ኢት-መጽሐፍት | ETHIO-BOOKS
Открыть в Telegram
👉 "የምታነበው መጽሐፍ ለአንተ የሚያስብልህ ሳይሆን አንተ እንድታስብ የሚያደርግ ነው።" ሃርፐር ሊ Fiction (ልቦለድ), History (ታሪክ), Politics (ፖለቲካ), Psychology (ስነልቦና), Biography (ግለ-ታሪክ), Self-help(ራስ አገዝ),& Philosophy(ፍልስፍና) የሀገር ውስጥ & የውጪ ሀገር መጽሐፎችን ያገኛሉ!አስተያየትዎን እዚህ @Desutech_bot ያድርሱን
Больше1 989
Подписчики
-324 часа
-67 дней
-5630 день
Архив постов
📚ርዕስ -የአና ማስታወሻ Anne frank - Diary of young girl
📝ደራሲ - Anne Frank
👤ተርጓሚ - አዶኒስ
📜ዘውግ - ግለ ታሪክ
📅የህትመት ዘመን - 1996
📖የገፅ ብዛት - 266
በአለም ላይ እጅግ ከፍተኛ የሽያጭ መጠን ካስመዘገቡ 10 መፅሐፍት መካከል አንዱ የሆነ ሊነበብ የሚገባው መፅሀፍ ነው ።
Join us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📚⛪️ፍኖተ አእምሮ📚
ይኻ መጽሀፍ ፍልስፍናዊ ስነ ልቦናዊ እንዲሁም መንፈሳዊ እይታችንን እንድናሰፋ በብዙ ይረዳናል።
✅ርዕስ ፡ ፍኖተ አእምሮ
💎ደራሲ : ልዑል ራስ ካሳ ኃይሉ
📚የገፅ ብዛቱ : 301
ውስጡ በምዕራፍና በቁጥር የተከፋፈለ ሲሆን 36 ምዕራፎች አሉት ።አፅንኦት እንዲሰጠው የሚፈልጉትን ሃሳብ ጥያቄ እያሉ በማንሳት ከታች ምላሽ ብለው ማብራሪያን ያክሉበታል።
መጽሀፉ የማይነካው ሃሳብ ያለ አይመስለኝም ብዙ ሃሳቦችን አንስቷል ።አለማዊና መንፈሳዊ ህይወትን እንዴት በዕርጋታና በሰከነ መንፈስ መምራት እንደምንችል ያሳያል።
መጽሀፉን እንድታነቡት እየጠቆምኩ ከመፅሀፉ የወጡትን በጥቂቱ ላጋራችሁ።
~~
💎#አሳብህ ብዙ የሚመኝ አንዱን ይዞ የማይሠራ ሲሆንብህ ሰይጣን በጎም ሥራ እንዳትሠራ ባለመሥራትህም እንዳትደነግጥበት መልካምን በማሳሰብ እየከለከለ በጥበብ ሰንሰለቱ እንዳሰረህ ዕወቅ።
ስለዚህ አንተ አንድ ሁነህ አሳብህን ብዙ አታድርግ።
የምትኖርበትን የማትለቀው አንድ ስራ ያዝ እንጂ ምኞትህን በየቀኑ አትለዋውጠውአንዱን መያዝ አንዱን መልቀቅ የእብደትና የዝሙት ነው እንጂ ምንም ደግ አሳብ ቢሆን የዕውቀት ጠባይ አይደለም ስለዚህ ቀድሞ የዠመርከውን ትንሹን የበጎ ምኞትህን ሳትሰራው ደግሞ ሌላ ትልቅ አትመኝ።
