7 369
Подписчики
+524 часа
+617 дней
+35230 день
Архив постов
7 369
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
እስካሁን በደረሰኝ መረጃ መሠረት በትናንትነው ዕለት(23/09/2018ዓ.ም) በምሥራቅ አርሲ ዞን በሦስት ወረዳዎች ብቻ 14 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል።በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 2፣በሽርካ 2 እና በአሰኮ ወረዳ 10 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል። ይኽ ሁሉ እልቂት በመንግሥት መዋቅር የሚፈጸም ነው።
7 369
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
ሀገራዊ ምርጫውን ተገን በማድረግ በምሥራቅ አርሲ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ጥቃት ተፈጸመ፤10 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል አብያተ ክርስቲያናትና የነዋሪዎች ንብረቶች ተቃጥለዋል
የሁሉም ትኩረት በሀገራዊ ምርጫ ላይ ማረፉን እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም፣ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በሚገኙ አካባቢዎች በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ያነጣጠረ መጠነ-ሰፊ ጥቃት መፈጸሙ ተገለጠ። ከትላንት ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተቀሰቀሰው በዚህ ጥቃት የሰው ሕይወት ማለፉን፣ ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናት መቃጠላቸውንና ከፍተኛ የንብረት ዘረፋና ውድመት መድረሱን የአካባቢው መረጃዎች አመልክተዋል።
የሰው ኃይል ጉዳት እና መፈናቀል በወረዳው ሥር በሚገኘው ጠላታ ጨፋ ቀበሌ በተፈጸመው ጥቃት እስካሁን የ10 ሰዎች ሕይወት በግፍ ማለፉ ተረጋግጧል።
በጥቃቱ ወቅት የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች መኖሪያ ቤቶች ተለይተው እየተቃጠሉና ከብቶቻቸውን ጨምሮ በርካታ ንብረቶቻቸው እየተዘረፉ መሆኑ ተመልክቷል።
በዚህም ምክንያት ነዋሪዎቹ አካባቢያቸውን ለቀው ሱንቴ ወደሚባል ስፍራ ለመሰደድ ተገደዋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በዛው ወረዳ በሚገኘው ካራ ኩፍቴና ቀበሌ የነዋሪዎች ቤቶች እየተቃጠሉ በመሆኑ፣ ሕዝቡ የመድኃኔዓለምን ታቦት ይዞ ሕይወቱን ለማዳን ወደ ሱንቴ አካባቢ መሸሹ ታውቋል።
በአብያተ ክርስቲያናት ላይ የደረሰ ውድመት
ጥቃቱ በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ብቻ ሳይሆን በታሪካዊ የሃይማኖት ተቋማት ላይም ያነጣጠረ ነበረ። በዚህም መሠረት ከ101 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በቃጠሎ ወድሟል።
የካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ንብረት የሆኑ ልዩ ልዩ የአገልግሎት መስጫ ቤቶችም ተቃጥለዋል።
የጥቃቱ ወቅታዊ ሁኔታ የአካባቢው ምንጮች እንደሚጠቁሙት፣ ጥቃቱ የተፈጸመው በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ያለው አጠቃላይ ትኩረት ወደ አገራዊ ምርጫው ባዘነበለበት ማግስት፣ የተፈጠረውን የጸጥታ ክፍተት እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ነው።
ይህ በተደጋጋሚ ጥቃት እንደሚፈጸምበት የሚነገረው የአርሲ አካባቢ ኦርቶዶክሳውያን፣ አሁንም በምርጫው ዋዜማና ዕለት የጥቃት ሰለባ ሆኗል።
ድምፀ ተዋሕዶ
7 369
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
አሳዛኝ ዜና
በምሥራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ሚታና ዋጂ ቀበሌ ሁለት ወንድማማች ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል። ትናንት ማለትም 23/09/2018 ዓ.ም ምሽት ቤታቸው ገብተው ሁለቱንም አፍነው ወሰደዋቸው 10ከ.ሚ በላይ እንዲጓዙ ካደረጉ በኋላ ጋዶ ማርያም ቤተ ክርስቲያን በቅርብ ርቀት ላይ አንዱን በአሰቃቂ ሁኔታ ያረዱት ሲሆን አንደኛውን ደግሞ ረሽነው ጥለው ሄደዋል።ሥርዐተ ቀብራቸው ዛሬ በጋዶ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።ጥቃቱን የፈጸሙት በመንሥት መዋቅር የሚመሩት አክራሪ ወሀቢያዎቹ ናቸው።
https://t.me/Eyo21e
7 369
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
የአርሲ ኦርቶዶክሳውያን
በአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመው የዘር ማጥፋት በቀላሉ የሚቆም እንዳልሆነ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ተገንዝቦ የድርሻውን መወጣት አለበት።
ለምንድን ነው በቀላሉ ሊቆም የማይችለው?
