶክሳዊ አሳባቸው በኅብረታዊነት መግለጽ መቻል ይገባዋል።
👉በኦርቶዶክሳዊነት አረዳድ ሥር ሁነን ስንተባበር በተለያዩ ቦታ፣ ሁኔታ፣ ጊዜ ወዘተ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውናንን አድሬስ ማድረግ እንችላለን።በዚያውም ላይ በቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰን እና ሊደርስ የታቀደን መከራ ማስቀረት ወይም መቀነስ ያስችላል።
👉በኅበረታዊነት ለቤተ ክርስቲያን ጠሎችም ለወዳጆችንም ሁሉንም የሰው ልጅ ሊጠቅሙ የሚችሉ ፈጣን እና ሚዛናዊ እውነታዊ መልእክቶችን ለማድረስ እውነተኛ ትምህርቶች በኦርቶዶክሳዊነት አስተሳስብ መገለጽ መቻል አለባቸው።
👉ኅብረታችንን በኦርቶዶክሳዊነት አስተሳስብ ቃኝተን በንቃት ስንጠቀመው በሚዲያ ጫካ የጠፋውን ትውልድ በሚዲያ ኀሠሣ መፈለግና ለመመለስ ያስችለናል።
👉በዚያውም ላይ አሁን ባለው እጅግ የበዛ ሥሁት የመረጃ ምንጭ መካከል በሐዋርያዊ አረዳድ ውስጥ ሁነን መተባበር ኦርቶዶክሳውያን አይነተኛ ሚዛናዊ ርቱዕ ታማኝ የመረጃ ምንጭ ሁነው መገኘት እንዲችሉ ያደርጋል።
👉የነበረንን፣ያለንን ስጦታ፣ ቅርስ፣ ታሪክ፣ ባህል፣ሀገር በቀል ዕውቀት፣ ትምህርት ወዘተ በአንድ ድምጽ ለማስተላለፍ በሁለገብ ዘርፍ መረዳዳት ያስፈልጋል።
👉ይባሱን ብሎ በራስ ሞባይል በተለያዩ ሥሁት እሳቤዎች ተተብትቦ ራስን መጉዳት ኦርቶዶክሳዊ ኅብረትን መጋፋት ግን በሰው ዘንድ ውርደት በእግዚአብሔር ዘንድ ደግሞ ኃጢአት ነው።
ከ[የኔታ ገብረመድኅን እንየው]
https://t.me/Eyo21e
