cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

መሰረተ ትምህርት ዘኦርቶዶክስ

"ቤተክርስቲያንን አየኋት፣ አወኳት፣ወደድኳት" ቅዱስ ያሬድ “በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል፥ የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤” ኤፌሶን 2፥20 "ሳትማሩና መጻሕፍት ሳታነቡ የምታገኙት ዕውቀት አይኖርም" መጽሐፈ ቀሌምንጦስ

Больше
Рекламные посты
590
Подписчики
Нет данных24 часа
+17 дней
+9430 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

“ይህን ሳስብ ነፍሴ በእኔ ውስጥ ፈሰሰች፥ ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ምስጋና መኖሪያ ስፍራ እገባለሁና፤ በዓል የሚያደርጉ ሰዎች የደስታና ምስጋና ቃል አሰሙ።” መዝሙር 42፥4
Показать все...
4🙏 2🥰 1
“በመጽናትና መጻሕፍት በሚሰጡት መጽናናት ተስፋ ይሆንልን ዘንድ አስቀድሞ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፎአልና።” ሮሜ 15፥4
Показать все...
8🔥 1
ትምህርቶቹን እዚ ቻናል ላይ የተለቀቁትን ከመጀመርያው ጀምሮ ከአምስቱ አእማደ ምሥጢራት ጀምራችሁ ማስታወሻ እየያዛችሁ ስሙ ፣ ጽሁፎቹንም አንብቡ ፣ የመጽሐፍ ጥቆማ ላይ ያሉትን መጽሐፎችም እንደ አቅማችሁ እየገዛችሁ አንብቡ ። ቤተክርስቲያናችን በብዙ ተኩላዎች ተከባለች ከውስጥም ከውጭም ብዙ ፈተና አለ በተኩላዎቹ በቀላሉ የሚበላው ቤተክርስቲያንን የማያውቅ እና በልማድ የሚመላለስ ክርስትያን ነው ስለዚህ ከልማድ ክርስትና ውጡ እና ወደ ተግባራዊ ክርስትና ጉዞውን ጀምሩ ለዚህም ዋናው ትጥቅ የቤተክርስቲያንን ትምህርት ማወቅ ፣ ያወቁትንም በተግባር ለመኖር እየታገልን ተጋድሎ ማድረግ ነው። ማቴዎስ 7 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁴ ስለዚህ ይህን ቃሌን ሰምቶ የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን በዓለት ላይ የሠራ ልባም ሰውን ይመስላል። ²⁵ ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት ገፋው፥ በዓለት ላይም ስለ ተመሠረተ አልወደቀም። ²⁶ ይህንም ቃሌን ሰምቶ የማያደርገው ሰው ሁሉ ቤቱን በአሸዋ ላይ የሠራ ሰነፍ ሰውን ይመስላል። ²⁷ ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት መታው፥ ወደቀም፥ አወዳደቁም ታላቅ ሆነ። ²⁸ ኢየሱስም ይህን ነገር በጨረሰ ጊዜ ሕዝቡ በትምህርቱ ተገረሙ፤ እንደ ጻፎቻቸው ሳይሆን ²⁹ እንደ ባለ ሥልጣን ያስተምራቸው ነበርና። 👉ልባችንን በዓለት ላይ የሰራን ልባም ክርስትያኖች መሆን ግዴታችን ነው። 👈
Показать все...
7🙏 2
“የመጀመሪያ እምነታችንን እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ፥ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና፤” ዕብራውያን 3፥14 “እንግዲህ በሰማያት ያለፈ ትልቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፥ ጸንተን ሃይማኖታችንን እንጠብቅ።” ዕብራውያን 4፥14
Показать все...
12
“ከሰነፍ ሰው ፊት ራቅ፥ በእርሱ ዘንድ የእውቀትን ከንፈር አታገኝምና።” ምሳሌ 14፥7
Показать все...
👍 13🔥 2🙏 1