፩ በአርሲ የሚኖረው ኦርቶዶክሳዊ ከ90% በላይ የሸዋ አማራና የሸዋ ኦሮሞ ማኅበረሰብ ነው።
👉 ፖለቲካው በፈጠረው የሐሰት ትርክት የሸዋ አማራው <<ነፍጠኛ>>የሸዋ ኦሮሞው <<ጎበና>>የሚል የጄኖሳይድ(የዘር ማጥፋት) ኮድ ተለጥፎበታል
👉 አጼ ምንሊክና ራስ ጎበና ዳጬ ወደ አርሲ "ዘምተው የጨፈጨፉት ሙስሊሙን ነው" የሚል የውሸት ትርክት አለ።ደፍሮ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል አንድም ምሁር የለም።
👉"የአርሲ መሬት መሆን ያለበት ለአርሲ ሙስሊሞች ብቻ ነው የሸዋ አማራውም የሸዋ ኦሮሞው ኦርቶዶክስ ታርዶም ተጨፍጭፎም ተሰዶም ከአርሲ ምድር መጽዳት አለበት "የሚል አቋም ይዘው ነው እየሠሩ ያሉት
፪ ከአርሲ እስከ ሞጆ ድረስ የተዘረጋ ኢስላማዊ ግዛት ። የአርሲ ድንበር እስከ ሞጆ ድረስ ነው ብለው ነው የሚያምኑት።እነ ፕሮፌሰር አባስ ሐጂ ገነሞ ፣ፕሮፌሰር ሐሰን ሙሐድ የዚህ አሳብ ዋና አቀንቃኞች ናቸው። ሸዋ(ምሥራቅ) ያለው ኦርቶዶክስ አርሲ ካለው ጋር እንዳይተባበርባቸው የአርሲውን አስቀድሞ የ መምታት ሥራ ነው እየሠሩ ያሉት።ሞጆ ሉሜ ወረዳ ቤተ ክህነት ላይ የተፈጸመው ፍጅት የፕሮጄክቱ አንዱ አካል።የልብ ሙቀት መለኪያ ማለት ነው።
፫ የሥርዐቱ ፍላጎት፦ሥርዐቱ በኦርቶዶክስ ጥላቻ ላይ የተመሠረተ ነው ።
👉ከ ፌዴራል መንግሥት እስከ ቀበሌ አስተዳደር የጭፍጨፋው ተሳተፊ ነው
👉 ለገዳዩቹ ድጋፍ ይሰጣል ከለላ ያድርጋላቸዋል
👉 ስንቅም ትጥቅም ያቀርብላቸዋል።
👉 ጭፍጨፋውን አጠናክሮ ለመቀጠል እንዲያመቸው በ ኦርቶዶክሱ ላይ "ፋኖ"የሚል ታፔላ ይለጥፋል
👉በአጭሩ ጅሃድስቶቹን ኦርቶዶክስን ለማፈራረስ እንደ መሳሪያ ነው የሚጠቀምባቸው
፬ ኢስላማዊት ኦሮሚያን" የማዋለድ ፕሮጄክት ውስጥ አርሲን እንደ መነሻቸው አድርገው እየተንቀሳቀሱ ስለሆነ
፭ ሀገር በቀል አክራሪ እስልምናን ለማጠናከር የሚደረጉ የዉጭ ኀይሎች ጣልቃ ገብነት እና ቀጣናዊ የሽብር ሰንሰለቶች።
አርሲ ላይ ያለው የወሀቢያው ቡድን በሶማሊያና በፑንትላንድ ካለው የአልሸባብ እና የአይኤስ የሽብር ቡድን ጋር ከፍተኛ የሆነ ቁርኝት ያለው ነው።
፮ ጂኦግራፊ፦
👉የሙስሊሙ ማኅበረሰብ በአብዛኛው የሚኖረው ደጋማውና ቆላማው አከባቢ ሲሆን ኦርቶዶክሱ ደግሞ መሃል ላይ ነው ።ስለዚህ አጥፊዎቹ ጥቃት አድረሰው ለመሸሸግ ያመቻቸዋል
