ru
Feedback
🎓University's

🎓University's

Открыть в Telegram

ሀገራዊና አለም አቀፍ ዚዩኒቚርሲቲዎቜ መሚጃዎቜ እንዳያመልጊ! ‎አስተማማኝ እና እውነተኛ  ዜናዎቜን ለማግኘት ዛሬውኑ ተቀላቀሉ#university #ministry of education # Ethiopian university # GATExam #ExitExam

БПльше
957
ППЎпОсчОкО
-324 часа
-47 ЎМей
-4030 ЎеМь

Загрузка ЎаММых...

ППхПжОе каМалы
Нет ЎаММых
ВПзМОклО прПблеЌы? ППжалуйста, ПбМПвОте страМОцу ОлО ПбратОтесь к МашеЌу support-ЌеМеЎжеру .
ОблакП тегПв
Нет ЎаММых
ВПзМОклО прПблеЌы? ППжалуйста, ПбМПвОте страМОцу ОлО ПбратОтесь к МашеЌу support-ЌеМеЎжеру .
ВхПЎящОе О ОсхПЎящОе упПЌОМаМОя
---
---
---
---
---
---
ПрОвлечеМОе пПЎпОсчОкПв
ОюМь '26
ОюМь '26
+1
в 0 каМалах
Ќай '26
+8
в 0 каМалах
Get PRO
апрель '26
+13
в 0 каМалах
Get PRO
Ќарт '26
+291
в 1 каМалах
Get PRO
февраль '26
+367
в 1 каМалах
Get PRO
яМварь '26
+449
в 1 каМалах
Дата
ПрОвлечеМОе пПЎпОсчОкПв
УпПЌОМаМОя
КаМалы
13 ОюМя0
12 ОюМя0
11 ОюМя0
10 ОюМя+1
09 ОюМя0
08 ОюМя0
07 ОюМя0
06 ОюМя0
05 ОюМя0
04 ОюМя0
03 ОюМя0
02 ОюМя0
01 ОюМя0
ППсты каМала
ዹኹፍተኛ ትምህርት ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና (Exit Exam) መሰጠት ጀምሯል፡፡ ፈተናው ኚዛሬ ሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ቀናት (ቅዳሜ እና እሑድ ሳይጚምር) በኩንላይን ይሰጣል፡፡ ለመጀመ
ዹኹፍተኛ ትምህርት ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና (Exit Exam) መሰጠት ጀምሯል፡፡   ፈተናው ኚዛሬ ሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ቀናት (ቅዳሜ እና እሑድ ሳይጚምር) በኩንላይን ይሰጣል፡፡   ለመጀመሪያ ጊዜ እና በድጋሜ ለመውጫ ፈተናው ዚሚቀመጡ በመቶ ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ዚመንግሥት እና ዹግል ተፈታኞቜ ፈተናውን ይወስዳሉ፡፡   ተፈታኞቜ ስለፈተናው አጠቃላይ ገለጻ ዛሬ ጠዋት ዚተሰጣ቞ው ሲሆንፀ በዛሬው ዚመጀመሪያ ቀን ዹፈተና ውሎ በጠዋት እና ኚሰዓት መርሐግብር (ኹ5፡00-7፡00 እና ኹ8፡30-11፡00) ዹ62 ትምህርት አይነት ፈተናዎቜ እንደሚሰጡ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ዚወጣው መርሐግብር ያሳያል፡፡   ዹኹፍተኛ ትምህርት ዚመውጫ ፈተና ኹ2015 ዓ.ም ጀምሮ እዚተሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ምስልፊ ዓዲግራት ዩኒቚርሲቲ፣ ወልድያ ዩኒቚርሲቲ እና ወራቀ ዩኒቚርሲቲ

2
ዹ2018 ዓ.ም ዚዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና መርሐግብር (Exit Exam Schedule) ዚቅድመ-ምሹቃ ዚመውጫ ፈተና ኹሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። @universityidea
288
3
ዹ2018 ዓ.ም ዹኹፍተኛ ትምህርት ብሔራዊ ፈተናዎቜ ዹጊዜ ሰሌዳ ትምህርት ሚኒስ቎ር ለተማሪዎቜ እና ለሚመለኚታ቞ው አካላት ይፋ ባደሚገው መርሃ-ግብር መሰሚትፊ ዚማጠናኚሪያ (Remedial) ፕሮግራም
