Nursing 2026
Открыть в Telegram
👩⚕️This channel aims to build theoretically and practically confident and effective nurses !!! The channel share important documents, informations, questions,and explanations which are related to nursing department.
Больше1 869
Подписчики
Нет данных24 часа
-17 дней
-2030 день
Архив постов
1 869
ለነርሲንግ ባለሙያዎች የተዘጋጀውን የብቃት ማሻሻያ ስልጠና ለመውሰድ የተመረጡ ባለሙያዎችን ስለማሳወቅ
የጤና ሚኒስቴር በማስተማሪያና ሶስተኛ ደረጃ ሆስፒታሎች የሚሰጠውን የጤና አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራት ለማሻሻል ከሚያደርጋቸው ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ስራዎች አንዱ የነርሲንግ አገልግሎትና ጤና ክብካቤ ደረጃን ማሳደግ ነው ፡፡
ይህን ግብ ተግባራዊ ለማድረግ የጤና ሚኒስቴር በከፍተኛ ደረጃ ሆስፒታሎች የሚሰሩ ነርስ ባለሙያዎችን በማወዳደር የብቃት ማሻሻያ ስልጠና ለማስጀመር በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡
ስለሆነም ከሆስፒታላችሁ የአምስት ወር የሙያ ማሻሻያ ስልጠና ለመወሰድ ከተወዳደሩት አመልካቾች መካከል መስፈርቱን አሟልተው የተገኙ የነርስ ባለሙያዎችን ስም ዝርዝር አያይዘን የላክን መሆኑን እየገለፅን ሰልጣኞች አስፈላጊውን ውልና ስምምነት ከሆስፒታሉ ጋር በማድረግ ወደ ፊት በምናሳውቀው የጊዜ ሰሌዳ እና የስልጠና ቦታ ተገኝተው ሪፖርት እንዲያደርጉ በእናንተ በኩል አሰፈላጊው ትብብር እንዲደረግላቸው በአክብሮት እንጠይቃለን ፡፡
Via: HIVN
Also check here in addition to the attached list
Note: This list may change at anytime, therefore we encourage applicants to check your emails and contacting responsible bodies to follow updates.
*edited
➡ Share
1 869
#NGAT
የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ እስከ ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም ብቻ የሚከናወን መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል፡፡
የመመዝገቢያ ሊንክ 👇
https://ngat.ethernet.edu.et
ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ የግድ ያስፈልጋል፡፡ የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር ሲሆን፤ በምዝገባ ወቅት በቴሌብር በኩል መክፈል ይጠበቅባችኋል።
ምዝገባው በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚከናወን መሆኑን የገለፀው አገልግሎቱ፤ የፈተና ጣቢያዎች ከምዝገባ በኋላ የተመዝጋቢ ቁጥሩ ታይቶ የሚወሰን መሆኑን ጠቁሟል፡፡
የፈተና መስጫ ጊዜው ወደፊት ይገለጻል ተብሏል፡፡
1 869
ለብቃት ምዘና ፈተና መረጃ በማስተሳሰር ላይ ለምትገኙ የጤና ሙያ ተመራቂዎች በሙሉ
___
የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ ስማችሁን ከብሄራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥራችሁ (National ID FAN 16 Digit) ጋር በማስተሳሰር ላይ የምትገኙ ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ያላገባደዳችሁ የጤና ሙያ ተመራቂዎች፤ የመረጃ ማስተሳሰሪያ ጊዜ ገደብ እስከ ሀምሌ 24/2018 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን እያሳወቅን ፣ በተጨማሪም ለፈተናው አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ የሚረዱና ጠቃሚ መረጃዎችን የያዙ Information Booklets እንዲሁም Practice Test Booklets ከዚህ በታች በተቀመጡት Zip files ውስጥ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
1 869
የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተናን ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ ተመዛኞች በሙሉ
____
የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ ጤና ባለሙያዎች በነሀሴ ወር 2018 ዓ.ም የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለመስጠት ተመዛኞች ከሰኔ 30/2018ዓ.ም ጀምሮ መረጃችሁን በማስተሳሰር ላይ እንደምትገኙ ይታወቃል፡፡
ስለዚህም መረጃችሁን ወደ ሲስተም ያላስገባችሁ ነባር እና አዲስ ተመዛኞች ማስተሳሰር የምትችሉት እስከ ሃምሌ 17/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ መሆኑን ተገንዝባችሁ ይህንን https://hple.moh.gov.et/ ማስፈንጠሪያ/Link/ በመጫን የብሄራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (National ID FAN 16 Digit) በማስገባት አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ለምዝገባ እንድትዘጋጁ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