❤️ስለዚህ ትንሹን በጎ ሥራህን ሳትለቅ በዚያው ላይ ለመጨመር ትጋ እንጂ የያዝከውን ለመልቀቅ ያለዐቅምህ ለመመኘት ምክንያትና ጥቅስ አትፈልግ።
አንተ ለሠራኸው ሥራ ያጸድቀኛል ይጠቅመኛል ያልክ እንደ ሆነ እንደ ጣዖት ሠሪዎች የገዛ ሥራህን ሰጪና ነሺ አድርገህ ማምለክእንዳይሆንብህ ሥራዬ ብቻ ያጸድቀኛል አትበል።
ዕምነት ያለው ብርቱ የተባለ ሰው የሚስትበት ከንቱ ሃሳብ ከትሩፋት ስራዬ እጠቀማለው ማለቱ ነው ይህም ትልቅ ትምክህት ነው በአምላክ ቸርነት እንጂ የትሩፋት ስራው እና ዕውቀቱ ለንፅህና ዋጋው አይደለምና ለሰው የሚጠቅመው በቸርነቱ መታመን ነው።
✅አእምሮ ማለት በእግዚአብሔር አርአያ ከተፈጠረች ከነፍስ ባህርይ የሚገኝ እጅግ ታላቅ ነገር ነውና አእምሮህን በማይረባው ሁሉ ቦታ እየበተንክ ለከንቱ ሥራ የጨረስከው እንደሆነ ጌታው አምኖ የሰጠውን ወርቅ ላዝማሪ ፣ለዘዋሪ፣ለመሸታ፣ ለጨዋታ እያደረገ ጨርሶ እንደሚቀጣ እብድ ተቆጥረህ ወደ እግዚአብሔር ቅጣት እንዳታልፍ አእምሮህን ለከንቱ ሥራ እንዳታባክን ተጠንቀቅ።
✅ስንፍና የነፍስንም የስጋንም ሥራ ሁሉ አስቀርቶ ይጎዳል በመጨረሻም የነፍስና የሥጋን ድኸነት ያመጣል። የሚያደክመውም ሥራ ስላጣ በቁጣ ሀጢአትን ሁሉ ያሰራል ከሰውሁሉ ያጣላል። ልቡናውንም ሥራ ስላስፈታው መጨረሻው ዝንጋት የሰውንም ወረታ መመለስ ያስቀራል።
✅ሰው እንኳን ከመሰሉ ሰው ከእንስሳ አይበልጥምና
በልቡ ትዕቢትን
ባለባበሱ ኩራትን
ባነጋገሩ ትምክሕትን
ባካሄዱ መቋፍን
ባስተያየቱ ፊት ማጥቆርን ጨርሶ እንዲተው የሚያኮራ አካል እንዳልተፈጠረለት ማወቅ ነው የሚገባው።
ሰው መባል የሥጋና የነፍስ ስም ነው እንጂ ያንዱ አካላችን ስም አይደለም።
አንድ ጊዜ ፈቃደ ነፍሱን አንድ ጊዜ ፈቃደ ሥጋውን እያፈራረቀ የሚሠራ አካል ለሁለት ጠባይ ተገዥ ስለ ሆነ ያማርኛችን ሊቆች በሁለት ፊደል #ሰ፡ው በሚል ስም ጠሩት።
✅በዚህ ዓላም የምናየውም የምንሰማውም የምንሰራውም መምሰል ነው እንጂ መሆን የለውም።
ይኸንን ልትረዳ ብትሻ መዠመሪያ በኛ አሳብ የምናየው ሰውነታችን
እየቆመ ሲሄድ
እየተናገረ ሲያሳምር
እየሠራ ሲያሳይ ቁም ነገር ያለው ትልቅ መስሎ ይታየናል። ከጥቂት ቀን በሆላ የቆመው ሥጋ በሞት ወድቆ የሚናገረው አንደበት ተዘግቶ የሠራው ፈርሶ መስሎ የነበረው ሁሉ ለዐይንም ጠፍቶ ለልብም ተረስቶ ውሸት ይሆናል።
👉 @et_books1
👉 @et_books1
ግጥሎት ፡ 2
(ግጥምና ፀሎት)
ሲጫንበት ቀንበር
ሲጠናበት ሸክም
ለምን አይረታ
ለምን ሰው አይደክም?