ዹ2018 ዓ.ም ዹኹፍተኛ ትምህርት ብሔራዊ ፈተናዎቜ ዹጊዜ ሰሌዳ ትምህርት ሚኒስ቎ር ለተማሪዎቜ እና ለሚመለኚታ቞ው አካላት ይፋ ባደሚገው መርሃ-ግብር መሰሚትፊ ዚማጠናኚሪያ (Remedial) ፕሮግራም ብሔራዊ ፈተና፩ ኚግንቊት 17 እስኚ ግንቊት 20 ቀን 2018 ዓ.ም (May 25 – 28, 2026) ይሰጣል። ዚመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎቜ ዚመውጫ ፈተና (Exit Exam)ፊ ኹሰኔ 2 እስኚ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም (June 9 – 19, 2026) ይሰጣል። ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና (ESSLCE)ፊ ኹሰኔ 24 እስኚ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (July 1 – 24, 2026) ይሰጣል። ዚድህሚ-ምሹቃ መግቢያ ፈተና (NGAT)ፊ ኹነሐሮ 1 እስኚ ነሐሮ 2 ቀን 2018 ዓ.ም (August 6 – 7, 2026) ይሰጣል። ለተማሪዎቜ በሙሉ መልካም ዚዝግጅት ጊዜ ይሁንላቾው
0
4
በኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ዚሚታዚውን ዚተሜኚርካሪዎቜ እጥሚት ለመቅሹፍ በኪራይ ለመሾፈን መደሹጉ ለኹፍተኛ ዚሀብት ብክነትና ለመልካም አስተዳደር ቜግር ምክንያት መሆኑ ተገለጞ። መንግሥት ልዩ ት
በኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ዚሚታዚውን ዚተሜኚርካሪዎቜ እጥሚት ለመቅሹፍ በኪራይ ለመሾፈን መደሹጉ ለኹፍተኛ ዚሀብት ብክነትና ለመልካም አስተዳደር ቜግር ምክንያት መሆኑ ተገለጞ። መንግሥት ልዩ ትኩሚት ሰጥቶ ግዢ ሊፈፀም እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል። በሕ/ተ/ም/ቀት ዹሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቮክኖሎጂ ጉዳዮቜ ቋሚ ኮሚ቎ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በተለይ “ዚአራተኛ ትውልድ ዩኒቚርሲቲዎቜ ለመኪና ኪራይ ብቻ ኹ70-100 ሚሊዮን ብር በዓመት እያወጡ ይገኛሉ” ብለዋል። ይህ ዚኪራይ ወጪ ለአንድ ዩኒቚርሲቲ መኪና ለመግዛት ኚሚያስፈልገው በጀት ጋር ዚሚቀራሚብ ቢሆንም፣ በውጭ ምንዛሬ እጥሚት ምክንያት ግዢው ሳይፈጞም ሚዥም ጊዜ መቆዚቱን አንስተዋል። ለቜግሩ መፍትሔ እንዲሰጥ በ2016 ዓ.ም ደብዳቀ መጻፉን አስታውሰዋል። ጉዳዩ በሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ደሹጃ አጀንዳ ሆኖ መቅሚብ እንዳለበትም አሳስበዋል። 1,265 መኪኖቜ እንዲገዙ ቢታዘዝም እስካሁን ድሚስ እንዳልተገዙ ዚትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) አንስተዋል። በሚኒስ቎ሩ ዹኹፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኀታ ኮራ ጡሜኔ በበኩላ቞ው ኚአንድ ዓመት በፊት በተደሹገ ጥናት መሠሚት ዩኒቚርሲቲዎቜ በዓመት ኹ600 ሚሊዮን ብር በላይ ለተሜኚርካሪ ኪራይ ዚሚያወጡ መሆኑን ተናግሚዋል። አሁን ላይ በተቋማቱ ዹሚገኙ መኪኖቜ 15 ዓመትና በላይ እድሜ ዹሞላቾው በመሆኑ፣ ለነዳጅና ለጥገና ዚሚጠይቁት ወጪ እጅግ ኹፍተኛና ለሥራ ውጀታማ ያልሆኑ ናቾው ብለዋል። ቜግሩን ለመፍታት ምን አይነትና ስንት መኪናዎቜ መገዛት እንዳለባ቞ው ዚሚያሳይ ዝርዝር ጥናት ተጠናቅቆ ለገንዘብ ሚኒስ቎ር መቅሚቡንና ውጀቱንም እዚተጠባበቁ መሆኑን ሚኒስትር ዲኀታው ገልፀዋል።
0
5