▪ ይህ መረጃን የማስተሳሰር ሂደት እንዳለቀ የፈተና ጣቢያ መረጣ ሂደት እንደሚቀጥል እናሳውቃለን፡፡
▪ በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፉችሁ ተመዛኞች የስም ዝርዝራችሁን በተማራችሁበት ተቋም አማካኝነት ወደ ሲስተም ማስጫን የሚጠበቅባችሁ መሆኑን እናሳስባለን።
1 869
Specifically for students who take CoC exam for the second time you should see this vedio to be free from confussion.👇👇👇
https://www.tiktok.com/@nursewithmulu/video/7662322968168549653?_r=1&u_code=f2c4fal3c19f49&preview_pb=0&sharer_language=en&_d=f3f8b6f17d7k11&share_item_id=7662322968168549653&source=h5_m×tamp=1784127395&user_id=7616001973473723412&sec_user_id=MS4wLjABAAAAYpAFGipCrpI-URqOVOlcXHy-5Cw9yCZykLvr18jz4yra14ILJJxnCklPsyRGFui8&item_author_type=1&social_share_type=0&utm_source=copy&utm_campaign=client_share&utm_medium=android&share_iid=7640935335359678228&share_link_id=4ab8e898-44f1-4fe4-9574-f30dcc47392d&share_app_id=1233&ugbiz_name=MAIN&ug_btm=b8727%2Cb2878&sp_root_share_link_id=4ab8e898-44f1-4fe4-9574-f30dcc47392d&link_reflow_popup_iteration_sharer=%7B%22click_empty_to_play%22%3A1%2C%22dynamic_cover%22%3A1%2C%22follow_to_play_duration%22%3A-1.0%2C%22profile_clickable%22%3A1%7D&enable_checksum=1&sp_level=1&sp_root_u=f2c4fal3c19f49&sp_root_d=f3f8b6f17d7k11
1 869
🌹🌹🌹Congratulation for students who pass the exam !!!
👌But for students who fail the exam you wait a few moment of time the next exam is on july so prepare yourself.
1 869
የሙያ ፈቃድ ፈተና ውጤት
በሰኔ 2018 ዓ.ም የተሰጠውን የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከነገ ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ https://hple.moh.gov.et ላይ በመግባትና የብሔራዊ መለያ ቁጥር (FAN) እና Password በማስገባት የፈተና ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።
በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከነገ ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት በአጭር ጥሪ ቁጥር 952 በሥራ ሰዓት በመደወል ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በማሳወቅ ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተናውን ያለፋችሁ ተመዛኞች ከሰኞ ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም ጀምሮ ስም ዝርዝራችሁ ወደ ክልል የሚላክ ስለሆነ፣ የሙያ ፍቃዳችሁን የ12ኛ ክፍል በተማራችሁበት ክልል ማውጣት ትችላላችሁ ተብሏል።
1 869
A 32-year-old female came to a hospital with complaints of cough with sputum and chest pain of
five days duration. Upon examination, the patient looks severely ill, in respiratory distress, and the
trachea is slightly deviated to the right. Absent breath sound on auscultation and dull sound on percussion
are noted. Examination findings show a temperature of 38.5 degrees centigrade; pulse rate of 109
beats/min; and respiratory rate of 32 breaths/min. The physician diagnosed the patient with pleural
effusion.
What is the most likely manifestation consistent with the diagnosis of pleural effusion?
A. Cough with sputum and chest pain
B. Use of respiratory muscle on breathing and fever
C. Absence of breath sound and dull not on percussion
D. Respiratory rate of 32 breaths/ min and pulse rate of 109 beat/minute
1 869
A 35-year-old male patient was admitted to a surgical ward with second-degree flame burn on his
entire anterior trunk, anterior and posterior right arm, and anterior part of his left leg.