👉 አርሲ ከባሌ እና ከሐረርጌ ጋር ይዋሰናል ።ሐረርጌና ባሌ ደግሞ ከሶማሌ ጋር ይዋሰናል ሶማሌ የአልሸባብ ክንፎች አሉ።ይኽ ደግሞ አርሲ ያሉት አክራሪዎች እዚህ ካሉት ጋር ጥምረት እንዲፈጥሩ ይረዳቸዋል
፯ የምንደኞቹ ተባባሪነት፦ እረኞቹ ሕዝቡን የመታደግ ምኞቱም ፍላጎቱም የላቸውም
👉 ከአጥፊዎቹ ጋር የሚተባበሩ ጳጳሳት፣ካህናትና ማኅበራት አሉ
፰ የኦርቶዶክሱ ድንዛዜና ኅብረት አልባነት፦
👉 አብዛኛው ሰው ምን እየተካሄደ እንዳለ እንኳ አልተረዳም።ግማሹ የብሔር ይመስለዋል፣ግማሹ ገዳዮችን ያገለግላል።
👉በዚህ መከራ ውስጥ ሆነን እንኳ ከሰፈርተኝነት፣ከጎጠኝነት፣ከቋንቋ በሸታ፣ከዘረኝነት፣ከክልልነት እሳቤ መላቀቅ አልቻልንም።
አንባቢው ያስተውል
✍ የሚጠብቅ እረኛ ከሌለ ሕዝቡ ተደራጅቶ ራሱን መጠበቅና ኅልዉናውን ማስከበር አለበት
👉 አርሲ ላይ ኦርቶዶክሳውያን የሚያርደው አክራሪ እስልምና በመንግሥት መዋቅር የሚደገፍና በዓለም አቀፍ የእስልምና አሸባሪዎች ከእነ አልሸባብ፣ከአልቃይዳና ከአይኤስአይኤስ ጋር ትስስር ያለው ነው
✍ጥቃቱ በአርሲ ብቻ የሚቆም ሳይሆን በሌሎች ስፍራዎችም ይቀጥላል
https://t.me/Eyo21e
ኢዮሳፍጥ ጌታቸው
7 369
አርሲ ስርካን ጨምሮ በመላው ኢትዮጵያ ኦርቶክዶሳዊያን ክርስቲያኖች ላይ ያነጣጠረው ግድያ መፈናቀል መንግሥታዊ የስነልቦና ጫና ማድረግ የተጠና በብዙ በጀት የሚንቀሳቀስ ስትራቴጂካዊ ተግባር ነው።
ይህ የዘር ማጽዳት ዘመቻ የተጀመረው በቅርቡ ወይም ዓብይ ወደ ስልጣን ስመጣ የሚመስላቸው ምስኪኖች አሉ። ነገሩ እንደዛ አይደለም። በንጉሡ ዘመን ሀኪም ላምቤ የሚባል ሚሲዮናዊ በአሁኑ አጠራር ምዕራብ ኦሮሚያና ጋሞጎፋ አከባቢ ይንቀሳቀስ ነበር። ሰውየው ከደቡብ ሱዳን ነበር ወደዚህ የመጣው።
በኢትዮጵያ ቆይታው በተለየዩ የሀገራችን ክፍል በመንቀሳቀስ የህክምና ዕርዳታ ከመስጠት ጎን ለጎን የወንጌል አስተምህሮ በመስጠት ይታወቅ ነበር። ከዚያ በተጨማሪ ኦሮሚያን ጨምሮ ደቡባዊውን የሀገራችን ክፍል በሰሜኑ የኦርቶዶክስ ቅኝ ግዛት ስር ናችሁ በማለት በጥላቻ እያጠመቀ ወደ ወጪ ልኮ ጸረ ኢትዮጵያና ኦርቶዶክስ በብዛት እንድፈላፈሉ አደረገ።
በጣሊያን ወረራ ወቅት የተማሩ ኦርቶዶክሳዊያን በአድስ አበባ እንድጨፈጨፉ አደረገ። በቅዱሱ ስፍራ በደብረ ሊባኖስ ገዳም የተረሸኑት አባቶች በሀኪም ላምቤ ቤት በተደረገ ስብሰባ መሆኑን የታሪክ ድርናት ያስረዳሉ። ንጉሱና አርበኞቹ አሸንፎ የሀገር ባንድራ ከፍ ሲል ከሀገር ተባረረ። ጸረ ኦርቶዶክስ እንቅስቃሴ የተጀመረው በአውሮፓ ሚሲዮናውያን መሆኑን ተረዳ እንግዲህ።