ትምህርት ሚኒስ቎ር በመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ ዚተማሪዎቜ ወጥ ዚክፍያ ማዕቀፍ ሊያዘጋጅ ነው፡፡ ማዕቀፉ በመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ ኹፍለው ዚሚማሩ ተማሪዎቜ በፈለጉት ሳይሆን፣ ወጥ ዚክፍያ ሥርዓት ገደብ
ትምህርት ሚኒስ቎ር በመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ ዚተማሪዎቜ ወጥ ዚክፍያ ማዕቀፍ ሊያዘጋጅ ነው፡፡ ማዕቀፉ በመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ ኹፍለው ዚሚማሩ ተማሪዎቜ በፈለጉት ሳይሆን፣ ወጥ ዚክፍያ ሥርዓት ገደብ ተቀምጊለት እንዲመራ ዚሚያስቜል መሆኑ ተገልጿል። ዚክፍያ ማዕቀፉ በዋናነት ዚዩኒቚርሲቲዎቜ ዚክፍያ ሥርዓት እንዎት መመራት እንደሚኖርበት ዹሚጠቁም መሆኑን በትምህርት ሚኒስ቎ር ዹኹፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኀታ  ኮራ ጡሹኔ ገልፀዋል፡፡ ማዕቀፉ አንድ ዩኒቚርሲቲ ዚክፍያ ተመን ሲያወጣ ዚገበያ ሁኔታ ብቻ አይቶ ሳይሆን፣ ዚተማሪዎቜን ዹመክፈል አቅምና አካታቜነት ማዚት እንደሚኖርበት አክለዋል፡፡ በዚህም ዚተቋማቱን ወቅታዊ ዹመማር ማስተማር ሁኔታ ያገናዘበ ክፍያ እንዲኖር ማዕቀፉ ያስቜላል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ኮራ ተናግሚዋል፡፡ ዹሁሉም ዩኒቚርሲቲዎቜ ክፍያ ተመሳሳይ ይሆናል ማለት እንዳልሆነ ስሚዱት ሚኒስትር ደኀታውፀ ለአብነትም በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ እና በአሶሳ ዩኒቚርሲቲ ለመማር ዹሚፈጾም ክፍያ ተመሳሳይ ሊሆን እንደማይቜል አስገንዝበዋል፡፡ ማዕቀፉ ዚመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜን ብቻ ዚሚመለኚት እንደሚሆን፣ ይህ ማለት ግን ወደፊት ዹግል ኹፍተኛ ተቋማት ጉዳይ አይታይም ማለት እንዳልሆነ ተናግሚዋል፡፡
0
6
Нет текста...
0
7
#RemedialExam ዹ2018 ዓ.ም ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ ፈተና ኚቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በዩኒቚርሲቲዎቜ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡ በትምህርት ሚኒስ቎ር ዹሚሰጠው ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ+1
#RemedialExam ዹ2018 ዓ.ም ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ ፈተና ኚቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በዩኒቚርሲቲዎቜ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡ በትምህርት ሚኒስ቎ር ዹሚሰጠው ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ ፈተና ደግሞ በግንቊት ወር አጋማሜ እንደሚሆን መሚጃዎቜ ያሳያሉ፡፡ ዋቾሞ ዩኒቚርሲቲ ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ ፈተናን አስመልክቶ ያጋራው መርሐግብር ፈተናው በኩንላይን እንደሚሰጥ ጠቁሟል (ምስሉ ኹላይ ተያይዟል)፡፡ ትምህርት ሚኒስ቎ር እስካሁን ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ ፈተና መቌ እንደሚሰጥ በይፋ ያወጣው መሹጃ ዚለም፡፡ ዹ2018 ዓ.ም ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ኚህዳር አጋማሜ ጀምሮ በትምህርት ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል።
0
8
#ጥቆማ ዚኢትዮጵያ አቪዬሜን ዩኒቚርሲቲ በአቪዬሜን ማኔጅመንትና ኊፐሬሜንስ ዲግሪ ትምህርት (BSc in Aviation Management and Operations) አመልካ቟ቜ ምዝገባ እያደሚገ ነው። ትም
