Addis ketema Education 2018
Открыть в Telegram
1 117
Подписчики
+324 часа
+627 дней
+33930 день
Архив постов
+4
ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡ሰኞ ሰኔ 22/2018 ዓ.ም የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር የጽ/ቤቱ ኃላፊ እንዱሁም የስራዎች አስተባሪዎች እና ሠራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡ የሰኞ ማለዳ የሠራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር "የመንግስት ሠራተኞች ብቃቶች" በሚል ርዕስ ዙሪያ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሱፐርቫይዘር በሆኑት በአቶ ነጋሽ እምቢአለ የቀረበ ሲሆን በክፍለ ከተማው ጽ/ቤት ውስጥ ላሉ የጽ/ቤቱ ሠራተኞች የመንግስት ሠራተኞች ብቃቶች በሆኑት የባህርያዊ ብቃት እና የቴክኒካል ብቃት ዙሪያ ላይ የራሳቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን በእውቀት ሽግግሩ ላይ በተገኙ ሰራተኞች በቀረበው የእውቀት ሽግግር ርዕስ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት እና የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የእውቀት ሽግግሩን በመሩት አቶ ሶሪ ሹሚ የማጠቃለያ ሀሳብ ተሰጥቶበት የዛሬው የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተጠናቋል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
ሰላም እንዴት ቆያችሁ?፦ ነገ ጠዋት የተመራቂ መምህራን የአድዋ ሙዚየም መግብያ በር በምዕራብ በር /Western Gate/ መሆኑን ለሚመለከተው አካል ሁሉ አሳውቁ።
የ2018 ዓ.ም የአንደኛ ደረጃ ፣ የመካከለኛ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ትቤቶች የተማሪዎች ከክፍል ወደ ክፍል የዝውውር ፖሊሲ.pdf
ተመራቂዎች፦ በአሰላ እና በደብረ ብርሃን ኮሌጅ የተማሩት የቅድመ-1ኛ ደረጃ መምህራን ቅዳሜ ማለትም በ20/10/2018ዓ.ም ጠዋት በአደዋ 00 ግቢ ውስጥ የሚመረቁ መሆኑን እየገለፅን። ተመራቂዎች አርብ በ19/10/18 2:30 ሚኒሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተገኝታችሁ ኦረንቴሽን እንድትወስዱ ጥሪ እናስተላልፋለን።
+6
ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡ሰኞ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር የጽ/ቤቱ ኃላፊ እንዱሁም የስራዎች አስተባሪዎች እና ሠራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡ የሰኞ ማለዳ የሠራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር "የራስ ተነሳሽነት(self motivation)" በሚል ርዕስ ዙሪያ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የመምህራን ልማት ባለሙያ በሆኑት በወ/ሮ ሳሮን ለገሰ የቀረበ ሲሆን በክፍለ ከተማው ጽ/ቤት ውስጥ ላሉ የጽ/ቤቱ ሠራተኞች የራስ ተነሳሽነት መጨመር እንዲሁም ጥቅሙ ዙሪያ ላይ የራሳቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን በእውቀት ሽግግሩ ላይ በተገኙ ሰራተኞች በቀረበው የእውቀት ሽግግር ርዕስ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት እና የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ እና የጽ/ቤቱ የስራዎች አስተባባሪ በሆኑት በአቶ ቤኩማ ደበሎ የማጠቃለያ ሀሳብ ተሰጥቶበት የዛሬው የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተጠናቋል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
+1
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበት የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ሆነ።ሰኔ 13/2018ዓ.ም የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞች በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል። ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል። ዝርዝሩን ከሚከተለው ሠንጠረዥ ይመልከቱ። የፈተና ስርቆትንና ኩረጃን በጋራ እንከላከል! #ምንጭ: የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+9
በከተማ አስተዳደሩ በ2018 የትምህርት ዘመን የተሰጡት የ6ኛና የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተናዎች በስኬት ተጠናቀዋል።