ደርግ ቤተክርስቲያን የነበሩትን ተሰሚነት ብቻ ሳይሆን ቅዱስ ፓትርያርኩን ጭምር አሰጣት። ኢህአዴግ የጴንጤ እንቅስቃሴ ላይ ገደብ ሰያደርግ በገፍ ምዕመናን ከዚህ እያወጡ በተጠና መልኩ ቁጡሯ እንድ ቀንስ ተደረገ። ለምሳሌ በምዕራብ ኦሮሚያ በወለጋ በአዋጅ ሰው ጳነጠጣ። ዝምታ ተመረጠ።
በነፍጠኛ የፖለቲካ ዕሳቤ ጸረ ኦርቶዶክስ ትውልድ ተፈጠረ። የቁቤ ትውልድ የሚባል ኦርቶዶክስ ያልሆነ ኦርቶዶኮስ አለመሆን ጽድቅ እንደሆነ በመንግሥት በጀት ተሰበከ። በኦርቶዶክስ ጥላቻ ተጠመቀ። ያ ትውልድ አሁን የስልጣን ባላቤት ነው። ስልጣን ይዞ በአዋጅ ነባሩን ኢትዮጵያዊ ክርስትና በማስተው በምዕራብ ሸዋ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ በከፍል ሰላሌ በምስራቅ ሸዋ በምስራቅ ወለጋ የቀረውን ኦርቶዶክስ ጴንጤ እንድሆን ያደረጋል።
እምቢ ማለት በመንግሥት ተቋማት ስራ ያሰጣል አገልግሎት አያስገኝም። የሚገርመው ሰር ቤት በሚገኘው የኦሮሚያ መስሪያ ቤቶች ውስጥ ከላይ የጴንጤ አዳራሽ አለ። በለስ ቀንቷቸው እዛ ከገባችሁ ስልጣን ገንዘብ የትምህርት ዕድል ወዘተረፈ በሽ ነው።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በሲዳማ በጋምቤላና ቤንሻንጉል የሚደረገው ተግባርም ይሄው ነው። ኢስላማዊ በሆነ የሀገራችን አከባቢ ደግሞ እሺ ያለውን ያሳልማሉ እምቢ ያለው ደግሞ ይገደላል።
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ደግሞ በድሮን በሜካናይዝድ ጦር ክርስቲያንን የለየ የዘር ፍጅት ይካሄዳል። ቤተከርስቲያንና ልጆቿ ፈተናቸው በስቷል። የትግራይና የአማራ ልህቃን ተግባብተው ይህንን ችግር መረዳት አይፈልጉም። ተረድተው ለችግሩ መፍትሔ መስጠት አይፈልጉም። ገና በብሔር ተጥሯል። ኧረ ንቁ። በሊባኖስ በውጭ ሀይል የተደረገው ኦርቶዶክስን አዳክሞ ጴንጤን የማንገሱ ተግባር ምን እንዳስከተለ ተመልከቱ። አባቶች ገና ናቸው። አልነቁም። ወጡሆይ ንቃ።
7 369
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
እልቂታችንን ሊያስያስቆምልን የሚችል ማን ነው?