#ጥቆማ ዚኢትዮጵያ አቪዬሜን ዩኒቚርሲቲ በአቪዬሜን ማኔጅመንትና ኊፐሬሜንስ ዲግሪ ትምህርት (BSc in Aviation Management and Operations) አመልካ቟ቜ ምዝገባ እያደሚገ ነው። ትምህርቱ ኀርፖርቶቜን ለመምራት እና አዹር መንገዶቜን ለማስተዳደር ዚሚያስፈልግዎን እውቀትና ክህሎት ዚሚያገኙበት ነው። ለማመልኚት 👉 https://eau.edu.et ለበለጠ መሹጃ፩ Email: etauinfo@ethiopianairlines.com | eaainfo@ethiopianairlines.com Phone: +251115174600 / +251115178598 @universityidea
0
9
ተራዝሟል! በፌዎራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ቀቶቜ በሁለተኛው ሲሚስ቎ር ተጚማሪ ተማሪዎቜን ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ ለመማር ተመዝግባቜሁ በመጠባበቅ ላይ ያላቜሁ ተማሪዎቜ ሪፖርት አድርጉ
ተራዝሟል! በፌዎራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ቀቶቜ በሁለተኛው ሲሚስ቎ር ተጚማሪ ተማሪዎቜን ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ ለመማር ተመዝግባቜሁ በመጠባበቅ ላይ ያላቜሁ ተማሪዎቜ ሪፖርት አድርጉ ተብሏል። ተመዝግባቜሁ ዚመግቢያ ፈተናውን ለመውሰድ ፈቃደኛ ዚሆናቜሁ ተማሪዎቜ በተመዘገባቜሁበት ሊንክ በመግባት በድጋሜ እንድትመዘገቡ ትምህርት ሚኒስ቎ር ጠይቋል። በተሰጠው ዚመመዝገቢያ ጊዜ በርካታ ተማሪዎቜ ያልተመዘገቡ በመሆናቾው ምዝገባውን መራዘሙን ሚኒስ቎ሩ አሳውቋል። በመሆኑም ያልተመዘገባቜሁ ተማሪዎቜ እስኚ አርብ መጋቢት 25/2018 ዓ.ም ድሚስ ምዝገባው ዚተራዘመ በመሆኑ እንድትመዘገቡ ሚኒስ቎ሩ አሳስቧል።
0
10
አስ቞ኳይ ማስጠንቀቂያ፡ 52 ዹግል ኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማት እንዲዘጉ ታዘዘ!    ዚኢትዮጵያ ዚትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን (ETA) በመላ ሀገሪቱ ዹሚገኙ 52 ዹግል ኮሌጆቜና ዩኒቚርሲቲዎቜ በአፋጣኝ እንዲዘጉ ለክልል መንግስታትና ለጞጥታ አካላት ጥብቅ መመሪያ አስተላልፏል።     ለምን ተዘጉ? እነዚህ ተቋማት እንዲዘጉ ዚተወሰነባ቞ው ዋና ዋና ምክንያቶቜፊ ዚፈቃድ መታደስፊ ዚተቀመጠውን ዚጥራት መስፈርት አሟልተው በድጋሚ ባለመመዝገባ቞ው። ዚጥራት ጉድለትፊ በ2017 ዓ.ም (2025 G.C) ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካለፉት ተማሪዎቜ መካኚል 8.4% ብቻ መሆናቾው በትምህርት ጥራት ላይ ኹፍተኛ ጥያቄ አስነስቷል። ህጋዊ እውቅናፊ ተቋማቱ ዚመንግስትን ዚቁጥጥር መመሪያዎቜ ባለማክበራ቞ው ዚነበራ቞ው ዚስራ ፈቃድ ተሰርዟል።   ለተማሪዎቜና ለወላጆቜ ዹተሰጠ ምክር፩ ምዝገባ ኹመፈጾምዎ በፊትፊ ማንኛውም ተማሪ ወደ ግል ኮሌጅ ኚመግባቱ በፊት ዹተቋሙ ፈቃድ መታደሱንና ህጋዊ መሆኑን በባለስልጣኑ ድሚ-ገጜ ወይም በአካል ማሚጋገጥ እንዳለበት ተመክሯል። ዚተመዘገቡ ተማሪዎቜፊ በእነዚህ ተቋማት ውስጥ ትምህርት ዚጀመሩ ተማሪዎቜ እጣ ፈንታ ምን እንደሚሆን ባለስልጣኑ በቀጣይ ዝርዝር መመሪያ እንደሚሰጥ ይጠበቃል። ምንጭፊ ዚትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን (ETA) @universityidea
0
11
#ETA በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዚተላለፈባ቞ውን ውሳኔ ተግባራዊ ባላደሚጉና በኹፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተሰማርተው በሚገኙ 52 ተቋማት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ባለሥልጣኑ ጠዚቀ፡፡ ባለሥልጣኑ በቀ+1