(ሰኔ 12/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ድረስ የተሰጡት የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በ199 የፈተና ጣቢያዎች ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንዲሁም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በ201 የፈተና ጣቢያዎች ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጡ ቆይተው በስኬት ተጠናቀዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክብር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በከተማ አስተዳደሩ ሲሰጡ የቆዩት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተናዎች በስኬት መጠናቀቃቸዉን ገልጸው ለስራዉ ውጤታማነት ከቅድመ ዝግጅት ተግባራት ጀምሮ በየደረጃው የተዋቀሩት የኮማንድ ፖስት አደረጃጀት አባላት ፣ የፈተና አስፈጻሚዎች ፣ የፀጥታ አካላት ፣ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ፣ ወላጆችና ተማሪዎች ሳበረክቱት ለቆዩት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ቢሮ ሀላፊው በከተማ አስተዳደሩ የተሰጠው የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን 85,017 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ጠቁመው በፈተናው ሂደት ውስጥ 199 የፈተና ጣቢያ ሀላፊዎች ፣ 767 አስፈታኝ ት/ቤቶች ፣ 782 ሱፐርቫይዘሮች እና 2414 ፈታኞች መሳተፋቸውን አመላክተዋል።
በ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናም 86,783 ተማሪዎች ፈተናዉን መውሰዳቸዉን ፤ በፈተናዉ ሂደት ውስጥም 201 ጣቢያ ሀላፊዎች ፣ 667 አስፈታኝ ት/ቤቶች ፣ 793 ሱፐርቫይዘሮች እና 2434 ፈታኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል።
ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመሰራቱ ፈተናው በሁሉም የፈተና መስጫ ጣቢያዎች ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ማስቻሉንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+9
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና መሰጠት ተጀመረ።
(ሰኔ 11/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰኔ 11 እና ሰኔ 12/2018 ዓ.ም የሚሰጠው የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በ201 የፈተና ጣቢያዎች በዛሬው እለት ተጀምሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ፈተናው ሰላማዊ ሆኖ ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ ቀደም ብሎ ኮማንድ ፖስት ከማደራጀት ጀምሮ ልምድ ያላቸውን የፈተና አስፈጻሚዎች በመመልመል በየፈተና ጣቢያው መመደቡን የፈተናውን አጀማመር ለመመልከት ከአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ ፣ ከምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ እንዲሁም ከክፍለ ከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ብሩክ ተክለማርያም ጋር በመሆን በዳግማዊ ብርሀን አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተገኙበት ወቅት አስታውቀዋል።
በከተማ አስተዳደሩ 86,783 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ ተመዝግበው ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ጠቁመው በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች የፈተናውን ሂደት የሚከታተሉ አመራሮችን ጨምሮ የጸጥታ አካላትና የፈተና አስፈጻሚዎች መመደባቸውን አመላክተዋል።
ተማሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ በየትምህርት ቤቱ የማጠናከሪያ ትምህርት ከመሰጠቱ ባሻገር ደረጃውን የጠበቀ የሞዴል ፈተና እንዲወስዱ መደረጉን ገልጸው ፈተናው ከኩረጃ ነጻ እንዲሆን ለተማሪዎችና የፈተና አስፈጻሚዎች ኦረንቴሽን መሰጠቱን አመላክተዋል።
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በ18 የፈተና ጣቢያዎች 7,893 ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውን የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ ገልጸው ፈተናው በሁሉም ጣቢያዎች ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ክፍለ ከተማው በት
Repost from N/a