👉ሲኖዶስ ነውን? አይደለም።
ለምን ?፦በገዳዮቻችን ቁጥጥር ስር ወድቋልና
👉 ጳጳሳት ናቸውን? አይደሉም።
ለምን? ፦ ድሎትን ማጣጠም፣ ሀብት ማፍራት፣ፎቅ መገንባት፣ድሎት ማሳደድ ላይ ተጠምደዋልና እልቂታችን ትዝ አይላቸውም። እንዲሁም የጸረ ኦርቶዶክስ ሥርዐት ሥራ አስፈጻሚዎች ናቸውና።
👉 መምህራን ናቸውን? አይደሉም።ለምን? ከጥቂቶች በቀር አጎበዳጅና መስሎ አዳሪ ሆነዋልና
👉ሰንበት ትምህርት ቤት ነውን? አይደለም።ለምን? ምናልባት ገጠር አከባቢ ካልሆነ በቀር የከተሜው(ከወረዳ ጀምሮ) ዓላማውን ስቶ በመንግሥት ደኅንነቶችና ሰላዮች ተጠርንፎ ተይዟልና።
👉ማኅበራት ናቸውን? አይደሉም።ለምን? አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ቤተ ክርስቲያንን ሊያሻግር የሚችል አንድም ማኅበር የለም። ህንጻ ግንባታ፣ነጭ ለብሶ አደባባይ ሞልቶ መዘመር ...ካልሆነ በቀር።እኔ በልጥ እኔ በልጥ እርሰበርሳቸው ውድድር ላይ ናቸው።
👉ዲያፖራው ነውን? አይደለም።ለምን? በነጻነት ሀገር እየኖረ ስንታረድ ስንሰደድ የመከራ ዶፍ ሲወርብን ወጥቶ ድምፁን ያላሰማልን እንዴት ነጻ ሊያወጣን ሊታደገን ይችላል?
👉 በየቦታው የታጠቁ ቡድኖች ናቸውን? አይደሉም።ለምን? ከዘረኝነት፣ከበታችነት ስሜት፣ከጎጠኝነት፣ከሰፈርተኝት ፣ከጥቅም፣ከሴራ፣ከባዕዳን ተላላኪነት ነጻ ያልሆነ እኛን ነጻ ሊያወጣን አይችልምና።
ታዲያ ማን ሊታደገን ነው?
👉እኔ ፣አንተ ፣አንቺ።
👉እንዴት ? እግዚአብሔርን ከፊት አስቀድመን ሁላችንም የሕመማችንን ጥልቀት ማወቅ መረዳት ከዚያን የበኩላችንን የሚጠበቅብንን ማድረግ፣ጥቃቱን እንደ አመጣጡ መመከት።
ማሳሰቢያ፦
1) ሲኖዶስ ተተቸብኝ፣ጳጳሳቱ ተተቹብኝ፣እነ እንትና ተነኩብኝ፣ማኅበሬ ተተቸብኝ.... ለሚሉ መንጋዎች ቦታም ጊዜም የለኝም።ማንም ቢሆን ከቤተ ክርስቲያን ኅልውና በታች ነው።ስሜ ያለ አግባብ ተጠራ የሚል ካለ እልቂታችንን ለማስቆም ቁርጠኝነቱን በተግባር ያሳየን።በደፋናው እንዲሁ አክብሩኝ አይሠራም።
2) እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ይታደጉኛል ብሎ የሚያምን ኦርቶዶክሳሳዊ ካለ መልካም የእልቂትና የስደት ጊዜ ይሁንልህ ከማለት በቀር ምን ማለት ይቻላል?
https://t.me/Eyo21e
7 369
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
ቤተ ክርስቲያን የጸረ ኦርቶዶክስ ፖለቲካ ተሸካሚ ከሆኑ ከማፊያ ሽማግሌዎች ቅኝ ግዛት ነጻ መውጣት አለባት።ሐዋርያዊ ልቡና ያላቸው እውነተኛ መነኮሳት ከገዳም ተመርጠው ሊመሯት ይገባል።ከአባት መሳይ ማፊያ ሽማግሌዎች ነጻ እንውጣ።