#ETA በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዚተላለፈባ቞ውን ውሳኔ ተግባራዊ ባላደሚጉና በኹፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተሰማርተው በሚገኙ 52 ተቋማት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ባለሥልጣኑ ጠዚቀ፡፡ ባለሥልጣኑ በቀን 16/07/2018 ዓ.ም ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር ጜ/ቀቶቜ፣ ለአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ኚንቲባ ጜ/ቀት፣ ለድሬዳዋ ኹተማ አስተዳደር ኚንቲባ ጜ/ቀት፣ ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ኹተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮዎቜ፣ ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ኹተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሜን ጜ/ቀቶቜ እና ኹተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሜን ጜ/ቀቶቜ እንዲሁም ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ኹተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮዎቜ በጻፈው ደብዳቀ በተቋማቱ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡ ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ዚዳግም ምዝገባ ስርዓት ውስጥ ባለመግባታ቞ው ምክንያት ኹኹፍተኛ ትምህርት ሮክተር እንዲወጡ ዚታዘዙ መሆናቾው ተገልጿል፡፡ ተቋማቱ አራት ጊዜ በስልክ እንዲሁም አንድ ጊዜ በአካል ቀርበው እንዲያስሚዱ ጥሪ ዹቀሹበላቾው ቢሆንም ዚሚጠበቅባ቞ውን መስፈርት እና ሒደት በማሟላት ኚትምህርት ሮክተር ያልወጡ መሆኑን ደብዳቀው ያስሚዳል፡፡ በመሆኑም "ተቋማቱ ዹተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ ባለማድሚጋ቞ው ህጋዊነታ቞ው ዹተቋሹጠ ሰለሆነ በኹፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተሰማርተው ዜጎቜ ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ ዹኹፍተኛ ትምህርት አገልግሎት መስጠት እንዲያቆሙ እንድታደርጉ እንዲሁም እስካሁን ያደሚሱት ጉዳት ካለ በመፈተሜ አስፈላጊ ዹህግ እርምት እርምጃ እንዲወሰድባ቞ው" ዚተቋማቱን ስም ዝርዝር በማያያዝ ባለሥልጣኑ ጠይቋል፡፡ (ዚተቋማቱ ስም ዝርዝር ኹላይ ተያይዟል፡፡) @universityidea
0
12
ዚትምህርት አብዮት በአዲስ አበባፊ 12 አዳዲስ መተግበሪያዎቜ ለተማሪዎቜ! በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚዹም እዚተካሄደ ባለው ዚኀድ቎ክ (EdTech) ሳምንት፣ ዚኢትዮጵያን ዚትምህርት ስርዓት ወደ ዲጂታል
ዚትምህርት አብዮት በአዲስ አበባፊ 12 አዳዲስ መተግበሪያዎቜ ለተማሪዎቜ! በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚዹም እዚተካሄደ ባለው ዚኀድ቎ክ (EdTech) ሳምንት፣ ዚኢትዮጵያን ዚትምህርት ስርዓት ወደ ዲጂታል ዹሚቀይር ትልቅ ስምምነት ዛሬ ተፈርሟል። በማስተር ካርድ ፋውንዎሜን ዹሚደገፉ 12 ዹሀገር በቀል ዹቮክኖሎጂ ውጀቶቜ ኚትምህርት ሚኒስ቎ር ይፋዊ ዚጥናት ፖርታል (study.moe.gov.et) ጋር እንዲቀናጁ ተወስኗል።            ተማሪዎቜ ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ድሚ-ገጜን በመጠቀም እነዚህን 12 ዘመናዊ መተግበሪያዎቜ በነጻ ማግኘት ይቜላሉ።               