What is the most likely f total body surface area (TBSA) burnt in this case?
A. 18 percent
B. 27 percent
C. 36 percent
D. 45 percent
1 869
A 62-year-old man with HIV AIDS came to a hospital with a complaint of lesions around his
right shoulder that do not pass the midline of the body. On assessment, lesions have blister and tingling
sensation. He experiences severe pain over the entire dermatome supplied by the affected nerve root. The
patient avoids movement and does not want clothing or bed linen to touch the affected shoulder.
What is the most appropriate priority management for the patient?
A. Administer antibiotics
B. Administer Acyclovir
C. Administer Tramadol
D. Administer calamine lotion
1 869
#MoH
የተግባር ፈተና የምትወስዱ የአንስቴዥያ ሙያ ተመራቂዎች ምዝገባ ከሰኔ 24 እስከ 26/2018 ዓ.ም ብቻ የሚከናወን መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።
ሰኔ 19/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዳችሁ የአንስቴዥያ ሙያ ተመዛኞች ከዛሬ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
የጽሁፉ ፈተና ያለፋችሁ የአንስቴዥያ ሙያ ተመዛኞች፥ የተግባር ፈተና ለመውሰድ ከሰኔ 24-26/2018 ዓ.ም ብቻ በኦንላይን https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት የብሔራዊ መለያ ቁጥር (FAN) እና Password በማስገባት መፈተኛ ጣቢያ በመምረጥ ምዝገባችሁን እንድታከናውኑ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
ከላይ ከተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውጪ ምንም ዓይነት የምዝገባ ጥያቄ የማያስተናግድ መሆኑን ማኒስቴሩ ገልጿል።
🔔 ከዚህ ቀደም የተግባር ፈተና ተፈትናችሁ ፈተናውን ያላለፋችሁ የአንስቴዥያ ተመዛኞች፥ የተግባር ፈተናውን #በድጋሜ ለመውሰድ የብሔራዊ መለያ ቁጥራችሁን (FAN) ከስማችሁ ጋር ማስተሳሰር ይጠበቅባችኋል።
1 869
#ተጨማሪ
የጤና ተመራቂዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና ውጤት በቅርቡ ይፋ የሚደረግ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር ገልጿል።
ከሰኔ 17-19/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች (ከአንስቴዥያ በስተቀር) ውጤት በቅርቡ ይፋ እስከሚደረግ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ሚኒስቴር ጠይቋል።
Telegram chat group :https://t.me/Ethio_Nursing_2026
Titok : https://www.tiktok.com/@nursewithmulu
Youtube: https://youtube.com/@nursing-simplified1?si=Fq5SEyEkVz-s5jtI
1 869
ለብቃት ምዘና ፈተና ተመዛኞች በሙሉ
__
ጤና ሚኒስቴር ከሰኔ 17 እስከ 19/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና በ28 የፈተና ጣቢያዎች በጥሩ ሁኔታ እየተሠጠ ይገኛል፡፡
በዚህም መሠረት:-
1. የነገ 19/10/2018 ዓ.ም የፈተናው መርሃ-ግብር Pharmacy, Anesthesia, Dental Medicine, Emergency and Critical Care Nursing, Environmental Health እና Psychiatric Nursing ሙያ ላይ የተመዘገባችሁ ተመዛኞች ምዘናው የጠዋቱ በ3 ሰዓት እንዲሁም የከሰዓቱ በ8 ሰዓት እንደሚጀመር አውቃችሁ ቀድማችሁ በፈተና ጣቢያ ተገኝታችሁ ምዘናውን እንድትወስዱ እያሳስባለን።
2. በተመሳሳይ መልኩ በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና የወስዳችሁ የጤና ሙያ ተመራቂዎችም የብቃት ምዘና ፈተናውን በሃምሌ ወር 2018 ዓ.ም መጨረሻ ለመስጠት በቅርብ ቀን ምዝገባ ስለምንጀምር ተመዛኞች አስፈላጊውን የትምህርት ማስረጃ እንድታሟሉ እና ለምዝገባ ራሳችሁን ዝግጁ እንድታደርጉ እናሳስባለን።
ለወቅታዊ ታማኝ የጤና መረጃዎች ⤵️