"መጽሐፍ ቅዱስ ከቤተክርስቲያን ሲወጣ ከባህር እንደወጣ አሳ ይሆናል ፣ አሳው በህይወት ለመኖር በባህር ውስጥ መሆን እንዳለበት ሁሉ መጽሐፍ ቅዱስም ህይወትን እንዲሰጥ በቤተክርስቲያን ውስጥ መሆን አለበት ይሄ ማለት መጽሐፍ ቅዱስን ከቤተክርስቲያን መነጽርነት ውጭ በሌላ የምንፍቅና እና የፍልስፍና መነጽር ማንበብ ወደ ህይወት ሳይሆን ወደ ሞት ይመራል ስለዚህ የእግዚአብሔርን ቃል ስናነብ በእግዚአብሔር ቤት አረዳድ እና መንፈስ ነው ማንበብ ያለብን" “እኛ ግን ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን።” ሐዋርያት 6፥4 “በዚያን ጊዜም ስለ እርሱ ደግሞ የታሰርሁበትን የክርስቶስን ምሥጢር እንድንነግር እግዚአብሔር የቃሉን ደጅ ይከፍትልን ዘንድ ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ፤” ቆላስይስ 4፥3
Показать все...
12😁 1
ስለ በዓላት የተሰጡ ትምህርቶች ይለቀቃሉ ፣ የመጽሐፍት ጥቆማም ይኖራል ከታች ላሉት ጥያቄዎች በተቻለ መጠን አጠር ያሉ መልሶችን አዘጋጅቼ እለቅላችኋለሁ 1.በዓል የምንለው ምንድነው? 2.በብሉይ ኪዳን በዓላት ነበሩ ወይ? በአዲስ ኪዳንስ የምናከብራቸው በዓላት መሰረታቸው ምንድነው? ዓበይት እና ንኡሳን በዓላት የሚባሉትስ የትኞቹ ናቸው ? 3. በዓላትን ስናከብር እንዴት ማክበር አለብን? ቤተክርስቲያንን የማይወክል የበዓላት አከባበር የቱ ነው ? 4. በዓላትን ማክበር ስራ እንዳንሰራ ያደርገናል ወይ? ከቤተክርስትያን ውጭ ያሉ አካላት እንደሚሉት ለኢትዮጵያ ድህነት ምንጭ የእኛ በዓላትን ማክበር ነው ወይ ? 5. በዓላትን ማክበር ገንዘብን ማባከን ነው ወይ? 6. የቅዱሳን እና የመላእክትን በዓል ማክበር ጣኦት አምላኪነት ወይም የእግዚአብሔርን ክብር ለፍጡራን መስጠት ነው ወይ? 7.በዓላትን የምታከብረው የእኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብቻ ናት ወይስ ሌሎቹም ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ አብያተ ክርስትያናት ያከብራሉ? 8. የንግሥ በዓላት የሚባሉት የትኞቹ ናቸው? ነገሰ የሚባለውስ ምን ለማለት ነው? 9.በየቀኑ የሚታሰቡትን ቅዱሳን ለማወቅ ስንፈልግ ማንበብ የምንችለው የተዘጋጀ መጽሐፍ አለ ወይ? 10."በዓል" እና "በአል" ልዩነታቸው ምንድነው? 11. በዓልን ማክበር ለመንፈሳዊ ህይወታችን የሚሰጠን ጥቅም አለ ወይስ ጥቅም የሌለው ልምምድ ነው? 12.የግዝት በዓላት የሚባሉት የትኞቹ ናቸው?
Показать все...
8🙏 1
"የቤተክርስትያን በዓላት" 👇👇
Показать все...
የሌሎቹን ከመስማታችሁ እና ከማንበባችሁ በፊት የራሳችሁን ትምህርት ተማሩ መጻሕፍትንም አንብቡ !! የራሳችሁን ሳታውቁ የሌሎችን መስማት ማለት ትጥቅ ሳይዙ ወደ ጦርነት እንደመሄድ ነው መጨረሻውም ጥፋት ነው የሚሆነው ስለዚህ መጀመርያ ቅድሚያ ለቤተክርስቲያን ትምህርት ስጡ በዚ ዘመን በስሜት እና በልማድ መመላለስ አያዋጣም የሚያዋጣው የሚማር እና የሚያነብ ኦርቶዶክስ መሆን ነው!!! ፍቅረ ማርያም
Показать все...
👍 9🙏 4
"አንተ ሰው ! ቃለ እግዚአብሔርን ተማር! ባትለወጥም ዝም ብለህ ተማር ! ሁልጊዜ ተማር ! ላትስተካከል ትችላለህ ፣ ላትለወጥ ትችላለህ ግን ተማር ! ቢያንስ ቢያንስ ጥሩ ሰው እንኳን ባትሆን ራስህን ለመውቀስ የትችልበት ዓቅም ታገኛለህ ። ካልተማርክ ግን ራስህን እንኳን መውቀስ የምትችልበት ዓቅም አታገኝም። ስለዚህ ተማር ! ስትማር ቢያንስ ኃጢአት እንኳን ስትሠራ ራስህን እየወቀስክ ትሠራለህ ። ይህች የንስሐ በር ትሆንልሃለች። አንድ ቀን ወደ ንስሐ ትመራሃለች!!"            ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
Показать все...
🥰 19 7🙏 1
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.