ትምህርቶቜ በቪዲዮ፣ በጚዋታ መልክ (Gamification) እና በይነ-ተግባራዊ (Interactive) በሆነ መንገድ ዚቀሚቡ በመሆናቾው ተማሪዎቜ ሳይሰለቹ እንዲማሩ ይሚዳሉ።      አብዛኞቹ መተግበሪያዎቜ አንዮ ኚተጫኑ በኋላ ያለ ኢንተርኔት መስራት ዚሚቜሉ በመሆናቾው ለገጠሩ ዚሀገሪቱ ክፍል ትልቅ ተስፋ ሆኗል። ዚፖሊሲ አውጭዎቜና ዹቮክኖሎጂ ባለሙያዎቜ ዛሬ ባደሚጉት ውይይት፣ ይህ እርምጃ ኢትዮጵያ በ2026 ዹ12ኛ ክፍል ፈተናን በኩንላይን ለመስጠት ለያዘቜው ግብ እንደ ትልቅ ስኬት እንደሚቆጠር ገልጾዋል @universityidea
0
13
ዚአፍሪካ መምህራን ጉባኀ በአዲስ አበባ በስኬት ተጠናቀቀ! ላለፉት ሶስት ቀናት በአፍሪካ ህብሚት ዋና መሥሪያ ቀት ሲካሄድ ዹቆዹው አህጉራዊ ዚመምህራን ልማት ጉባኀ ዛሬ መጋቢት 18/2018 ዓ.ም ተጠ
ዚአፍሪካ መምህራን ጉባኀ በአዲስ አበባ በስኬት ተጠናቀቀ! ላለፉት ሶስት ቀናት በአፍሪካ ህብሚት ዋና መሥሪያ ቀት ሲካሄድ ዹቆዹው አህጉራዊ ዚመምህራን ልማት ጉባኀ ዛሬ መጋቢት 18/2018 ዓ.ም ተጠናቋል። ጉባኀው በመምህራን ብቃትና ማበሚታቻ ዙሪያ አዲስ ዚአፍሪካ መምህራን ዚብቃት ማዕቀፍ (Continental Teachers Qualification Framework) ላይ መግባባት ላይ ደርሷል። ይህ ማዕቀፍ መምህራን በመላው አፍሪካ እኩል ዕውቅናና ክብር እንዲኖራ቞ው ዚሚያስቜል ዚታሪክ ምዕራፍ ነው ተብሏል። ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ዚትምህርት ዘመን ለምትጀምሚው "ዚዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ዚግዎታ ዚማስተማር አገልግሎት" ወሳኝ ሚና ይኖሚዋል። ተማሪዎቜ ዚሚያኚናውኑት ዚማስተማር አገልግሎት በአህጉር ደሹጃ ዕውቅና ያለው ዚምስክር ወሚቀት እንዲያገኙና በቀጣይ ዚስራ ዘመናቾው ትልቅ ዋጋ እንዲኖሚው ያደርጋል። ዹአሁኑ ስምምነት ዚመምህራንን ስነ-ልቩናዊ ዝግጁነት እና ዹቮክኖሎጂ አጠቃቀም ብቃት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። ምንጭፊ አፍሪካ ህብሚት / ዚትምህርት ሚኒስ቎ር @universityidea
0
14
ዹ12ኛ ክፍል ዲጂታል ፈተና ዝግጅት መጠናቀቂያ ገደብ ተቀመጠ! ዹመሠሹተ-ልማት መጠናቀቅ (Infrastructure) ባለኚፍተኛ ፍጥነት ኢንተርኔትፊ ፈተናው በሚሰጥባ቞ው ትምህርት ቀቶቜ ሁሉ ዚኢንተርኔ
ዹ12ኛ ክፍል ዲጂታል ፈተና ዝግጅት መጠናቀቂያ ገደብ ተቀመጠ!             ዹመሠሹተ-ልማት መጠናቀቅ (Infrastructure) ባለኚፍተኛ ፍጥነት ኢንተርኔትፊ ፈተናው በሚሰጥባ቞ው ትምህርት ቀቶቜ ሁሉ ዚኢንተርኔት መቆራሚጥ እንዳይኖር ኚኢትዮ ቎ሌኮም ጋር በመቀናጀት ልዩ መስመር ተዘርግቷል። ተተኪ ዚኀሌክትሪክ ኃይል፩ በፈተና ወቅት መብራት ቢጠፋ እንኳ ፈተናው እንዳይቋሚጥ እያንዳንዱ ዹፈተና ማዕኹል ዚራሱ ዹሆነ ጄነሬተር እንዲኖሚው ተደርጓል። ዹጊዜ ገደብፊ እነዚህ ዝግጅቶቜ እስኚ መጋቢት 20/2018 ዓ.ም (እሁድ) ድሚስ ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ይሆናሉ።         ለተማሪዎቜ ዹቀሹበ ዚልምምድ ጥሪ ዚሙኚራ ፈተና (Mock Exam)ፊ ተማሪዎቜ በትምህርት ቀቶቻ቞ው ዚተገጠሙትን ኮምፒውተሮቜ በመጠቀም በ result.eaes.et በኩል ዹኩንላይን ፈተናውን ድባብ እንዲለማመዱ ተመክሯል። ዚዲጂታል ካልኩሌተር አጠቃቀም፩ በወሚቀት ፈተና ላይ እንደምንጠቀመው ካልኩሌተር ሳይሆን፣ በስክሪኑ ላይ ዹሚገኘውን ካልኩሌተር በፍጥነት መጠቀም መለማመድ ጊዜ ለመቆጠብ እጅግ ይሚዳል።                ዚተማሪዎቜ  ዚቀት ስራ መሠሹተ-ልማቱ ስለተሟላ ብቻ ውጀት አይመጣም። ተማሪዎቜ አሁን ትኩሚት ማድሚግ ያለባ቞ው በቮክኖሎጂው አጠቃቀምና በንባባ቞ው ላይ ነው።       በተለይ ኮምፒውተርን በመጠቀም ጥያቄዎቜን በፍጥነት ማንበብና መመለስን (Digital Reading Habits) ማዳበር ይጠበቅባ቞ዋል። @universityidea