በአዲስ ክፍለ ከተማ ት/ፅ/ቤት ስር ላላችሁ የመንግስት KG ት/ቤቶች ር/መምህራን በሙሉ፦ በቅድመ 1ኛ ደረጃ (KG) ስልጠና ላይ ለተሳተፉ መምህራን፣ አስተባባሪዎች እና ሱፐርቫይዘሮች ሰርተፊኬት ስለተዘጋጀ የስም ስህተት እንዳይኖር፣ ከታች በተላከው ዝርዝር (List) ላይ ሰልጣኞች ስማቸውን እንዲያረጋግጡ ይደረግ። በተጨማሪም ከስማቸው ፊት ለፊት የት/ቤታቸው እና የክፍለ ከተማቸው ስም ተፅፎ የ2ቱም ተጠምሮ በቴሌግራም አድራሻችን እንድትልኩልን እንጠይቃለን።
ተመራቂዎች፦ በአሰላ እና በደብረ ብርሃን ኮሌጅ የተማሩት የቅድመ-1ኛ ደረጃ መምህራን ቅዳሜ ማለትም በ13/10/2018ዓ.ም የሚመረቁ መሆኑን እንገልፃለን።
🏆🏆🏆Congratulations እንኳን ደስ አላችሁ Baga Gammaddan🏆🏆🏆
🎉🎉🎉🎉🎉🎉💐💐💐💐💐💐🎉🎉🎉🎉
✍ ታሪክ ተሰራ Seenaan hojjatameeraa✍
✍ ት/ቤታችን የውጪ ኢንስፔክሽን ሲያከሄድ መቆያቱ ይታወቃል:: በዚሁም እንደ ትምህርት ቤት በደረግናው ከፍተኛ ዝግጅት ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ደረጃ 4 ላይ ማረፍ ችሏል:: የልፋታችን ውጤት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ
✍ Akka mana barumsaa keenyaa inspection ala irra akka turee ni beekama.kanaaf akka mana barumsaatti qophii cimaa goonneen qabxii ol aanaa galmeesisun sadarkaa 4 irra galuu dandeenyeera. Qabxii hojjii cimaadhan dhufee waan ta'eef baga gammaddan 🎉🎉🎉🏆🏆🏆🏆🏆🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉
+4
የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡ሰኞ ሰኔ 01/2018 ዓ.ም የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር የጽ/ቤቱ ኃላፊ እንዱሁም የስራዎች አስተባሪዎች እና ሠራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡ የሰኞ ማለዳ የሠራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር የመርሃ ግብሩ ሰብሳቢ በሆኑት በአቶ አንተነህ ገ/እግዚአብሔር መድረክ መሪነት "የመስሪያ ቤት (ተቋም ) ውጤታማነት” በሚል ርዕስ ዙሪያ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የአፋን ኦሮሞ ምገባ ባለሙያ በሆኑት በእቶ መልካሙ ቶሎሳ የቀረበ ሲሆን በክፍለ ከተማው ጽ/ቤት ውስጥ ላሉ የጽበ/ቤቱ ሠራተኞች በተቋም ውጤታማነት አስተዋፅኦ በሚያደርጉ ጉዳዮች ዙሪያ የራሳቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን በእውቀት ሽግግሩ ላይ በተገኙ ሰራተኞች በቀረበው የእውቀት ሽግግር ርዕስ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት እና የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የዛሬው የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተጠናቋል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
በአዲስ ክፍለ ከተማ ት/ፅ/ቤት ስር ላላችሁ የመንግስት ት/ቤቶች ር/መምህራን በሙሉ፦
1. ጡረታ የወጡ መ/ራንን ከት/ቤታችሁ በጡረታ ብቻ መገለላቸውን ሳታረጋግጡ ምንም የመታወቂያ መረጃ እንዳትሠጡ፤ ከተረጋገጠ በኋላ ደግሞ በE-school መመዝገብን እንዳትዘነጉ፤
2. ጡረተኞችን የአንበሣ መታወቂያ ለመውሰድ ስትልኩ በE-school መመዝገባቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ ከት/ቤት አስይዛችሁ እንድትልኩ፣
3. አዲሱ መታወቂያ የጠፋባቸውና ስም ያስቀየሩ የድጋሜ መታወቂያ መስጠት ስላልተጀመረ ት/ቢሮ ሔደው አንዳይጉላሉ እና መታወቂያቸውን በጥንቃቄ እንዲይዙ መልዕክት እንድታስተላልፉላቸው እናሳስባለን።
ለመምህራን የባስ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚዎች በሙሉ፦
የዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቱ የሚሰጠው ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ብቻ መሆኑን አውቃችሁ፣ ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር መሰረት እንድትጠቀሙበት እናሳስባለን።
📌📌📌አስቸኳይ
ለሁሉም አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችበዚህ የነጻ የትምህርት እድል ተጠቃሚ መሆኑ ለሚፈልጉ ተማሪዎች በሚከተለው ሊንክ https://forms.gle/NYxESRDkg8xSWKB76 ተጠቅመው በእናንተ በኩል ተደራሽ እንድታደርጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+1
የተከለሰ የ2018 የትምህርት ዘመን የትምህርት የማጠቃለያ ፈተና መርሃ-ግብር
(ግንቦት 18/2018 ዓ.ም)
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