ግፈፈው ፅልመቱን
ሽረፍልኝ ሌቱን
አቅናልኝ መንገዱን
ወይም ፅናት ስጠኝ
ወይ ችረኝ መልመዱን።
ሲጋልበኝ ዘመን
ልክ እንደ ሹም በቅሎ
ሲጠምብኝ ህይወት
ሲከብድ እንደ አለሎ
ወይ ጠቁመኝ መላ
ሸክሜን የሚያቀል
ደግመህ ዝራኝና
ደሞ እንዳዲስ ልብቀል።
አቁመኝ መልሰህ
እንዳልቀር ጨንግፌ
ሰባብሬ ልውጣ
ቅርፊቴን ቀፍፌ።
ንሸጣ : በዕውቀቱ ስዩም
Join us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
የሰው ልጅ አካል አስደናቂ እውነታዎች ❗️
1. የአንድ ሰው በሰውነቱ ውስጥ ያለው ደም ክብደት ከአጠቃላይ ከሰውየው ክብደት 8 በመቶ ብቻ ይመዝናል፡፡
2. ምንም እንኳን በተፈጥሮ ሁለት ኩላሊት ቢኖረንም በሕይወት ለመኖር አንዱ ብቻ ያስፈልገናል፡፡
3. የሰው ልጅ አፍንጫ 1 ትሪሊዮን የተለያዩ ሽታዎችን መለየት ይችላል፡፡
4. ቆዳችን ትልቁ የሰውነታችን አካል ሲሆን ከክብደታችን ውስጥ 15 በመቶውን ይይዛል፡፡
5. ልባችን በአማካኝ በሕይወት ዘመናችን ለ3ቢሊዮን ያህል ጊዜ ይመታል፡፡
6. ሳይንቲስቶች የምናዛጋበትን ትክክለኛ ምክንያት እስካሁን አልደረሱበትም፤ነገር ግን የሰውነት ሙቀትን ለማመጣጠን እንደሚረዳ ይታመናል፡፡
7. የእጃችን ጠፍር ከሞትን በኃላ አያድግም፡፡
8. የሰው ልጅ ብቸኛ አገጭ ያለው ፍጥረት ነው፡፡
9. አውራ ጣት የራሱ የሆነ ትርታ አለው፡፡
10. በሰው አፍ ውስጥ የሚገኙት የባክቴሪያዎች ቁጥር በዓለማችን ከሚኖረው ሕዝብ ብዛት እኩል ወይም ሊበዛ ይችላል፡፡
11. በአንድ ቀን ደማቸን 19,312 ኪሎሜትር ያህል ይሮጣል፡፡
12. የሰው ልጅ አይን 10 ሚሊዮን የተለያዩ ቀለማትን መለየት የሚችል ሲሆን፤ ነገር ግን አእምሮአችን ሁሉንም ማስታወስ አይችልም፡፡
13. አንድ ሰው በአማካኝ 35 ቶን ወይም 35,000 ኪሎግራም ክብደት ያለው ምግብ በዕድሜ ዘመኑ ይመገባል፡፡
14. በየአንዳንዱ ቀን የሰው ልጅ 1 ሚሊዮን የቆዳ ሐዋሳት (ሴል) ያጣል፡፡ ይህ ደግሞ በዓመት 2 ኪሎ ይደርሳል፡፡
15. በሰውነታችን ውስጥ ትልቁ ሕዋስ (ሴል) በሴቶች ማህፀን ውስጥ የሚገኘው እንቁላል ሲሆን ያለማጉያ መነፅር እንዲሁ በአይናችን ማይት ይቻላል፡፡ በሰውነታችን ውስጥ ትንሹ ሴል ደግሞ የወንድ ዘር ፈሳሽ (ስፐርም ሴል ) ነው፡፡
Join us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📖ርዕስ= የብርሃን ፈለጎች
✍️ደራሲ=አለማየሁ ገላጋይ
🔍ዘውግ= ልቦለድ
🧾 የገፅ ብዛት= 248
Join us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