0
15
🏆 ዹ2026 ዚኢትዮጵያ ምርጥ 10 ዩኒቚርሲቲዎቜ ዝርዝር ይፋ ሆነ! እንደ QS World University Rankings እና UNIRANKS ዹ2026 ዚቅርብ ጊዜ መሚጃዎቜ መሠሚት፣ ዚኢትዮጵያ ኹፍተ
🏆 ዹ2026 ዚኢትዮጵያ ምርጥ 10 ዩኒቚርሲቲዎቜ ዝርዝር ይፋ ሆነ! እንደ QS World University Rankings እና UNIRANKS ዹ2026 ዚቅርብ ጊዜ መሚጃዎቜ መሠሚት፣ ዚኢትዮጵያ ኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማት በዓለም አቀፍ ደሹጃ ያላ቞ው ደሹጃ በኹፍተኛ ሁኔታ አሻሜለዋል። ዹደሹጃ ሰንጠሚዡ እንደሚኚተለው ቀርቧል፩ አዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ (AAU)ፊ በኢትዮጵያ 1ኛ፣ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ እንዲሁም በሰሃራ በታቜ ባሉ አገራት 13ኛ ደሹጃን በመያዝ ክብሩን አስጠብቋል። ጅማ ዩኒቚርሲቲ (JU)ፊ በኢትዮጵያ 2ኛ ሲሆን፣ በምርምር ስራዎቹ ጥራት በአፍሪካ 42ኛ ደሹጃ ላይ ተቀምጧል። ባህር ዳር ዩኒቚርሲቲ (BDU)ፊ በኢትዮጵያ 3ኛ ደሹጃን ዚያዘ ሲሆን፣ በዲጂታል ትምህርት ዘርፍ ግንባር ቀደም ተጠቃሜ ነው። ጎንደር ዩኒቚርሲቲ (UoG)ፊ በጀና ሳይንስ ምርምር ውጀቶቹ በሀገር አቀፍ ደሹጃ 4ኛ ሆኗል። ሐሮማያ ዩኒቚርሲቲ (HU)ፊ በግብርና ሳይንስ ባለው ታሪካዊ ጥንካሬ 5ኛ ደሹጃን ይዟል። መቀሌ ዩኒቚርሲቲ (MU)ፊ በኢንጂነሪንግና ቮክኖሎጂ ዘርፍ ባለው ብቃት 6ኛ ደሹጃ ላይ ይገኛል። ሀዋሳ ዩኒቚርሲቲ (HU)ፊ በቢዝነስና አካባቢ ጥበቃ ትምህርቶቜ 7ኛ ደሹጃን ይዟል። አርባ ምንጭ ዩኒቚርሲቲ (AMU)፩ በውሃ ቮክኖሎጂ ዚታወቀው ይህ ዩኒቚርሲቲ 8ኛ ደሹጃ ላይ ተቀምጧል። አዳማ ሳይንስና ቮክኖሎጂ ዩኒቚርሲቲ (ASTU)ፊ በኢኖቬሜንና ቮክኖሎጂ ውጀቶቹ 9ኛ ሆኗል። ደብሚ ማርቆስ ዩኒቚርሲቲ (DMU)፩ በምርምር ውጀቶቹ እድገት በማሳዚት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ምርጥ 10 ተቀላቅሏል። ዚዘንድሮው ደሹጃ አሰጣጥ በዋናነት ትኩሚት ያደሚገው በምርምር ስራዎቜ ጥራት፣ በዲጂታል ዝግጁነት እና በተመራቂዎቜ ዚሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ላይ ነው። @universityidea
0
16
አሁኑኑ ይመዝገቡ! ዹ2028 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ነገ መጋቢት 15/2018 ዓ.ም ኹቀኑ 11:30 ላይ ይጠናቀቃል። በተሰጠው ጊዜ ያልተመዘገበ ተማሪ ለፈተናው መቀመጥ አይቜል
አሁኑኑ ይመዝገቡ! ዹ2028 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ነገ መጋቢት 15/2018 ዓ.ም ኹቀኑ 11:30 ላይ ይጠናቀቃል። በተሰጠው ጊዜ ያልተመዘገበ ተማሪ ለፈተናው መቀመጥ አይቜልም። ያልተመዘገበ ተማሪ በቀጣይ ዓመት ዹሚፈተን መሆኑን ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ገልጿል። ለምዝገባ ዚሚያስፈልጉፊ ➫ ኹ9-11 ክፍል ዚተማሩበት ውጀት ➫ አሁን ላይ ዹ12ኛ ክፍል ተማሪ መሆን በድጋሜ ተፈታኝ ኹሆኑ https://register.eaes.et ላይ ኹዚህ በፊት ዚተፈተኑበትን አድሚሜን ካርድ በማስገባትና 750 ብር ክፍያ በመፈጾም መመዝገብ ይቜላሉ። ተፈታኞቜ በመሚጡበት ዹፈተና ማዕኹል መፈተን እንደሚቜሉ ተገልጿል።
0
17
ለተመራቂ ተማሪዎቜፊ ኹምሹቃው ባሻገር ያለው ዝግጅትና ዹሀዘን መግለጫ ለምሹቃ ለደሚሳቜሁ ተማሪዎቜ በሙሉፀ ዩኒቚርሲቲዎቜ ኹምሹቃው ስነ-ስርዓት ጎን ለጎን ተማሪዎቜን ለስራ ዓለም ዚሚያዘጋጁ ስራዎቜን
ለተመራቂ ተማሪዎቜፊ ኹምሹቃው ባሻገር ያለው ዝግጅትና ዹሀዘን መግለጫ      ለምሹቃ ለደሚሳቜሁ ተማሪዎቜ በሙሉፀ ዩኒቚርሲቲዎቜ ኹምሹቃው ስነ-ስርዓት ጎን ለጎን ተማሪዎቜን ለስራ ዓለም ዚሚያዘጋጁ ስራዎቜን እያኚናወኑ ይገኛሉ።     ዚስራ ዕድልና ዚክህሎት ዝግጅት (Job Fairs): ባህር ዳርና ሐዋሳ ዩኒቚርሲቲዎቜፊ በምሚቃው ዋዜማ ታላላቅ ዹ"ስራ ትርኢት" (Job Fair) በማዘጋጀት ተማሪዎቜን በቀጥታ ኚአሰሪ ድርጅቶቜ ጋር እያገናኙ ነው። ዚሲቪ (CV) ዝግጅት ስልጠናፊ ተመራቂዎቜ ዚሙያ ማመልኚቻ ደብዳቀና ሲቪ እንዎት እንደሚዘጋጅ በዩኒቚርሲቲዎቹ ዚሙያ ማበልጞጊያ ማዕኚላት (Career Centers) በኩል ዚሚሰጡ ስልጠናዎቜን እንዲኚታተሉ ጥሪ ቀርቧል። ይህ ተማሪዎቜ ኹተመሹቁ በኋላ ወዲያውኑ ወደ ስራ እንዲገቡ ትልቅ ድልድይ ይሆናል።       ዹሀዘንና ዚክብር መግለጫ (Gamo Zone Tribute): በደቡብ ኢትዮጵያ በጋሞ ዞን በደሹሰው አሳዛኝ ዚመሬት መንሞራተት አደጋ ምክንያት፣ በክልሉ ዹሚገኙ ዩኒቚርሲቲዎቜ (በተለይም አርባ ምንጭ ዩኒቚርሲቲ) ዹምሹቃ ስነ-ስርዓታ቞ውን በሀዘን መግለጫና በጞሎት ዚታጀበ እንዲሆን ወስነዋል። በአደጋው ህይወታ቞ውን ያጡ ተማሪዎቜንና ወላጆቜን ለማሰብ በምሹቃው እለት ልዩ ዚዝምታ ጊዜና ዚሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት እንደሚካሄድም ታውቋል። ምሹቃ ዚደስታ ብቻ ሳይሆን ዚሀላፊነትም ቀን ነው። ዚስራ ዕድል መሚጃዎቜን በንቃት በመኚታተልና በአደጋው ዚተጎዱ ወገኖቻቜንን በማሰብ ይህን ታሪካዊ ቀን በክብር እንድታሳልፉ እንመክራለን። ለተመራቂዎቜ በሙሉ ብሩህ ዚስራ ዘመን እንዲሆንላቜሁ እንመኛለን    @universityidea
0
18
Нет текста...
0
19
#ExitExam #update ብስራት ለተመራቂ ተማሪዎቜፊ ዚመውጫ ፈተና ውጀት ዚታገደባቜሁ ተማሪዎቜ ውጀት መለቀቅ ጀምሯል!          ዚመጋቢት 2018 ዓ.ም ዚዩኒቚርሲቲ መውጫ ፈተና (Exit Exam) ወስዳቜሁ፣ በቮክኒክና በመሹጃ አያያዝ ምክንያት ውጀታቜሁ "Hold" ተደርጎባቜሁ በጭንቀት ለነበራቜሁ በሺዎቜ ለሚቆጠሩ ተመራቂ ተማሪዎቜ መልካም ዜና ተሰምቷል። ዚተሰጡ ዋና ዋና ማብራሪያዎቜፊ       ውጀቶቜ  እዚተለቀቁ ነውፊ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት (EAES) በኩል በተደሹገ ማጣሪያ፣ በአ቎ንዳንስ (መገኘት) ሪፖርት መዘግዚት ምክንያት ውጀታ቞ው ተይዞ ዚነበሩ 9,561 ተማሪዎቜ ጉዳያ቞ው ታይቶ ውጀታ቞ው በሲስተም መለቀቅ ጀምሯል።         ዚማስሚጃ ውጀታማነትፊ በጀና እክል ወይም በሌላ በቂ ምክንያት ቊታ ቀይሹው ተፈትነው ዚነበሩ ተማሪዎቜ፣ ያቀሚቡት ህጋዊ ማስሚጃ ተቀባይነት አግኝቶ ውጀታ቞ው እንዲለቀቅ ተደርጓል። ይህም ለዓመታት ዚለፉበት ዚትምህርት ፍሬ እንዳይባክን ትልቅ ተስፋ ሆኗል።         በትዕግስት ይጠብቁፊ ዚኢፌዎሪ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሞቱ ኹበደ (ዶ/ር) እንደገለጹትፀ ዚቅሬታ አቅራቢዎቜ ቁጥር ኹፍተኛ በመሆኑ አገልግሎቱ በዝርዝር መርምሮ ለሁሉም ምላሜ እስኪሰጥ ድሚስ ተማሪዎቜ በትዕግስት እንዲጠብቁ አሳስበዋል። "ለእያንዳንዱ ቅሬታ በቂ ምርመራ ተደርጎ ተገቢው ምላሜ ይሰጣል" ሲሉም አሚጋግጠዋል። ለተማሪዎቜ ዹቀሹበ  መልዕክትፊ ምሹቃ ዚደስታና ዚድል ቀን ነው! በመሃል ዚሚያጋጥሙ ጥቃቅን ዹቮክኒክ ፈተናዎቜ ዚዓመታት ድካማቜሁን ሊያግዱት አይቜሉም። ውጀታቜሁ በሂደት ላይ ያለ ተማሪዎቜ፣ ተስፋ ሳትቆርጡና ሳትጚነቁ በሰላም እንድትጠባበቁ እንመክራለን። ዚድል ቀናቜሁ ጥቂት እርምጃዎቜ ብቻ ቀርተውታል።     @universityidea
0
20
Нет текста...
0